መሳፍንት 7 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 7:1-25

ጌዴዎን ምድያማውያንን ድል አደረገ

1ይሩበኣል የተባለው ጌዴዎን፣ ከእርሱም ጋር የነበሩት ሰዎች ሁሉ በጧት ተነሥተው በሐሮድ ምንጭ አጠገብ ሰፈሩ። የምድያማውያንም ሰፈር እስራኤላውያን ከሰፈሩበት በስተ ሰሜን በኩል፣ በሞሬ ኰረብታ አጠገብ በሸለቆው ውስጥ ነበር። 2እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “ምድያማውያንን በእጃቸው አሳልፌ እንዳልሰጥ አብረውህ ያሉት ሰዎች በጣም ብዙ ናቸው፤ እስራኤላውያን የገዛ ኀይላቸው እንዳዳናቸው በመቍጠር እንዳይታበዩብኝ፣ 3‘ማንም የፈራ ቢኖር የገለዓድን ተራራ ትቶ ወደ መጣበት ይመለስ’ ብለህ ለሕዝቡ ዐውጅ።” ስለዚህ ሃያ ሁለቱ ሺሕ ሲመለሱ ዐሥሩ ሺሕ ብቻ ቀሩ።

4እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “አሁንም ሰዎቹ ብዙ ናቸው፤ ወደ ወንዝ ይዘሃቸው ውረድ፤ በዚያም እለይልሃለሁ። ‘ይህ ከአንተ ጋር ይሂድ’ የምለው፣ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ነገር ግን፣ ‘ይህ ከአንተ ጋር አይሂድ’ የምለው፣ ከአንተ ጋር አይሄድም።”

5ስለዚህ ጌዴዎን ሰዎቹን ወደ ወንዝ ይዟቸው ወረደ፤ እዚያም እግዚአብሔር፤ “ውሻ በምላሱ እየጨለፈ እንደሚጠጣ ሁሉ፣ በምላሳቸው የሚጠጡትን፣ በጕልበታቸው ተንበርክከው ከሚጠጡት ለይ” አለው። 6ሦስት መቶ ሰዎች ውሃውን በእጃቸው እያፈሱ ጠጡ፤ የቀሩት ሁሉ ግን ለመጠጣት በጕልበታቸው ተንበረከኩ።

7እግዚአብሔርም ጌዴዎንን፣ “ውሃውን በእጃቸው እያፈሱ በጠጡት ሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ፤ ምድያማውያንንም በእጃችሁ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፤ የቀሩት በሙሉ ወደየመጡበት ይመለሱ” አለው። 8ጌዴዎንም የቀሩትን እስራኤላውያን በሙሉ ወደ የድንኳናቸው እንዲመለሱ አደረገ፤ ሦስት መቶውን ግን አስቀራቸው፤ እነርሱም የሚመለሱትን ሰዎች ስንቅና መለከት ወሰዱ።

በዚህ ጊዜ የምድያማውያኑ ሰፈር ከእነርሱ በታች በሸለቋማው ውስጥ ነበር። 9በዚያች ሌሊት እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “ተነሥ፤ በሰፈሩም ላይ ውረድ፤ በእጅህ አሳልፌ ሰጥቼሃለሁና። 10አደጋ ለመጣል የምትፈራ ከሆነ ግን፣ ፉራ ከተባለው አገልጋይህ ጋር ወደ ሰፈሩ ውረድ፤ 11የሚሉትንም አድምጥ፤ ከዚያ በኋላ በሰፈሩ ላይ አደጋ ለመጣል ድፍረት ታገኛለህ።” ስለዚህም ጌዴዎን አገልጋዩን ፉራን አስከትሎ እስከ ሰፈሩ ዳርቻ ወረደ። 12ብዛታቸው እንደ አንበጣ መንጋ የሆነ ምድያማውያን፣ አማሌቃውያንና ሌሎችም የምሥራቅ ሕዝቦች በሸለቆው ውስጥ ሰፍረው ነበር፤ የግመሎቻቸውም ብዛት በባሕር ዳርቻ እንዳለ አሸዋ ስፍር ቍጥር አልነበረውም።

13አንድ ሰው ያየውን ሕልም ለጓደኛው በሚነግርበት ጊዜ ጌዴዎን እዚያ ደረሰ። ያም ሰው፣ “በሕልሜ ክብ የሆነ አንድ የገብስ ቂጣ ከላይ ተንከባሎ በምድያማውያን ሰፈር ላይ ሲወርድ፣ ድንኳኑንም ሲመታው ከአመታቱም ኀይለኛነት የተነሣ ድንኳኑ ተገልብጦ ሲፈራርስ አየሁ” በማለት ይነግረው ነበር።

