እስራኤላውያን ከቀሩት ከነዓናውያን ጋር ያደረጉት ውጊያ
1ጕኢያሱ ከሞተ በኋላ እስራኤላውያን፣ “ከነዓናውያንን ለመውጋት ማን ቀድሞ ይውጣልን?” ብለው እግዚአብሔርን ጠየቁ።
2እግዚአብሔርም፣ “ይሁዳ ቀድሞ ይውጣ፤ እነሆ ምድሪቱን በእጁ አሳልፌ ሰጥቼዋለሁ” በማለት መለሰ።
3የይሁዳም ሰዎች ወንድሞቻቸውን የስምዖንን ልጆች፣ “ከነዓናውያንን ለመውጋት ድርሻችን ወደ ሆነው ምድር አብረን እንውጣ፤ እኛም እንደዚሁ ድርሻችሁ ወደ ሆነው ምድር አብረናችሁ እንወጣለን” አሏቸው፤ ስለዚህም የስምዖን ሰዎች አብረዋቸው ሄዱ።
4ይሁዳ በከነዓናውያንና በፌርዛውያን ላይ ወጣ፤ እግዚአብሔርም በእጃቸው አሳልፎ ሰጣቸው፤ ቤዜቅ በተባለውም ስፍራ ዐሥር ሺሕ ሰው ገደሉ። 5በዚህም ኦዶኒቤዜቅን አግኝተው ተዋጉት፤ ከነዓናውያንንና ፌርዛውያንን ድል አደረጉ። 6አዶኒቤዜቅም ከዚያ ሸሸ፤ እነርሱ ግን አሳድደው ያዙት፤ የእጆቹንና የእግሮቹንም አውራ ጣቶች ቈረጡ።
7ከዚያም አዶኒቤዜቅ፣ “የእጃቸውና የእግራቸው አውራ ጣቶች የተቈረጡባቸው ሰባ ነገሥታት ከገበታዬ ሥር የወደቀ ፍርፋሪ ይለቃቅሙ ነበር፤ አሁን ግን እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ የፈጸምሁትን አመጣብኝ” አለ፤ እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም አመጡት፤ በዚያም ሞተ።
8የይሁዳ ሰዎች ኢየሩሳሌምን ወግተው ያዟት፤ ከተማዪቱንም በሰይፍ ስለት መተው፣ በእሳት አቃጠሏት።
9ከዚያም በኋላ የይሁዳ ሰዎች በኰረብታማው አገር፣ በኔጌብና በምዕራቡ ኰረብታ ግርጌ የሚኖሩትን ከነዓናውያንን ለመውጋት ወረዱ፤ 10ቀደም ሲል ቂርያት አርባቅ ተብላ በምትጠራው በኬብሮን በሚኖሩት ከነዓናውያን ላይ ዘመቱ፤ ሴሲንን፣ አኪመንንና ተላሚንን ድል አደረጉ።
11ከዚያም ቀደም ሲል ቅርያትሤፍር ተብላ በምትጠራው በዳቤር በሚኖሩት ሰዎች ላይ ዘመቱ። 12ካሌብም፣ “ቅርያት ሤፍርን ወግቶ ለሚይዛት ሰው ልጄን ዓክሳንን እድርለታለሁ” አለ። 13በዚህ ጊዜ የካሌብ ወንድም የቄኔዝ ልጅ ጎቶንያል ከተማዪቱን ያዘ፤ ካሌብም ልጁን ዓክሳንን ዳረለት።
14እርሷም ወደ ጎቶንያል በመጣች ጊዜ፣ አባቷ የዕርሻ መሬት እንዲሰጠው ይለምነው ዘንድ አጥብቃ ነገረችው፤1፥14 ዕብራይስጡ፣ ሰብዓ ሊቃናትና ቩልጌት አጥብቆ ነገረው ይላሉ። ካሌብም እርሷ ከአህያዋ ላይ እንደ ወረደች “ምን እንዳደርግልሽ ትፈልጊያለሽ?” ሲል ጠየቃት።
15እርሷም፣ “እባክህ አንድ ነገር አድርግልኝ፤ በኔጌብ መሬት እንደ ሰጠኸኝ ሁሉ፣ አሁንም የውሃ ምንጭ ስጠኝ” አለችው፤ ካሌብም የላይኛውንና የታችኛውን ምንጮች ሰጣት።
16የቄናዊው የሙሴ ዐማት ዝርያዎች ከዓራድ አጠገብ በኔጌብ ውስጥ በይሁዳ ምድረ በዳ ካሉት ሕዝቦች ጋር አብረው ለመኖር፣ ከይሁዳ ሰዎች ጋር በመሆን ከባለ ዘንባባዋ ከተማ ከኢያሪኮ ወጡ።
