መሳፍንት 7 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 7:1-25

ጌዴዎን ምድያማውያንን ድል አደረገ

1ይሩበኣል የተባለው ጌዴዎን፣ ከእርሱም ጋር የነበሩት ሰዎች ሁሉ በጧት ተነሥተው በሐሮድ ምንጭ አጠገብ ሰፈሩ። የምድያማውያንም ሰፈር እስራኤላውያን ከሰፈሩበት በስተ ሰሜን በኩል፣ በሞሬ ኰረብታ አጠገብ በሸለቆው ውስጥ ነበር። 2እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “ምድያማውያንን በእጃቸው አሳልፌ እንዳልሰጥ አብረውህ ያሉት ሰዎች በጣም ብዙ ናቸው፤ እስራኤላውያን የገዛ ኀይላቸው እንዳዳናቸው በመቍጠር እንዳይታበዩብኝ፣ 3‘ማንም የፈራ ቢኖር የገለዓድን ተራራ ትቶ ወደ መጣበት ይመለስ’ ብለህ ለሕዝቡ ዐውጅ።” ስለዚህ ሃያ ሁለቱ ሺሕ ሲመለሱ ዐሥሩ ሺሕ ብቻ ቀሩ።

4እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “አሁንም ሰዎቹ ብዙ ናቸው፤ ወደ ወንዝ ይዘሃቸው ውረድ፤ በዚያም እለይልሃለሁ። ‘ይህ ከአንተ ጋር ይሂድ’ የምለው፣ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ነገር ግን፣ ‘ይህ ከአንተ ጋር አይሂድ’ የምለው፣ ከአንተ ጋር አይሄድም።”

5ስለዚህ ጌዴዎን ሰዎቹን ወደ ወንዝ ይዟቸው ወረደ፤ እዚያም እግዚአብሔር፤ “ውሻ በምላሱ እየጨለፈ እንደሚጠጣ ሁሉ፣ በምላሳቸው የሚጠጡትን፣ በጕልበታቸው ተንበርክከው ከሚጠጡት ለይ” አለው። 6ሦስት መቶ ሰዎች ውሃውን በእጃቸው እያፈሱ ጠጡ፤ የቀሩት ሁሉ ግን ለመጠጣት በጕልበታቸው ተንበረከኩ።

7እግዚአብሔርም ጌዴዎንን፣ “ውሃውን በእጃቸው እያፈሱ በጠጡት ሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ፤ ምድያማውያንንም በእጃችሁ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፤ የቀሩት በሙሉ ወደየመጡበት ይመለሱ” አለው። 8ጌዴዎንም የቀሩትን እስራኤላውያን በሙሉ ወደ የድንኳናቸው እንዲመለሱ አደረገ፤ ሦስት መቶውን ግን አስቀራቸው፤ እነርሱም የሚመለሱትን ሰዎች ስንቅና መለከት ወሰዱ።

በዚህ ጊዜ የምድያማውያኑ ሰፈር ከእነርሱ በታች በሸለቋማው ውስጥ ነበር። 9በዚያች ሌሊት እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “ተነሥ፤ በሰፈሩም ላይ ውረድ፤ በእጅህ አሳልፌ ሰጥቼሃለሁና። 10አደጋ ለመጣል የምትፈራ ከሆነ ግን፣ ፉራ ከተባለው አገልጋይህ ጋር ወደ ሰፈሩ ውረድ፤ 11የሚሉትንም አድምጥ፤ ከዚያ በኋላ በሰፈሩ ላይ አደጋ ለመጣል ድፍረት ታገኛለህ።” ስለዚህም ጌዴዎን አገልጋዩን ፉራን አስከትሎ እስከ ሰፈሩ ዳርቻ ወረደ። 12ብዛታቸው እንደ አንበጣ መንጋ የሆነ ምድያማውያን፣ አማሌቃውያንና ሌሎችም የምሥራቅ ሕዝቦች በሸለቆው ውስጥ ሰፍረው ነበር፤ የግመሎቻቸውም ብዛት በባሕር ዳርቻ እንዳለ አሸዋ ስፍር ቍጥር አልነበረውም።

13አንድ ሰው ያየውን ሕልም ለጓደኛው በሚነግርበት ጊዜ ጌዴዎን እዚያ ደረሰ። ያም ሰው፣ “በሕልሜ ክብ የሆነ አንድ የገብስ ቂጣ ከላይ ተንከባሎ በምድያማውያን ሰፈር ላይ ሲወርድ፣ ድንኳኑንም ሲመታው ከአመታቱም ኀይለኛነት የተነሣ ድንኳኑ ተገልብጦ ሲፈራርስ አየሁ” በማለት ይነግረው ነበር።

