ለብንያማውያን ሚስት ስለ ማግኘት
1እስራኤላውያን በምጽጳ፣ “ከእኛ አንድም ሰው ሴት ልጁን በጋብቻ ለብንያማውያን መዳር የለበትም” በማለት ተማምለው ነበር።
2ሕዝቡ ወደ ቤቴል21፥2 ወይም ወደ እግዚአብሔር ቤት ተብሎ መተርጐም ይቻላል። ሄደው በዚያም እስከ ማታ ድረስ በእግዚአብሔር ፊት ተቀመጡ፤ ድምፃቸውንም ከፍ በማድረግ አምርረው አለቀሱ፤ 3እንዲህም አሉ፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ ለምን በእስራኤል ላይ ሆነ? ዛሬ ከእስራኤል አንድ ነገድ እንዴት ይታጣ?”
4በማግስቱም ጧት ሕዝቡ መሠዊያ ሠሩ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕት21፥4 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። አቀረቡ።
5በምጽጳ፣ በእግዚአብሔር ጉባኤ ፊት ያልተገኘ ማንኛውም ሰው መገደል አለበት ብለው እስራኤላውያን ተማምለው ስለ ነበር፣ “ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ሳይወጣ የቀረ ማን አለ?” ሲሉ ጠየቁ።
6በዚህ ጊዜ እስራኤላውያን ስለ ወንድሞቻቸው ስለ ብንያማውያን በማዘን እንዲህ አሉ፤ “ዛሬ ከእስራኤል ነገዶች አንዱ ታጥቷል፤ 7ሴቶች ልጆቻችንን ለእነዚህ ብንያማውያን በጋብቻ ላንሰጥ በእግዚአብሔር ስለ ማልን ለተረፉት እንዴት ሚስት ልናገኝላቸው እንችላለን?” 8ከዚያም፣ “ከእስራኤል ነገዶች ምጽጳ ላይ በእግዚአብሔር ጉባኤ ፊት ሳይወጣ የቀረ ማን ነው” ሲሉ ጠየቁ፤ ታዲያ ከኢያቢስ ገለዓድ አንድም ሰው ለጉባኤው ወደ ሰፈሩ አለመምጣቱን ተረዱ፤ 9ሕዝቡን ሲቈጥሩም ከኢያቢስ ገለዓድ ሰዎች አንድም ሰው አልነበረምና።
10ስለዚህ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ተዋጊዎች ወደ ኢያቢስ ገለዓድ ሄደው በእዚያ የሚኖሩትን በሙሉ ሴቶቹንና ሕፃናቱን ጭምር በሰይፍ እንዲፈጇቸው ጉባኤው መመሪያ ሰጥቶ ላካቸው። 11እነርሱም፣ “እንግዲህ የምታደርጉት ይህ ነው፤ ወንዱን በሙሉ እንዲሁም ድንግል ያልሆኑትን ሴቶች ሁሉ ግደሉ” አሏቸው። 12በኢያቢስ ገለዓድ ከሚኖረው ሕዝብ መካከል ወንድ ያልደረሰባቸው አራት መቶ ደናግል አገኙ፤ በከነዓን ምድር በሴሎ ወደሚገኘውም ሰፈር አመጧቸው።
13ከዚያም ጉባኤው በሙሉ በሬሞን ዐለት ወዳሉት ብንያማውያን የሰላም ጥሪ አስተላለፈ። 14ስለዚህ በዚህን ጊዜ ብንያማውያን ተመለሱ፤ ከመገደል የተረፉትንም የኢያቢስ ገለዓድ ሴቶች ሰጧቸው፤ ይሁን እንጂ የሴቶቹ ቍጥር ለሁሉም የሚበቃ አልነበረም። 15እግዚአብሔር በእስራኤል ነገዶች መካከል አስደንጋጭ ስብራት ስላደረገ የእግዚአብሔር ሕዝብ ለብንያማውያን ዐዘነ። 16የጉባኤውም መሪዎች እንዲህ አሉ፤ “እነሆ፤ የብንያም ሴቶች ዐልቀዋል፤ ታዲያ ለቀሩት ወንዶች ሚስት የምናገኝላቸው እንዴት ነው? 17ከእስራኤል ነገዶች አንዱ የሆነው እንዳይጠፋ አሁን በሕይወት ያሉት ብንያማውያን ወራሽ የሚሆን ዘር ሊኖራቸው ይገባል። 18‘ልጁን ለብንያማዊ የሚድር ርጉም ይሁን’ ብለን እኛ እስራኤላውያን ስለ ተማማልን እንግዲህ ልጆቻችንን ልንድርላቸው አንችልም፤ 19ይሁን እንጂ ከቤቴል በስተ ሰሜንና ከቤቴል ወደ ሴኬም በሚወስደው መንገድ በስተ ምሥራቅ እንዲሁም ከለቦና በስተ ደቡብ ባለችው በሴሎ የእግዚአብሔር በዓል በየዓመቱ ይከበራል።”