14ጓደኛውም መልሶ፣ “ይህ የእስራኤላዊው የኢዮአስ ልጅ የጌዴዎን ሰይፍ እንጂ ሌላ ነገር ሊሆን አይችልም፤ እነሆ፤ እግዚአብሔር ምድያማውያንንና ሰፈሩን በሙሉ በእጁ አሳልፎ ሰጥቶታልና” አለው።

15ጌዴዎንም ሕልሙንና ፍቺውን በሰማ ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰገደ፤ ከዚያም ወደ እስራኤላውያን ሰፈር ወጥቶ፣ “እግዚአብሔር የምድያማውያንን ሰፈር በእጃችሁ አሳልፎ ሰጥቷልና ተነሡ” አላቸው። 16ሦስቱን መቶ ሰዎች በሦስት ቡድን ከፍሎ፣ እያንዳንዱን ሰው ቀንደ መለከትና በውስጡ ችቦ ያለበት ባዶ ማሰሮ በእጁ እንዲይዝ አደረገ።

17ጌዴዎንም እንዲህ አላቸው፤ “እኔን ተመልከቱ፤ የማደርገውንም አድርጉ፤ በሰፈሩ ዳርቻ ስደርስ እኔ የማደርገውን አይታችሁ ልክ እንደዚያው አድርጉ። 18እኔና አብረውኝ ያሉት ሁሉ ቀንደ መለከቶቻችንን በምንነፋበት ጊዜ እናንተም በሰፈሩ ዙሪያ ሁሉ ቀንደ መለከቶቻችሁን እየነፋችሁ፣ ‘ለእግዚአብሔርና ለጌዴዎን’ ብላችሁ ጩኹ።”

19ዘቦቹ ተቀያይረው የእኩለ ሌሊቱን ጥበቃ በጀመሩበት ጊዜ፣ ጌዴዎንና አብረውት የነበሩት መቶ ሰዎች በሰፈሩ ዳርቻ ደረሱ፤ እነርሱም ቀንደ መለከቶቻቸውን ነፉ፤ የያዟቸውንም ማሰሮች ሰበሩ። 20በሦስት ቡድን የተከፈሉት ሰዎች ቀንደ መለከቶቻቸውን ነፉ፤ ማሰሮቻቸውንም ሰበሩ፤ ችቦዎቻቸውን በግራ እጆቻቸው፣ የሚነፏቸውንም ቀንደ መለከቶች በቀኝ እጆቻቸው ይዘው፣ “የእግዚአብሔርና የጌዴዎን ሰይፍ” በማለት ጮኹ። 21እያንዳንዱ ሰው በሰፈሩ ዙሪያ የተመደበበትን ቦታ እንደ ያዘም ምድያማውያኑ እየጮኹ ሸሹ።

22የሦስት መቶው ቀንደ መለከት ድምፅ እንደ ተሰማም እግዚአብሔር በሰፈሩ ውስጥ ያለው ሰው አንዱ በሌላው ላይ ሰይፉን እንዲመዝበት አደረገ፤ ሰራዊቱ በጽሬራ አቅጣጫ ወደ ቤት ሺጣ፣ ከዚያም ዐልፈው በጠባት አጠገብ እስካለው እስከ አቤላሞሖላ ድንበር ድረስ ሸሽተው ሄዱ። 23በንፍታሌም፣ በአሴርና በመላው የምናሴ ምድር የሚገኙ እስራኤላውያን ተጠርተው ወጡ፤ ምድያማውያንንም አሳደዱ። 24ጌዴዎንም በኤፍሬም ኰረብታማ አገር ለሚኖሩት ሁሉ፣ “በምድያማውያን ላይ ውረዱ፤ እስከ ቤትባራ ድረስ ያለውንም የዮርዳኖስ ወንዝ ቀድማችሁ ያዙ” አላቸው።

ስለዚህ የኤፍሬም ሰዎች ሁሉ ተጠርተው ወጡ፤ እስከ ቤትባራ ድረስ ያለውንም የዮርዳኖስን ወንዝ ያዙ። 25እንዲሁም ሔሬብና ዜብ የተባሉትን ሁለቱን የምድያም መሪዎች ያዙ። ሔሬብን በሔሬብ ዐለት አጠገብ፣ ዜብን ደግሞ በዜብ የወይን መጭመቂያ ላይ ገደሏቸው፤ ምድያማውያንንም አሳደዱ፤ የሔሬብንና የዜብን ራስ ቈርጠው ጌዴዎን ወዳለበት ወደ ዮርዳኖስ ይዘው መጡ።

Swedish Contemporary Bible

Domarboken 7:1-25

Gideon besegrar midjaniterna

1Tidigt nästa morgon slog Gideon, eller Jerubbaal som han nu också kallades, och hans armé läger vid Harodkällan. Midjaniternas läger låg norr om dem nere i dalen vid foten av Morehöjden.

