መሳፍንት 5 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 5:1-31

የዲቦራ መዝሙር

1በዚያን ዕለት ዲቦራና የአቢኒኤም ልጅ ባርቅ ይህን ቅኔ ተቀኙ፤

2“በእስራኤል ያሉ መሳፍንት ሲመሩ፣

ሕዝቡም በፈቃዱ ራሱን ሲያስገዛ፣

እግዚአብሔርን አመስግኑ።

3“እናንት ነገሥታት ይህን ስሙ፤

ገዦችም አድምጡ፤

ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ፤ ደግሜም

ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሴይር በወጣህ ጊዜ፣

ከኤዶም ምድርም በተነሣህ ጊዜ፣

ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ሰማያትም ዝናብ አዘነቡ፤

ደመናዎችም ውሃ አፈሰሱ።

5ተራሮች በሲና አምላክ በእግዚአብሔር ፊት፣

በእስራኤልም አምላክ በእግዚአብሔር ፊት ተናወጡ።

6“በዓናት ልጅ በሰሜጋር ዘመን፣

በኢያዔል ጊዜ መንገዶች ባድማ ሆኑ፤

ተጓዦችም በጠመዝማዛ መንገድ ሄዱ።

7ለእስራኤል እናት ሆኜ

እኔ ዲቦራ እስክነሣ ድረስ

በእስራኤል ያለው የከተማ ኑሮ አበቃለት፤

8አዳዲስ አማልክትን በተከተሉ ጊዜ፣

ጦርነት እስከ ከተማው በር መጣ፤

ጋሻም ሆነ ጦር፣

በአርባ ሺሕ እስራኤላውያን መካከል አልተገኘም።

9ልቤ ከእስራኤል መሳፍንት፣

ፈቃደኞችም ከሆኑ ሰዎች ጋር ነው፤

እግዚአብሔር ይመስገን።

10“እናንት በነጫጭ አህዮች የምትጋልቡ፣

በባለ ግላስ ኮርቻ ላይ የምትቀመጡ፣

በመንገድ ላይ የምትጓዙ፣

በውሃ ምንጮች ዙሪያ ያለውን፣

11የዝማሬ ድምፅ5፥11 ወይም ቀስተኞች ተብሎ ሊተረጐም ይችላል። ስሙ።

ይህም የእግዚአብሔር የጽድቅ ሥራ፣

ጦረኞቹም በእስራኤል ያደረጉትን ያስታውሳል።

“ከዚያም የእግዚአብሔር ሕዝቦች፣

ወደ ከተማዪቱ5፥11 ወይም ወደ መንደሮቹ ተብሎ መተርጐም ይቻላል። በሮች ወረዱ።

12‘ዲቦራ ሆይ፤ ንቂ፤ ንቂ፤

ንቂ፤ ንቂ፤ ቅኔም ተቀኚ፤

የአቢኒኤል ልጅ ባራቅ ሆይ፤ ተነሣ፤

ምርኮኞችህንም ማርከህ ውሰድ’ አሉ።

13“የቀሩትም ሰዎች፣

ወደ መኳንንቱ ወረዱ፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ እንደ ኀያል ጦረኛ ወደ እኔ መጣ።

14መሠረታቸው ከአማሌቅ የሆነ አንዳንዶች

ከኤፍሬም መጡ፤ ብንያም አንተን ከተከተሉ ሰዎች ጋር ነበር፤

የጦር አዛዦች ከማኪር፣

የሥልጣን በትር የያዙም ከዛብሎን ወረዱ።

15የይሳኮር መሳፍንት ከዲቦራ ጋር ነበሩ፤

ይሳኮርም ራሱ ወደ ሸለቆው ከኋላው

በመከተል፣ ከባርቅ ጋር ነበረ።

በሮቤል አውራጃዎች፣ ብዙ የልብ

ምርምር ነበር።

16በበጎች ጕረኖ5፥16 ወይም በኮርቻ ላይ ተብሎ መተርጐም ይቻላል። መካከል ለምን ተቀመጥህ?

መንጎችን የሚጠራውን ፉጨት ለመስማት ነውን?