20ስለዚህም ለብንያማውያን እንዲህ ሲሉ መመሪያ ሰጧቸው፤ “ሄዳችሁ በወይኑ የአትክልት ስፍራ ተደበቁ፤ 21አድፍጣችሁ ተጠባበቁ። የሴሎ ልጃገረዶች ለጭፈራ ወደዚያ በሚወጡበት ጊዜ፣ ከወይኑ አትክልት ቦታ ወጥታችሁ ከልጃገረዶቹ ለየራሳችሁ ሚስት ጥለፉ፤ ወደ ብንያምም ምድር ሂዱ። 22አባቶቻቸውም ሆኑ ወንድሞቻቸው ቢቃወሙ፣ ‘በጦርነት ጊዜ ለእያንዳንዳቸው የሚሆኑ ሚስቶች ስላላገኘን ነውና እነርሱን በመርዳት ምሕረት አድርጉልን፤ እናንተም ደግሞ ልጆቻችሁን ፈቅዳችሁ ያልዳራችሁ በመሆናችሁ በደለኞች አትሆኑም’ እንላቸዋለን።”
23ብንያማውያን እንደ ተባሉት አደረጉ፤ ልጃገረዶቹ በሚጨፍሩበትም ጊዜ እያንዳንዱ ሰው አንዳንድ እየጠለፈ ሚስት እንድትሆነው ይዞ ሄደ፤ ከዚያም ወደ ርስታቸው ተመለሱ፤ ከተሞቻቸውንም አድሰው በዚያ ኖሩ።
24በዚያን ጊዜ እስራኤላውያን ያን ቦታ ትተው ወደየቤታቸው፣ ወደየርስታቸው፣ ወደየጐሣቸውና ወደየነገዳቸው ሄዱ።
25በዚያን ዘመን በእስራኤል ንጉሥ አልነበረም፤ እያንዳንዱም ሰው መልካም መስሎ የታየውን ያደርግ ነበር።
زنانی برای قبیلهٔ بنيامين
1رهبران اسرائيل وقتی در مصفه جمع شده بودند، قسم خوردند كه هرگز اجازه ندهند دختران آنها با مردان قبيلهٔ بنيامين ازدواج كنند. 2سپس به بيتئيل آمده تا غروب آفتاب در حضور خدا نشستند. آنها به شدت میگريستند و میگفتند: 3«ای خداوند، خدای اسرائيل، چرا اين حادثه رخ داد و ما يكی از قبايل خود را از دست داديم؟»
4روز بعد، صبح زود برخاسته، قربانگاهی ساختند و بر روی آن قربانیهای سلامتی و سوختنی تقديم كردند. 5آنها میگفتند: «وقتی كه برای مشورت در حضور خداوند در مصفه جمع شديم آيا قبيلهای از اسرائيل بود كه به آنجا نيامده باشد؟» (در آن موقع همه با هم قسم خورده بودند كه اگر يكی از قبايل، از آمدن به حضور خداوند خودداری نمايد، حتماً بايد نابود گردد.) 6قوم اسرائيل به سبب نابود شدن قبيلهٔ بنيامين، سوگوار و غمگين بودند و پيوسته با خود میگفتند: «از قبايل اسرائيل يک قبيله نابود شد. 7اكنون برای آن عدهای كه باقيماندهاند از كجا زن بگيريم؟ زيرا ما به خداوند قسم خوردهايم كه دختران خود را به آنها ندهيم؟»
8-9برای اينكه معلوم شود كدام قبيله از قبايل اسرائيل از آمدن به مصفه خودداری كرده بود، آنها به شمارش قوم پرداختند. سرانجام معلوم شد كه از يابيش جلعاد هيچكس نيامده بود. 10-12پس اسرائيلیها دوازده هزار نفر از بهترين جنگاوران خود را فرستادند تا مردم يابيش جلعاد را نابود كنند. آنها رفته، تمام مردان و زنان و بچهها را كشتند و فقط دختران باكره را كه به سن ازدواج رسيده بودند باقی گذاردند. تعداد اين دختران چهارصد نفر بود كه آنها را به اردوگاه اسرائيل در شيلوه آوردند.