17የይሁዳ ሰዎች ከወንድሞቻቸው ከስምዖን ልጆች ጋር ሆነው በጻፋት በሚኖሩት ከነዓናውያን ላይ ዘመቱ፤ ከተማዪቱንም ፈጽሞ ደመሰሷት1፥17 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ነገር ወይም ሰው ሙሉ ለሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን የሚያሳይ ነው፤ ስለዚህ ከተማዪቱ ሔርማ1፥17 ሔርማ ማለት ጥፋት ማለት ነው ተብላ ተጠራች። 18ደግሞም የይሁዳ ሰዎች ጋዛ፣ አስቀሎና፣ አቃሮን የተባሉትን ከተሞች ከነግዛቶቻቸው ያዙ1፥18 ዕብራይስጡና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም አልያዙም ይላሉ።።
19እግዚአብሔር ከይሁዳ ሰዎች ጋር ነበር፤ ስለዚህ ኰረብታማውን አገር ያዙ፤ ነገር ግን በረባዳው ምድር የሚኖሩት ሰዎች ከብረት የተሠሩ ሠረገሎች ስለ ነበሯቸው ከዚያ አሳድደው ሊያስወጧቸው አልቻሉም። 20ሙሴ ባዘዘው መሠረት ኬብሮን ለካሌብ ተሰጠች፤ እርሱም ሦስቱን የዔናቅ ልጆች ከውስጧ አሳደደ። 21የብንያም ልጆች በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን ኢያቡሳውያንን ከዚያ ሊያስወጧቸው አልቻሉም፤ ስለዚህ ኢያቡሳውያን እስከ ዛሬ ድረስ ከብንያማውያን ጋር በዚያ አብረው ይኖራሉ።
22የዮሴፍ ወገን ደግሞ ቤቴልን ወጉ፤ እግዚአብሔርም ከእነርሱ ጋር ነበር። 23እነርሱም ቀደም ሲል ሎዛ ትባል ወደ ነበረችው ወደ ቤቴል ሰላዮችን በላኩ ጊዜ፣ 24ሰላዮቹም አንድ ሰው ከከተማዪቱ ሲወጣ አይተው፤ “የከተማዪቱን መግቢያ አሳየን፤ እኛም ምሕረት እናደርግልሃለን” አሉት። 25እርሱም አሳያቸው፤ እነርሱም ከሰውየውና ከቤተ ሰቡ በስተቀር የከተማዪቱን ሕዝብ በሰይፍ ስለት ፈጁ። 26ሰውየውም ወደ ኬጢያውያን ምድር ሄዶ ከተማ ሠራ፤ ስሟንም ሎዛ ብሎ ጠራት፤ እስከ ዛሬም የምትጠራው በዚሁ ስም ነው።
27የምናሴ ነገድ ግን በቤትሳን፣ በታዕናክ፣ በዶር፣ በይብለዓም፣ በመጊዶንና በየአካባቢያቸው ያሉት መንደሮች ነዋሪውን ሕዝብ ስላላስወጡ፣ ከነዓናውያን ኑሯቸውን በዚያው ለማድረግ ወሰኑ። 28እስራኤላውያን በበረቱ ጊዜ ግን ከነዓናውያንን የጕልበት ሥራ እንዲሠሩ አስገደዷቸው እንጂ ፈጽሞ አላስወጧቸውም። 29እንደዚሁም የኤፍሬም ወገኖች በጌዝር የሚኖሩትን ከነዓናውያንን ማስወጣት አልቻሉም፤ ስለዚህ ከነዓናውያን በመካከላቸው እዚያው መኖርን ቀጠሉ። 30ዛብሎንም እንደዚሁ በቂድሮንና በነህሎል የነበሩትን በመካከላቸው የቀሩትን ከነዓናውያንን አላስወጣም፤ ነገር ግን የጕልበት ሥራ እንዲሠሩ አስገደዳቸው። 31አሴርም በዓኮ፣ በሲዶን፣ በአሕላብ፣ በአክዚብ፣ በሒልባ፣ በኣፌቅና በረአብ የሚኖሩትን አላስወጣም፤ 32በዚህ ምክንያት የአሴር ሕዝብ በምድሪቱ ካሉት ከነዓናውያን ጋር አብረው ኖሩ። 33ንፍታሌምም በቤት ሳሚስና በቤትዓናት የሚኖሩትን አላስወጣም፤ ስለዚህ የንፍታሌም ነገድ በምድሪቱ ከሚኖሩት ከነዓናውያን ጋር አብረው ኖሩ፤ ይሁን እንጂ በቤት ሳሚስና በቤትዓናት የሚኖሩት ለእነርሱ የጕልበት ሥራ ተገድደው ይሠሩ ነበር። 34የዳን ነገድ በኰረብታማው ምድር ብቻ እንዲወሰን እንጂ ወደ ሜዳማው አገር እንዲወርድ አሞራውያን አልፈቀዱለትም። 35አሞራውያንም በሔሬስ ተራራ፣ በኤሎንና በሸዓልቢም ኑሯቸውን ቀጠሉ፤ ይሁን እንጂ የዮሴፍ ወገን በበረታ ጊዜ ተገድደው የጕልበት ሥራ ከመሥራት አላመለጡም። 36የአሞራውያን ድንበር አቅራቢያም መተላለፊያ እስከ ሴላዕና ከዚያም የሚያልፍ ነበር።
