መሳፍንት 5 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 5:1-31

የዲቦራ መዝሙር

1በዚያን ዕለት ዲቦራና የአቢኒኤም ልጅ ባርቅ ይህን ቅኔ ተቀኙ፤

2“በእስራኤል ያሉ መሳፍንት ሲመሩ፣

ሕዝቡም በፈቃዱ ራሱን ሲያስገዛ፣

እግዚአብሔርን አመስግኑ።

3“እናንት ነገሥታት ይህን ስሙ፤

ገዦችም አድምጡ፤

ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ፤ ደግሜም

ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሴይር በወጣህ ጊዜ፣

ከኤዶም ምድርም በተነሣህ ጊዜ፣

ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ሰማያትም ዝናብ አዘነቡ፤

ደመናዎችም ውሃ አፈሰሱ።

5ተራሮች በሲና አምላክ በእግዚአብሔር ፊት፣

በእስራኤልም አምላክ በእግዚአብሔር ፊት ተናወጡ።

6“በዓናት ልጅ በሰሜጋር ዘመን፣

በኢያዔል ጊዜ መንገዶች ባድማ ሆኑ፤

ተጓዦችም በጠመዝማዛ መንገድ ሄዱ።

7ለእስራኤል እናት ሆኜ

እኔ ዲቦራ እስክነሣ ድረስ

በእስራኤል ያለው የከተማ ኑሮ አበቃለት፤

8አዳዲስ አማልክትን በተከተሉ ጊዜ፣

ጦርነት እስከ ከተማው በር መጣ፤

ጋሻም ሆነ ጦር፣

በአርባ ሺሕ እስራኤላውያን መካከል አልተገኘም።

9ልቤ ከእስራኤል መሳፍንት፣

ፈቃደኞችም ከሆኑ ሰዎች ጋር ነው፤

እግዚአብሔር ይመስገን።

10“እናንት በነጫጭ አህዮች የምትጋልቡ፣

በባለ ግላስ ኮርቻ ላይ የምትቀመጡ፣

በመንገድ ላይ የምትጓዙ፣

በውሃ ምንጮች ዙሪያ ያለውን፣

11የዝማሬ ድምፅ5፥11 ወይም ቀስተኞች ተብሎ ሊተረጐም ይችላል። ስሙ።

ይህም የእግዚአብሔር የጽድቅ ሥራ፣

ጦረኞቹም በእስራኤል ያደረጉትን ያስታውሳል።

“ከዚያም የእግዚአብሔር ሕዝቦች፣

ወደ ከተማዪቱ5፥11 ወይም ወደ መንደሮቹ ተብሎ መተርጐም ይቻላል። በሮች ወረዱ።

12‘ዲቦራ ሆይ፤ ንቂ፤ ንቂ፤

ንቂ፤ ንቂ፤ ቅኔም ተቀኚ፤

የአቢኒኤል ልጅ ባራቅ ሆይ፤ ተነሣ፤

ምርኮኞችህንም ማርከህ ውሰድ’ አሉ።

13“የቀሩትም ሰዎች፣

ወደ መኳንንቱ ወረዱ፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ እንደ ኀያል ጦረኛ ወደ እኔ መጣ።

14መሠረታቸው ከአማሌቅ የሆነ አንዳንዶች

ከኤፍሬም መጡ፤ ብንያም አንተን ከተከተሉ ሰዎች ጋር ነበር፤

የጦር አዛዦች ከማኪር፣

የሥልጣን በትር የያዙም ከዛብሎን ወረዱ።

15የይሳኮር መሳፍንት ከዲቦራ ጋር ነበሩ፤

ይሳኮርም ራሱ ወደ ሸለቆው ከኋላው

በመከተል፣ ከባርቅ ጋር ነበረ።

በሮቤል አውራጃዎች፣ ብዙ የልብ

ምርምር ነበር።

16በበጎች ጕረኖ5፥16 ወይም በኮርቻ ላይ ተብሎ መተርጐም ይቻላል። መካከል ለምን ተቀመጥህ?

መንጎችን የሚጠራውን ፉጨት ለመስማት ነውን?

