መክብብ 8 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መክብብ 8:1-17

1ነገሮችን መግለጽ የሚችል፣

እንደ ጠቢብ ያለ ሰው ማን ነው?

ጥበብ የሰውን ፊት ታበራለች፤

የከበደ ገጽታውንም ትለውጣለች።

ንጉሥን ታዘዝ

2በእግዚአብሔር ፊት መሐላ ስለ ፈጸምህ፣ የንጉሥን ትእዛዝ አክብር እልሃለሁ። 3ከንጉሥ ፊት ተጣድፈህ አትውጣ፤ የወደደውንም ማድረግ ስለሚችል ለጥፋት አትሰለፍ። 4የንጉሥ ቃል የበላይ ስለሆነ እርሱን፣ “ምን ታደርጋለህ?” ማን ሊለው ይችላል?

5እርሱን የሚታዘዝ ሁሉ አይጐዳም፤

ጥበበኛም ልብ ትክክለኛውን ጊዜና ተገቢውን አሠራር ያውቃል።

6የሰው መከራ እጅግ ቢጫነውም፣

ለሁሉም ነገር ትክክለኛ ጊዜና ተገቢ አሠራር አለው።

7ሰው የወደ ፊቱን ስለማያውቅ፣

ሊመጣ ያለውን ማን ሊነግረው ይችላል?

8ሰው ነፋስን መቈጣጠር አይችልም8፥8 ወይም መንፈሱን ለማቈየት አይችልም

በዕለተ ሞቱም ላይ ሥልጣን ያለው ማንም የለም፤

በጦርነት ጊዜ ማንም ከግዴታ ነጻ እንደማይሆን፣

ክፋትም የሚለማመዷትን አትለቃቸውም።

9ከፀሓይ በታች የተሠራውን ሁሉ በአእምሮዬ መርምሬ፣ ይህን ሁሉ አየሁ። ሰው ሰውን ለመጕዳት ገዥ የሚሆንበት ጊዜ አለ። 10እንዲሁም ወደ ቅዱሱ ስፍራ ይመጡና ይሄዱ የነበሩት ክፉዎች ተቀብረው አየሁ፤ ይህን ባደረጉበት ከተማም ይመሰገኑ ነበር8፥10 አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆችና ሰብዓ ሊቃናት (አቍዊላ) እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን ተረስተዋል ይላሉ።፤ ይህም ደግሞ ከንቱ ነው።

11በወንጀል ላይ ባፋጣኝ ፍርድ ካልተሰጠ፣ የሰዎች ልብ ክፉን በማድረግ ዕቅድ ይሞላል። 12ኀጥእ መቶ ወንጀል ሠርቶ ዕድሜው ቢረዝምም፣ እግዚአብሔርን የሚያከብሩ፣ ፈሪሀ እግዚአብሔር ያላቸው ሰዎች መልካም እንደሚሆንላቸው ዐውቃለሁ። 13ነገር ግን ክፉዎች እግዚአብሔርን ስለማይፈሩ መልካም አይሆንላቸውም፤ ዕድሜያቸው እንደ ጥላ አይረዝምም።

14በምድር ላይ የሚከሠት ሌላም ከንቱ ነገር አለ፤ ጻድቃን ለክፉዎች የሚገባውን፣ ክፉ ሰዎችም ለጻድቃን የሚገባውን ይቀበላሉ፤ ይህም ደግሞ ከንቱ ነገር ነው አልሁ። 15ለሰው፣ ከፀሓይ በታች ከመብላት፣ ከመጠጣትና ከመደሰት ሌላ የተሻለ ነገር ስለሌለ፣ በሕይወት ደስ መሰኘት መልካም ነው አልሁ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ከፀሓይ በታች በሰጠው የሕይወት ዘመኑ ሁሉ በሥራው ደስታ ይኖረዋል።

16ጥበብን ለማወቅና ሌት ተቀን እንቅልፍ የማያውቀውን በምድር ያለውን የሰውን ድካም ለመገንዘብ በአእምሮዬ ስመረምር፣ 17እግዚአብሔር ያደረገውን ሁሉ አየሁ። ከፀሓይ በታች የሚደረገውን ማንም ሊያውቅ አይችልም፤ ሰው ለመመርመር ብዙ ቢጥርም፣ ትርጕሙን ማግኘት አይችልም፤ ጠቢብም እንኳ ዐውቀዋለሁ ቢል፣ ፈጽሞ ሊገነዘበው አይችልም።

New International Version – UK

Ecclesiastes 8:1-17

1Who is like the wise?

Who knows the explanation of things?

A person’s wisdom brightens their face

and changes its hard appearance.

Obey the king

2Obey the king’s command, I say, because you took an oath before God. 3Do not be in a hurry to leave the king’s presence. Do not stand up for a bad cause, for he will do whatever he pleases. 4Since a king’s word is supreme, who can say to him, ‘What are you doing?’

5Whoever obeys his command will come to no harm,

and the wise heart will know the proper time and procedure.

6For there is a proper time and procedure for every matter,

though a person may be weighed down by misery.

7Since no-one knows the future,

who can tell someone else what is to come?

8As no-one has power over the wind to contain it,

so8:8 Or over the human spirit to retain it, / and so no-one has power over the time of their death.

As no-one is discharged in time of war,

so wickedness will not release those who practise it.

9All this I saw, as I applied my mind to everything done under the sun. There is a time when a man lords it over others to his own8:9 Or to their hurt. 10Then too, I saw the wicked buried – those who used to come and go from the holy place and receive praise8:10 Some Hebrew manuscripts and Septuagint (Aquila); most Hebrew manuscripts and are forgotten in the city where they did this. This too is meaningless.

11When the sentence for a crime is not quickly carried out, people’s hearts are filled with schemes to do wrong. 12Although a wicked person who commits a hundred crimes may live a long time, I know that it will go better with those who fear God, who are reverent before him. 13Yet because the wicked do not fear God, it will not go well with them, and their days will not lengthen like a shadow.

14There is something else meaningless that occurs on earth: the righteous who get what the wicked deserve, and the wicked who get what the righteous deserve. This too, I say, is meaningless. 15So I commend the enjoyment of life, because there is nothing better for a person under the sun than to eat and drink and be glad. Then joy will accompany them in their toil all the days of the life God has given them under the sun.

16When I applied my mind to know wisdom and to observe the labour that is done on earth – people getting no sleep day or night – 17then I saw all that God has done. No-one can comprehend what goes on under the sun. Despite all their efforts to search it out, no-one can discover its meaning. Even if the wise claim they know, they cannot really comprehend it.