በሮቤል አውራጃዎች፣ ብዙ የልብ

ምርምር ነበር።

17ገለዓድ ከዮርዳኖስ ማዶ ተቀመጠ፤

ዳን ለምን በመርከብ ውስጥ ዘገየ?

አሴር በጠረፍ ቀረ፤

በባሕሩ ዳርቻም ተቀመጠ።

18የዛብሎን ሰዎች ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጡ፤

የንፍታሌም ሰዎች እንደዚሁ በምድሪቱ ኰረብታዎች አደረጉ።

19“ነገሥታት መጡ፤ ተዋጉም፤

የከነዓን ነገሥታት፣ በመጊዶ ውሆች

አጠገብ በታዕናክ ተዋጉ፤

ብርም ሆነ ሌላ ምርኮ ተሸክመው አልሄዱም።

20ከሰማያት ከዋክብት ተዋጉ፤

በአካሄዳቸውም ሲሣራን ገጠሙት።

21ጥንታዊው ወንዝ፣ የቂሶን ወንዝ፣

የቂሶን ወንዝ ጠርጎ ወሰዳቸው፤

ነፍሴ ሆይ፤ በኀይል ገሥግሺ

22የፈረሶች ኰቴ ድምፅ በኀይል ተሰማ፤

ጋለቡ፤ በኀይልም ፈጥነው ጋለቡ።

23የእግዚአብሔር መልአክ፣ ‘ሜሮዝን ርገሙ፤’

‘ሕዝቧንም አብራችሁ ርገሙ፤

ከኀያላን ሰልፍ እግዚአብሔርን ለመርዳት፣

በእግዚአብሔርም ጐን ለመቆም አልመጡምና’ አለ።

24“የቄናዊው የሔቤር ሚስት ኢያዔል፣

ከሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን፤

በድንኳን ከሚኖሩ ሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን።

25ውሃ ለመነ፤ ወተት ሰጠችው፤

ለመኳንንት በሚገባ ዕቃ፣ እርጎ አቀረበችለት።

26እጇ ካስማ ያዘ፤

ቀኝ እጇም የሠራተኛ መዶሻ ጨበጠ፤

ሲሣራን መታችው፤ ራሱንም ተረከከችው፤

ክፉኛ ወጋችው፤ ጆሮ ግንዱን በሳችው።

27በእግሯ ሥር ተደፋ፤ ወደቀ፤

በዚያም ተዘረረ፤ በእግሯ ሥር ተደፋ፤

ወደቀ፤ በተደፋበት በዚያ ወደቀ፤

ሞተም።

28“የሲሣራ እናት በመስኮት ተመለከተች፤

በዐይነ ርግቡ ቀዳዳም ጮኻ ተጣራች፤

‘ለምን ሠረገላው ሳይመጣ ዘገየ?

የሠረገሎቹስ ድምፅ ለምን ጠፋ?’ አለች።

29ብልኅተኞች ወይዛዝርቷም መለሱላት፤

እርሷ ግን ለራሷ እንዲህ አለች፤

30‘ምርኮ አግኝተው እየተከፋፈሉ፣

እያንዳንዱም ሰው አንዲት ወይም ሁለት ልጃገረዶች እየወሰደ አይደለምን?

ይህ ሁሉ ምርኮ፣ በቀለም ያጌጡ ልብሶች

ለሲሣራ ደርሰውት፣

በጌጣጌጥ የተጠለፉ ልብሶች ለዐንገቴ

ይዞልኝ እየመጣ አይደለምን?’

31“እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ ሁሉ ይጥፉ፤

አንተን የሚወድዱህ ግን፣ የንጋት ፀሓይ

በኀይል እንደሚወጣ እንዲያ ይሁኑ።”

ከዚያም በኋላ ምድሪቱ ለአርባ ዓመት ሰላም አገኘች።

Swedish Contemporary Bible

Domarboken 5:1-31

Deboras och Baraks sång

1Debora och Barak, Avinoams son, sjöng den dagen denna sång:

2”När Israels furstar visar vägen

och folket villigt offrar sig,

prisa Herrens namn!