በሮቤል አውራጃዎች፣ ብዙ የልብ

ምርምር ነበር።

17ገለዓድ ከዮርዳኖስ ማዶ ተቀመጠ፤

ዳን ለምን በመርከብ ውስጥ ዘገየ?

አሴር በጠረፍ ቀረ፤

በባሕሩ ዳርቻም ተቀመጠ።

18የዛብሎን ሰዎች ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጡ፤

የንፍታሌም ሰዎች እንደዚሁ በምድሪቱ ኰረብታዎች አደረጉ።

19“ነገሥታት መጡ፤ ተዋጉም፤

የከነዓን ነገሥታት፣ በመጊዶ ውሆች

አጠገብ በታዕናክ ተዋጉ፤

ብርም ሆነ ሌላ ምርኮ ተሸክመው አልሄዱም።

20ከሰማያት ከዋክብት ተዋጉ፤

በአካሄዳቸውም ሲሣራን ገጠሙት።

21ጥንታዊው ወንዝ፣ የቂሶን ወንዝ፣

የቂሶን ወንዝ ጠርጎ ወሰዳቸው፤

ነፍሴ ሆይ፤ በኀይል ገሥግሺ

22የፈረሶች ኰቴ ድምፅ በኀይል ተሰማ፤

ጋለቡ፤ በኀይልም ፈጥነው ጋለቡ።

23የእግዚአብሔር መልአክ፣ ‘ሜሮዝን ርገሙ፤’

‘ሕዝቧንም አብራችሁ ርገሙ፤

ከኀያላን ሰልፍ እግዚአብሔርን ለመርዳት፣

በእግዚአብሔርም ጐን ለመቆም አልመጡምና’ አለ።

24“የቄናዊው የሔቤር ሚስት ኢያዔል፣

ከሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን፤

በድንኳን ከሚኖሩ ሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን።

25ውሃ ለመነ፤ ወተት ሰጠችው፤

ለመኳንንት በሚገባ ዕቃ፣ እርጎ አቀረበችለት።

26እጇ ካስማ ያዘ፤

ቀኝ እጇም የሠራተኛ መዶሻ ጨበጠ፤

ሲሣራን መታችው፤ ራሱንም ተረከከችው፤

ክፉኛ ወጋችው፤ ጆሮ ግንዱን በሳችው።

27በእግሯ ሥር ተደፋ፤ ወደቀ፤

በዚያም ተዘረረ፤ በእግሯ ሥር ተደፋ፤

ወደቀ፤ በተደፋበት በዚያ ወደቀ፤

ሞተም።

28“የሲሣራ እናት በመስኮት ተመለከተች፤

በዐይነ ርግቡ ቀዳዳም ጮኻ ተጣራች፤

‘ለምን ሠረገላው ሳይመጣ ዘገየ?

የሠረገሎቹስ ድምፅ ለምን ጠፋ?’ አለች።

29ብልኅተኞች ወይዛዝርቷም መለሱላት፤

እርሷ ግን ለራሷ እንዲህ አለች፤

30‘ምርኮ አግኝተው እየተከፋፈሉ፣

እያንዳንዱም ሰው አንዲት ወይም ሁለት ልጃገረዶች እየወሰደ አይደለምን?

ይህ ሁሉ ምርኮ፣ በቀለም ያጌጡ ልብሶች

ለሲሣራ ደርሰውት፣

በጌጣጌጥ የተጠለፉ ልብሶች ለዐንገቴ

ይዞልኝ እየመጣ አይደለምን?’

31“እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ ሁሉ ይጥፉ፤

አንተን የሚወድዱህ ግን፣ የንጋት ፀሓይ

በኀይል እንደሚወጣ እንዲያ ይሁኑ።”

ከዚያም በኋላ ምድሪቱ ለአርባ ዓመት ሰላም አገኘች።

Het Boek

Richteren 5:1-31

Het lied van Debora en Barak

1Toen zongen Debora en Barak, de zoon van Abinoam, het volgende lied op de geweldige overwinning:

2‘Prijs de Here! Israëls bevelhebbers namen de leiding en het volk volgde vrijwillig!

3Luister, koningen en vorsten, want ik zal zingen voor de Here, psalmen zingen voor de God van Israël.