13آنگاه اسرائیلیها نمايندگانی جهت صلح نزد بازماندگان قبيلهٔ بنيامين كه به صخرهٔ رمون گريخته بودند، فرستادند. 14مردان قبيلهٔ بنيامين به شهر خود بازگشتند و اسرائیلیها آن چهارصد دختر را به ايشان دادند. ولی تعداد اين دختران برای آنها كافی نبود.
15قوم اسرائيل برای قبيلهٔ بنيامين غمگين بود، زيرا خداوند در ميان قبايل اسرائيل جدايی بوجود آورده بود. 16-17رهبران اسرائيل میگفتند: «برای بقيهٔ آنها از كجا زن بگيريم، چون همهٔ زنان قبيلهٔ بنيامين مردهاند؟ بايد در اين باره چارهای بينديشيم تا نسل اين قبيله از بين نرود و قبيلهای از اسرائيل كم نشود. 18ولی ما نمیتوانيم دختران خود را به آنها بدهيم، چون كسی را كه دختر خود را به قبيلهٔ بنيامين بدهد لعنت كردهايم.» 19ولی بعد به ياد آوردند كه هر سال در شيلوه عيدی برای خداوند برگزار میشود. (شيلوه در سمت شرقی راهی كه از بيتئيل به شكيم میرود در ميان لبونه و بيتئيل واقع شده بود.) 20پس به مردان بنيامينی گفتند: «برويد و خود را در تاكستانها پنهان كنيد. 21وقتی دختران شيلوه برای رقصيدن بيرون آيند، شما از تاكستانها بيرون بياييد و آنها را برباييد و به خانههای خود ببريد تا همسران شما گردند. 22اگر پدران و برادران آنها برای شكايت نزد ما بيايند به ايشان خواهيم گفت: آنها را ببخشيد و بگذاريد دختران شما را پيش خود نگه دارند؛ زيرا در اين جنگ آنها بدون زن مانده بودند و شما نيز نمیتوانستيد برخلاف عهد خود رفتار كرده، به آنها زن بدهيد.»
23پس مردان بنيامينی چنين كردند و از ميان دخترانی كه در شيلوه میرقصيدند، هر يک برای خود زنی گرفته، به سرزمين خود برد. سپس ايشان شهرهای خود را از نو بنا كرده، در آنها ساكن شدند.
24بنیاسرائيل پس از اين واقعه، آن مكان را ترک گفته، هر يک به قبيله و خاندان و ملک خود بازگشتند.
25در آن زمان بنیاسرائيل پادشاهی نداشت و هر کس هر چه دلش میخواست میكرد.