14ጓደኛውም መልሶ፣ “ይህ የእስራኤላዊው የኢዮአስ ልጅ የጌዴዎን ሰይፍ እንጂ ሌላ ነገር ሊሆን አይችልም፤ እነሆ፤ እግዚአብሔር ምድያማውያንንና ሰፈሩን በሙሉ በእጁ አሳልፎ ሰጥቶታልና” አለው።

15ጌዴዎንም ሕልሙንና ፍቺውን በሰማ ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰገደ፤ ከዚያም ወደ እስራኤላውያን ሰፈር ወጥቶ፣ “እግዚአብሔር የምድያማውያንን ሰፈር በእጃችሁ አሳልፎ ሰጥቷልና ተነሡ” አላቸው። 16ሦስቱን መቶ ሰዎች በሦስት ቡድን ከፍሎ፣ እያንዳንዱን ሰው ቀንደ መለከትና በውስጡ ችቦ ያለበት ባዶ ማሰሮ በእጁ እንዲይዝ አደረገ።

17ጌዴዎንም እንዲህ አላቸው፤ “እኔን ተመልከቱ፤ የማደርገውንም አድርጉ፤ በሰፈሩ ዳርቻ ስደርስ እኔ የማደርገውን አይታችሁ ልክ እንደዚያው አድርጉ። 18እኔና አብረውኝ ያሉት ሁሉ ቀንደ መለከቶቻችንን በምንነፋበት ጊዜ እናንተም በሰፈሩ ዙሪያ ሁሉ ቀንደ መለከቶቻችሁን እየነፋችሁ፣ ‘ለእግዚአብሔርና ለጌዴዎን’ ብላችሁ ጩኹ።”

19ዘቦቹ ተቀያይረው የእኩለ ሌሊቱን ጥበቃ በጀመሩበት ጊዜ፣ ጌዴዎንና አብረውት የነበሩት መቶ ሰዎች በሰፈሩ ዳርቻ ደረሱ፤ እነርሱም ቀንደ መለከቶቻቸውን ነፉ፤ የያዟቸውንም ማሰሮች ሰበሩ። 20በሦስት ቡድን የተከፈሉት ሰዎች ቀንደ መለከቶቻቸውን ነፉ፤ ማሰሮቻቸውንም ሰበሩ፤ ችቦዎቻቸውን በግራ እጆቻቸው፣ የሚነፏቸውንም ቀንደ መለከቶች በቀኝ እጆቻቸው ይዘው፣ “የእግዚአብሔርና የጌዴዎን ሰይፍ” በማለት ጮኹ። 21እያንዳንዱ ሰው በሰፈሩ ዙሪያ የተመደበበትን ቦታ እንደ ያዘም ምድያማውያኑ እየጮኹ ሸሹ።

22የሦስት መቶው ቀንደ መለከት ድምፅ እንደ ተሰማም እግዚአብሔር በሰፈሩ ውስጥ ያለው ሰው አንዱ በሌላው ላይ ሰይፉን እንዲመዝበት አደረገ፤ ሰራዊቱ በጽሬራ አቅጣጫ ወደ ቤት ሺጣ፣ ከዚያም ዐልፈው በጠባት አጠገብ እስካለው እስከ አቤላሞሖላ ድንበር ድረስ ሸሽተው ሄዱ። 23በንፍታሌም፣ በአሴርና በመላው የምናሴ ምድር የሚገኙ እስራኤላውያን ተጠርተው ወጡ፤ ምድያማውያንንም አሳደዱ። 24ጌዴዎንም በኤፍሬም ኰረብታማ አገር ለሚኖሩት ሁሉ፣ “በምድያማውያን ላይ ውረዱ፤ እስከ ቤትባራ ድረስ ያለውንም የዮርዳኖስ ወንዝ ቀድማችሁ ያዙ” አላቸው።

ስለዚህ የኤፍሬም ሰዎች ሁሉ ተጠርተው ወጡ፤ እስከ ቤትባራ ድረስ ያለውንም የዮርዳኖስን ወንዝ ያዙ። 25እንዲሁም ሔሬብና ዜብ የተባሉትን ሁለቱን የምድያም መሪዎች ያዙ። ሔሬብን በሔሬብ ዐለት አጠገብ፣ ዜብን ደግሞ በዜብ የወይን መጭመቂያ ላይ ገደሏቸው፤ ምድያማውያንንም አሳደዱ፤ የሔሬብንና የዜብን ራስ ቈርጠው ጌዴዎን ወዳለበት ወደ ዮርዳኖስ ይዘው መጡ።