Juda og Simeon indtager deres område
1Efter Josvas død spurgte israelitterne Herren: „Hvem skal nu gå i spidsen i kampen mod kana’anæerne?”
2Herren svarede: „Judas stamme. Jeg vil hjælpe dem til at indtage det land, jeg har lovet dem.”
3Lederne af Judas stamme sagde til lederne af Simeons stamme: „Hjælp os med at besejre de kana’anæere, som bor i det område, der skal tilhøre os. Så hjælper vi bagefter jer med at indtage jeres område.” Så fulgte mændene fra Simeons stamme med Judas mænd.
4Da de angreb, gav Herren dem sejr over kana’anæerne og perizzitterne, så de dræbte 10.000 af fjendens krigere ved byen Bezek. 5Fjendens hær blev anført af kong Adonibezek, 6og det lykkedes ham at undslippe, men israelitterne fangede ham og huggede hans tommelfingre og storetæer af. 7„Jeg har selv behandlet 70 høvdinge på samme måde,” sagde kongen, „og jeg har ladet dem spise smulerne under mit bord. Nu gengælder Gud mig for, hvad jeg har gjort imod dem.” Derefter blev han ført til Jerusalem, hvor han blev til sin dødsdag.
8Judas mænd angreb også Jerusalem, huggede indbyggerne ned og satte ild til byen. 9Derefter rykkede de ud mod kana’anæerne i det sydlige højland, i Negev og på de vestlige bakkeskråninger. 10De gik til angreb på kana’anæerne i Hebron, det tidligere Kirjat-Arba, og besejrede Sheshajs, Ahimans og Talmajs mænd. 11De angreb også byen Debir, der tidligere hed Kirjat-Sefer. 12Kaleb havde forinden sagt: „Den, der indtager Kirjat-Sefer, får min datter Aksa til kone.” 13Otniel, der var søn af Kalebs yngre bror, Kenaz, erobrede byen og fik som belønning Aksa til kone.