4Here, toen U uit Seïr trok, uit de velden van Edom, beefde de aarde en stroomde de regen uit de hemel.

5De bergen wankelden voor de Here, de God van Israël, ja, óók de berg Sinaï.

6In de dagen van Samgar, de zoon van Anath, en in de dagen van Jaël lagen de hoofdwegen verlaten. Reizigers gebruikten de smalle, kronkelende zijpaden.

7Er waren geen leiders in Israël, totdat ik, Debora, opstond als een moeder voor Israël.

8Als Israël nieuwe goden uitkoos, stond de vijand voor haar poorten. Maar bij de veertigduizend soldaten van Israël was geen schild of speer te vinden!

9Ik verheug mij over Israëls leiders, die zich zo vrijwillig aanboden. Prijs de Here voor zulke mannen!

10Maak het overal bekend, rijken die op ezelinnen met zachte zadels rijden en armen die te voet over de wegen moeten gaan.

11Laten de muzikanten zich bij de dorpsbron verzamelen om de overwinningen van de Here te bezingen en te zingen van de overwinning die de leiders van Israël hebben behaald terwijl het volk van de Here door de poorten marcheerde.

12Word wakker, word wakker, Debora, en zing een lied! Vooruit, Barak! Voer uw krijgsgevangenen weg, zoon van Abinoam!

13De ware helden daalden de berg Tabor af. Het volk van de Here rukte op tegen een grote overmacht.

14Bij Israëls leger sloten zich Amalekieten uit Efraïm aan, gevolgd door mannen uit Benjamin. Er kwamen ook leiders uit Machir bij en legeraanvoerders uit Zebulon.

15De vorsten van Issachar marcheerden in de gelederen mee, samen met Debora en Barak. Zij stormden het dal in, maar de stam Ruben ging niet mee.

16Waarom bleef u thuis zitten bij de veestallen, luisterend naar het fluitspel van de herders? Ja, de stam Ruben kon maar niet tot een besluit komen.

17Waarom bleef Gilead rustig aan de overkant van de Jordaan zitten? Waarom bleef Dan bij zijn schepen? En waarom bleef Aser aan de zeekust zitten en verliet zijn havens niet?

18Maar Zebulon en Naftali uit de hoogvlakten, dat zijn stammen die hun leven gewaagd hebben.

19De koningen van Kanaän rukten op naar Taänach en vochten daar bij de rivieren bij Megiddo. Maar geen stukje zilver viel als buit in hun handen!

20Vanuit hun baan langs de hemel vochten de sterren tegen Sisera.

21Door het geweld van de beek Kison werd de vijand meegesleurd.—Verder moet ik, onverschrokken!

22Hoor het dreunen van de paardenhoeven van de vijand! Hoor ze eens galopperen!

23Maar de Engel van de Here zei: vervloekt zijn de burgers van de stad Meroz, omdat zij de Here niet hebben geholpen in de strijd tegen de vijanden.

24Maar Jaël, de vrouw van de Keniet Eber, zij geprezen boven alle vrouwen die in tenten wonen.

25Hij vroeg haar om water en zij gaf hem melk, zij bracht hem room in een prachtige kom.

26Toen pakte zij een tentharing en een timmermanshamer en hamerde op Sisera, doornagelde zijn hoofd, verbrijzelde en doorboorde zijn slapen.

27Voor haar voeten kromp hij ineen, viel neer en bleef liggen. Ja, hij kromp ineen en bleef ter plekke dood liggen.

28Siseraʼs moeder keek uit het raam en riep luid: “Waarom zie ik zijn strijdwagen nog steeds niet komen? Waar blijft het ratelende geluid van zijn wagens?”

29Maar enkele verstandige hofdames—en ook zijzelf—gaven ten antwoord:

30“Er is natuurlijk veel buit te verdelen. Dat kost tijd. Iedere man krijgt een paar meisjes, en Sisera zal prachtige geborduurde kleren buitmaken en talrijke geschenken voor mij meenemen.”

31Och, Here, laten al uw vijanden net als Sisera omkomen! Maar zij die U liefhebben, zullen krachtig stralen als de opgaande zon.’

Daarna heersten er veertig jaar rust en vrede in het land.