New International Reader’s Version

Judges 7:1-25

Gideon Wins the Battle Over the Midianites

1Early in the morning Jerub-Baal and all his men camped at the spring of Harod. Jerub-Baal was another name for Gideon. The camp of Midian was north of Gideon’s camp. It was in the valley near the hill of Moreh. 2The Lord said to Gideon, “I want to hand Midian over to you. But you have too many men for me to do that. Then Israel might brag, ‘My own strength has saved me.’ 3So here is what I want you to announce to the army. Tell them, ‘Those who tremble with fear can turn back. They can leave Mount Gilead.’ ” So 22,000 men left. But 10,000 remained.

4The Lord said to Gideon, “There are still too many men. So take them down to the water. There I will reduce the number of them for you. If I say, ‘This one will go with you,’ he will go. But if I say, ‘That one will not go with you,’ he will not go.”

5So Gideon took the men down to the water. There the Lord said to him, “Some men will drink the way dogs do. They will lap up the water with their tongues. Separate them from those who get down on their knees to drink.” 6Three hundred men brought up the water to their mouths with their hands. And they lapped it up the way dogs do. All the rest got down on their knees to drink.

7The Lord spoke to Gideon. He said, “With the help of the 300 men who lapped up the water I will save you. I will hand the Midianites over to you. Let all the other men go home.” 8So Gideon sent those Israelites home. But he kept the 300 men. They took over the supplies and trumpets the others had left.

The Midianites had set up their camp in the valley below where Gideon was. 9During that night the Lord said to Gideon, “Get up. Go down against the camp. I am going to hand it over to you. 10But what if you are afraid to attack? Then go down to the camp with your servant Purah. 11Listen to what they are saying. After that, you will not be afraid to attack the camp.” So Gideon and his servant Purah went down to the edge of the camp. 12The Midianites had set up their camp in the valley. So had the Amalekites and all the other tribes from the east. There were so many of them that they looked like huge numbers of locusts. Like the grains of sand on the seashore, their camels couldn’t be counted.

13Gideon arrived just as a man was telling a friend about his dream. “I had a dream,” he was saying. “A round loaf of barley bread came rolling into the camp of Midian. It hit a tent with great force. The tent turned over and fell down flat.”

14His friend replied, “That can only be the sword of Gideon, the son of Joash. Gideon is from Israel. God has handed the Midianites over to him. He has given him the whole camp.”

15Gideon heard the man explain what the dream meant. Then Gideon bowed down and worshiped. He returned to the camp of Israel. He called out, “Get up! The Lord has handed the Midianites over to you.” 16Gideon separated the 300 men into three fighting groups. He put a trumpet and an empty jar into the hands of each man. And he put a torch inside each jar.

17“Watch me,” he told them. “Do what I do. I’ll go to the edge of the enemy camp. Then do exactly as I do. 18I and everyone with me will blow our trumpets. Then blow your trumpets from your positions all around the camp. And shout the battle cry, ‘For the Lord and for Gideon!’ ”

19Gideon and the 100 men with him reached the edge of the enemy camp. It was about ten o’clock at night. It was just after the guard had been changed. Gideon and his men blew their trumpets. They broke the jars that were in their hands. 20The three fighting groups blew their trumpets. They smashed their jars. They held their torches in their left hands. They held in their right hands the trumpets they were going to blow. Then they shouted the battle cry, “A sword for the Lord and for Gideon!” 21Each man stayed in his position around the camp. But all the Midianites ran away in fear. They were crying out as they ran.

22When the 300 trumpets were blown, the Lord caused all the men in the enemy camp to start fighting one another. They attacked one another with their swords. The army ran away to Beth Shittah toward Zererah. They ran all the way to the border of Abel Meholah near Tabbath. 23Israelites from the tribes of Naphtali, Asher and all of Manasseh were called out. They chased the Midianites. 24Gideon sent messengers through the entire hill country of Ephraim. They said, “Come on down against the Midianites. Take control of the waters of the Jordan River before they get there. Do it all the way to Beth Barah.”

So all the men of Ephraim were called out. They took control of the waters of the Jordan all the way to Beth Barah. 25They also captured Oreb and Zeeb. Those men were two of the Midianite leaders. The men of Ephraim killed Oreb at the rock of Oreb. They killed Zeeb at the winepress of Zeeb. They chased the Midianites. And they brought the heads of Oreb and Zeeb to Gideon. He was by the Jordan River.