14Efter brylluppet bad Aksa sin mand om tilladelse til at tage hjem til sin far og bede om et stykke agerjord. Da hun kom derhen og stod af sit æsel, spurgte Kaleb hende: „Hvad kan jeg gøre for dig?” 15„Velsign mig med en afskedsgave. Du har jo bortgiftet mig til det tørre sydland, så jeg har brug for nogle vandkilder.” Så gav Kaleb hende de øvre og de nedre kilder.
16Dengang Judas stamme drog op fra Palmernes By,1,16 Det vil sige Jeriko. fulgte efterkommerne af Moses’ svigerfar med dem. De hed kenitterne, og de slog sig ned blandt de øvrige beboere i Negevs ørken syd for Arad.
17Da Judas og Simeons mænd drog i kamp sammen, udryddede de kana’anæerne i Zefat og udslettede byen totalt. Derfor kaldes byen nu Horma.1,17 Horma betyder „udslettelse”. 18Judas hær indtog også byerne Gaza, Ashkalon og Ekron med de omkringliggende områder. 19Herren hjalp Judas stamme med at indtage højlandet, men de klarede ikke at få alle folkene i lavlandet drevet bort, fordi de havde stridsvogne af jern.
20Kaleb havde nu fået Hebron, som Moses i sin tid havde lovet ham, og han fik jaget de folk bort, som boede der. De var efterkommere af Anaks tre sønner.
De øvrige stammer fordriver ikke alle de oprindelige indbyggere
21Benjamins stamme fordrev ikke alle jebusitterne fra Jerusalem. Derfor bor jebusitterne stadig i byen sammen med benjaminitterne.
22-23Efraims og Manasses stammer angreb byen Betel, tidligere kaldet Luz, og Herren var med dem. De sendte først spioner af sted, 24som fangede en mand, der var på vej ud af byen. De sagde så til ham: „Hvis du viser os, hvordan vi kommer ind i byen, vil vi skåne dit liv.” 25Manden viste dem et smuthul, hvorefter hele byens befolkning blev hugget ned, med undtagelse af den mand og hans familie. 26Senere flyttede han til hittitternes land og grundlagde der en by, som han kaldte Luz.1,26 Opkaldt efter det gamle navn på hans hjemby. Det vides ikke, hvor denne by lå. Byen ligger der den dag i dag.
27Manasses stamme fordrev ikke alle indbyggerne i Bet-Shan, Ta’anak, Dor, Jibleam og Megiddo og landsbyerne deromkring, for kana’anæerne var fast besluttet på at blive boende. 28Senere, da israelitterne blev stærkere, gjorde de kana’anæerne til slaver, men de fik aldrig fordrevet dem fra landet. 29På samme måde gik det for Efraims stamme. Kana’anæerne blev boende side om side med dem i Gezer.
30Zebulons stamme udryddede heller ikke kana’anæerne i Kitron og Nahalol, men gjorde dem til slaver, 31og Ashers stamme fordrev ikke indbyggerne i Akko, Sidon, Ahlab, Akzib, Helba, Afik og Rehob. 32Kana’anæerne blev boende side om side med Ashers stamme. 33På samme måde gik det for Naftalis stamme: de fordrev ikke indbyggerne i Bet-Shemesh og Bet-Anat, men de gjorde dem til slaver.
34Amoritterne holdt stand mod Dans stamme, så de ikke kunne bosætte sig i lavlandet. 35Amoritterne blev også boende på Heresbjerget, i Ajjalon og i Sha’albim, men da Efraims og Manasses stammer blev stærkere, gjorde de dem til slaver. 36Amoritternes sydlige grænse løber fra Akrabbimpasset til Sela og videre opefter.