ሕዝቅኤል 7 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 7:1-27

ፍጻሜው ደረሰ

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“አንተ የሰው ልጅ ሆይ፤ ጌታ እግዚአብሔር ለእስራኤል ምድር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ፍጻሜ! በአራቱም የምድሪቱ ማእዘን

ፍጻሜ መጥቷል!

3አሁንም መጨረሻሽ ደርሷል፤

ቍጣዬን በአንቺ ላይ አፈስሳለሁ፤

እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤

ስለ ጸያፍ ተግባርሽ ሁሉ፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

4በርኅራኄ ዐይን አልመለከትሽም፤

ምሕረትም አላደርግልሽም፤

ስለ አካሄድሽና በመካከልሽ ስላለው ጸያፍ ተግባር፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ፤

በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።’

5“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘መዓት! ተሰምቶ የማይታወቅ መዓት7፥5 አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች እንዲሁ ናቸው፤ አንዳንድ የዕብራይስጥና የሱርስት የጥንት ቅጆች ግን በጥፋት ላይ ጥፋት ይላሉ ይመጣል።

6ፍጻሜ መጥቷል!

ፍጻሜ መጥቷል!

በአንቺ ላይ ተነሣሥቷል፤

እነሆ፤ ደርሷል!

7እናንት በምድሪቱ የምትኖሩ ሆይ፤

የጥፋት ፍርድ መጥቶባችኋል፤

ጊዜው ደርሷል፤

በተራሮች ላይ እልልታ ሳይሆን ሽብር የሚሰማበት ቀን ቀርቧል።

8እነሆ፤ መዓቴን በቅርብ ቀን አፈስስብሻለሁ፤

በአንቺ ላይ ቍጣዬን እፈጽምብሻለሁ፤

እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤

ስለ ጸያፍ ተግባርሽም ሁሉ ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

9በርኅራኄ ዐይን አልመለከትሽም፤

ምሕረት አላደርግልሽም፤

ስለ አካሄድሽና በመካከልሽ ስላለው ጸያፍ ተግባር፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ፤

በዚያ ጊዜ፣ የምቀሥፍ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ታውቃላችሁ።

10“ ‘እነሆ ቀኑ ይኸው ደረሰ!

የጥፋት ፍርድ ተገልጧል፤

በትሩ አቈጥቍጧል፤

ትዕቢት አብቧል።

11ዐመፅ ዐድጋ7፥11 ወይም ዐመፀኛው የክፋት በትር

የክፋት በትር ሆነች፤

ከሕዝቡ አንድም አይተርፍም፤

ከሰዎቹ፣

ከሀብታቸውና እርባና ካለው ነገር

አንዳች አይቀርም።

12ጊዜው ደርሷል፤

ቀኑም ይኸው!