3Hör, ni kungar, lyssna ni härskare!

Jag ska sjunga inför Herren

och spela inför Israels Gud.

4Du, Herre, ledde oss ut ur Seir

och fram över Edoms slätter,

marken skakade, från himlen strömmade regnet ner

och vatten strömmar ur molnen.

5Bergen skälvde inför Herren,

den Väldige på Sinai, Herren, Israels Gud.

6På Shamgars, Anats sons, och Jaels tid

låg vägarna öde.

Vandrarna valde vindlande stigar.

7Israel saknade ledare,

tills Debora trädde fram,

tills hon blev en mor för Israel.

8När Israel valde nya gudar

kom striden fram till stadsportarna.5:8 Grundtexten är mycket svårtolkad och innebörden osäker.

Varken sköld eller spjut fanns.

Israels 40 000 saknade vapen.

9Mitt hjärta vänder sig till Israels ledare

och till alla som villigt följer dem!

Prisa Herren!

10Prisa honom, alla ni som rider på vita åsnor,

och sitter på dyrbara mattor

och alla ni som går till fots!

11Sångarna sjunger lovsång vid brunnen,

sången om Herrens rättfärdiga gärningar,

hur han räddade Israel

med sina krigare.

Herrens folk tågade in

genom portarna.

12Vakna, Debora,

vakna och sjung!

Stå upp, Barak!

Du, Avinoams son, för bort dina fångar!

13Männen som fanns kvar

marscherade ner till de tappra.

Herrens folk kom till mig

med sina mäktiga.

14Män kom från Efraim,

med rotfäste i Amalek,

och Benjamin,

som följde efter dig med dina skaror.

Från Makir kom furstar

och från Sebulon män med ledarstav.

15Isaskars furstar följde Debora

och Barak ner i dalen.

Men Rubens stam

höll grundliga rådslag.

16Varför satt du hemma bland fållorna5:16 Eller: vid lägerelden. Eller: mellan sadelväskorna.

och lyssnade på herdeflöjter?

Rubens stam höll grundliga rådslag.

17Gilead stannade på andra sidan Jordan.

Varför blev Dan kvar vid sina fartyg?

Och Asher blev kvar vid stranden

i lugn och ro.

18Men Sebulons och Naftalis stammar

riskerade livet på stridsfältets höjder.

19Kanaans kungar

stred vid Tanak

nära Megiddos källor

men de blev utan silver och utan byte.

20Till och med himlens stjärnor

stred mot Sisera.

21Den brusande floden Kishon,

urtidsfloden

förde bort dem.

Dra vidare, var stark min själ!

22Hör hovtrampet från fiendens hingstar!

Se hur stridshästarna jagar fram!

23Men Herrens ängel befallde att förbanna Meros.

’Förbanna dess inbyggare’, sa han.

’De kom inte till Herrens hjälp,

till Herrens och hjältarnas hjälp.’

24Välsignad bland kvinnorna ska Jael vara,

keniten Hevers hustru,

ja, välsignad mer än andra kvinnor som bor i tält.

25Han bad om vatten, men hon gav honom mjölk

i en dyrbar skål,

hon bjöd honom på tjockmjölk.

26Hennes hand grep efter tältpluggen,

hennes högra hand efter hammaren,

och med snickarens hammare

slog hon honom i huvudet,

genomborrade Siseras tinning.

27Han sjönk ner vid hennes fötter,

låg stilla och var död.

28Siseras mor såg väntande ut genom fönstret

och hon ropade:

’Varför dröjer hans vagn så länge?

Var är klappret av hovar?’

29Då svarar hennes hovdam,

och själv ger hon samma svar:

30’Bytet de skiftar är stort,

en flicka åt var man eller två,

dyrbara mantlar åt Sisera

och vackra tyger,

brokiga dukar, en eller två åt den som tog byte.

Allt detta som byte!’

31Herre, så ska alla dina fiender förgås,

men de som älskar Herren ska stråla av kraft

som den uppgående solen!”

Därefter fick landet fred i fyrtio år.