2Då sa Herren till Gideon: ”Ni är alldeles för många! Jag kan inte låta er allesammans strida mot midjaniterna, för då kommer Israels folk att skryta och säga: ’Vi klarade vår räddning själva.’ 3Meddela folket att alla som är rädda och oroliga får lämna Gilboaberget och gå hem.” 22 000 man vände då hem igen och 10 000 blev kvar.

4”Det är fortfarande för många”, sa Herren till Gideon. ”För ner dem till källan, så ska jag göra ett urval åt dig. Den, om vilken jag säger till dig att han ska gå med dig, ska följa med och den, om vilken jag säger att han inte ska gå med dig, ska inte följa med.” 5Gideon samlade dem alltså nere vid vattnet och där sa Herren till honom: ”De som lapar i sig vattnet som en hund, ska du skilja från dem som lägger sig på knä för att dricka.” 6Det var bara trehundra man som lapade ur handen. Alla de övriga föll på knä och drack.

7”Jag ska rädda er med dessa trehundra som lapade vattnet ur sin hand,” sa Herren till Gideon. ”Skicka hem alla de andra!” 8När Gideon hade samlat ihop allas proviant och horn, skickade han hem de övriga israeliterna och behöll de trehundra. Midjaniternas läger låg nedanför honom på slätten.

9På natten sa Herren till Gideon: ”Bryt upp nu! Anfall lägret, för jag ska ge det i ditt våld. 10Men om du är rädd och tvekar, ska du först gå ner till deras läger med din tjänare Pura 11och lyssna till vad de säger om er. Du kommer att få mod att anfalla lägret.”

Gideon tog alltså med sig Pura och de gick fram till utkanten av lägret. 12Midjaniterna, amalekiterna och östlänningarna uppfyllde dalen som gräshoppor och det var lika omöjligt att räkna deras kameler som sanden på havsstranden. 13Gideon kom fram, just som en man höll på att berätta en dröm för sina kamrater.

”Jag hade en dröm”, sa han. ”Jag såg en kornbrödskaka som rullade in i midjaniternas läger. Den rullade fram mot vårt tält så att det slogs omkull och blev liggande.”

14”Din dröm kan bara betyda en sak”, sa hans kamrat, ”israeliten Gideons, Joashs sons, svärd. Gud har överlämnat midjaniterna och hela lägret åt honom.”

15När Gideon hörde om drömmen och dess uttydning, tillbad han Gud. Han återvände till Israels läger och ropade: ”Gör er genast i ordning, för Herren har gett midjaniternas läger i er hand!”

16Han delade upp de trehundra männen i tre grupper och gav varje man ett horn och en lerkruka med en fackla i. 17Sedan sa han till dem: ”När jag kommer till de första vakterna vid förposten, ska ni göra som jag gör. 18Så snart jag och männen i min grupp blåser i hornen, ska ni också blåsa i era horn från alla håll runt lägret och sedan ropa: ’För Herren och för Gideon!’ ”

19Gideon och hans hundra män nådde lägrets utkant strax efter vaktavlösningen vid midnatt.

De blåste i sina horn och slog sönder lerkrukorna de hade med sig. 20Alla tre grupperna gjorde likadant. De blåste i hornen och krossade krukorna. De tog facklorna med den vänstra handen och höll i högra handen hornen de stötte i och ropade: ”Svärd för Herren och för Gideon!”

21Sedan stod de där, var och en på sin plats runt lägret, medan hela lägret irrade omkring, skrek och flydde. 22När de blåste i de trehundra hornen, lät Herren dem börja slåss mot varandra överallt i hela lägret. De flydde ända bort till Bet Hashitta nära Serera och förbi Tabbat till trakten av Avel Mechola.

23Alla israeliterna samlades från Naftali, Asher och Manasse och de förföljde midjaniterna. 24Gideon skickade också ut budbärare över hela Efraims bergsbygd med order att dra ut mot midjaniterna och spärra övergångsställena vid Jordan ända upp till Bet Bara. Efraims män samlades och spärrade flodövergångarna ända till Bet Bara vid Jordan.

25Orev och Seev, midjaniternas två generaler blev tillfångatagna. Orev dödades vid den klippa som nu bär hans namn och Seev blev dödad vid det som numera kallas Seevs vinpress. Israeliterna fortsatte att förfölja midjaniterna och tog med sig Orevs och Seevs huvuden över Jordan och till Gideon.