መዓት በሕዝቡ ሁሉ ላይ ስለ መጣ፣

የሚገዛ አይደሰት፤

የሚሸጥም አይዘን።

13ሁለቱ በሕይወት እስካሉ ድረስ

ሻጩ የሸጠውን መሬት አያስመልስም፤

ስለ መላው ሕዝብ የተነገረው ራእይ አይለወጥምና።

ከኀጢአታቸው የተነሣ ሕይወቱን ማትረፍ የሚችል አንድም አይገኝም።

14“ ‘መለከት ቢነፉም፣

ሁሉንም ነገር ቢያዘጋጁም፣

ወደ ጦርነት የሚሄድ አንድ እንኳ አይኖርም፤

መዓቴ በሕዝብ ሁሉ ላይ መጥቷልና።

15በውጭ ሰይፍ፣

በውስጥ ደግሞ ቸነፈርና ራብ አለ፤

በገጠር ያሉት

በሰይፍ ይወድቃሉ፤

በከተማ ያሉትም

በራብና በቸነፈር ያልቃሉ።

16ተርፈው ያመለጡት ሁሉ

በሸለቆ እንደሚኖሩ ርግቦች

ስለ ኀጢአታቸው እያለቀሱ

በተራራ ላይ ይሆናሉ።

17እጅ ሁሉ ይዝላል፤

ጕልበት ሁሉ ውሃ ይሆናል።

18ማቅ ይለብሳሉ፤

ሽብርም ይውጣቸዋል።

ፊታቸው ኀፍረት ይለብሳል፤

ራሳቸውም ይላጫል።

19“ ‘ብራቸውን በየጐዳናው ይጥላሉ፤

ወርቃቸውም እንደ ርኩስ ነገር ይቈጠራል።

በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን

ብራቸውና ወርቃቸው

ሊያድናቸው አይችልም፤

በኀጢአት እንዲወድቁ ዕንቅፋት ሆኖባቸዋልና

በልተው አይጠግቡበትም፤ ሆዳቸውንም አይሞሉበትም።

20በውብ ዕንቋቸው ታብየዋል፤

ይህንም አስጸያፊ የጣዖት ምስሎቻቸውንና

ርኩስ ቅርጻ ቅርጾችን ለመሥራት ተጠቅመውበታል።

ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ወደ ርኩሰት እለውጥባቸዋለሁ።

21ለባዕዳን ዝርፊያ፣ ለምድር ክፉዎችም ብዝበዛ አድርጌ አሳልፌ እሰጣለሁ፤

እነርሱም ያረክሱታል።

22ፊቴን ከእነርሱ እመልሳለሁ፤

እነርሱም የከበረውን ቦታዬን ያረክሳሉ፤

ወንበዴዎች ይገቡበታል፤

ያረክሱታልም።

23“ ‘ምድር በደም መፋሰስ፣

ከተማዪቱም በዐመፅ ተሞልታለችና

ሰንሰለት አዘጋጅ።

24እጅግ የከፉትን ከአሕዛብ አምጥቼ

ቤቶቻቸውን እንዲነጥቁ አደርጋለሁ፣

የኀያላኑንም ትዕቢት አጠፋለሁ፤

መቅደሳቸውም ይረክሳል።

25ሽብር በመጣ ጊዜ ሰላምን ይሻሉ፤

ነገር ግን አያገኟትም።

26ጥፋት በጥፋት ላይ፣

ወሬም በወሬ ላይ ይመጣል።

ራእይን ከነቢይ ለማግኘት ይጥራሉ፤

የሕግ ትምህርት ከካህኑ፣

ምክርም ከሽማግሌው ዘንድ ይጠፋል።

27ንጉሡ ያለቅሳል፤

መስፍኑ ተስፋ መቍረጥን ይከናነባል፤

የምድሪቱም ሕዝብ እጅ ትንቀጠቀጣለች።

የእጃቸውን እከፍላቸዋለሁ፤

ራሳቸው ባወጡት መስፈርት መሠረት

እፈርድባቸዋለሁ።

በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

New International Version

Ezekiel 7:1-27

The End Has Come

1The word of the Lord came to me: 2“Son of man, this is what the Sovereign Lord says to the land of Israel:

“ ‘The end! The end has come

upon the four corners of the land!

3The end is now upon you,

and I will unleash my anger against you.

I will judge you according to your conduct

and repay you for all your detestable practices.

4I will not look on you with pity;

I will not spare you.

I will surely repay you for your conduct

and for the detestable practices among you.

“ ‘Then you will know that I am the Lord.’

5“This is what the Sovereign Lord says:

“ ‘Disaster! Unheard-of7:5 Most Hebrew manuscripts; some Hebrew manuscripts and Syriac Disaster after disaster!

See, it comes!

6The end has come!

The end has come!

It has roused itself against you.

See, it comes!

7Doom has come upon you,

upon you who dwell in the land.

The time has come! The day is near!

There is panic, not joy, on the mountains.

8I am about to pour out my wrath on you

and spend my anger against you.

I will judge you according to your conduct

and repay you for all your detestable practices.

9I will not look on you with pity;

I will not spare you.

I will repay you for your conduct

and for the detestable practices among you.

“ ‘Then you will know that it is I the Lord who strikes you.

10“ ‘See, the day!

See, it comes!

Doom has burst forth,

the rod has budded,

arrogance has blossomed!

11Violence has arisen,7:11 Or The violent one has become

a rod to punish the wicked.

None of the people will be left,

none of that crowd—

none of their wealth,

nothing of value.

12The time has come!

The day has arrived!

Let not the buyer rejoice

nor the seller grieve,

for my wrath is on the whole crowd.

13The seller will not recover

the property that was sold—

as long as both buyer and seller live.

For the vision concerning the whole crowd

will not be reversed.

Because of their sins, not one of them

will preserve their life.

14“ ‘They have blown the trumpet,

they have made all things ready,

but no one will go into battle,

for my wrath is on the whole crowd.

15Outside is the sword;

inside are plague and famine.

Those in the country

will die by the sword;

those in the city

will be devoured by famine and plague.

16The fugitives who escape

will flee to the mountains.

Like doves of the valleys,

they will all moan,

each for their own sins.

17Every hand will go limp;

every leg will be wet with urine.

18They will put on sackcloth

and be clothed with terror.

Every face will be covered with shame,

and every head will be shaved.

19“ ‘They will throw their silver into the streets,

and their gold will be treated as a thing unclean.

Their silver and gold

will not be able to deliver them

in the day of the Lord’s wrath.

It will not satisfy their hunger

or fill their stomachs,

for it has caused them to stumble into sin.

20They took pride in their beautiful jewelry

and used it to make their detestable idols.

They made it into vile images;

therefore I will make it a thing unclean for them.

21I will give their wealth as plunder to foreigners

and as loot to the wicked of the earth,

who will defile it.

22I will turn my face away from the people,

and robbers will desecrate the place I treasure.

They will enter it

and will defile it.

23“ ‘Prepare chains!

For the land is full of bloodshed,

and the city is full of violence.

24I will bring the most wicked of nations

to take possession of their houses.

I will put an end to the pride of the mighty,

and their sanctuaries will be desecrated.

25When terror comes,

they will seek peace in vain.

26Calamity upon calamity will come,

and rumor upon rumor.

They will go searching for a vision from the prophet,

priestly instruction in the law will cease,

the counsel of the elders will come to an end.

27The king will mourn,

the prince will be clothed with despair,

and the hands of the people of the land will tremble.

I will deal with them according to their conduct,

and by their own standards I will judge them.

“ ‘Then they will know that I am the Lord.’ ”