ሕዝቅኤል 41 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 41:1-26

1ከዚያም ወደ መቅደሱ አገባኝ፤ ዐምዶቹንም ለካ፤ የዐምዶቹም ወርድ41፥1 አንድ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጅና ሰብዐ ሊቃናት እንዲሁ ሲሆኑ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን …የድንኳኑ ወርድ ይላሉ በአንዱ በኩል ስድስት ክንድ፣ በሌላውም በኩል ስድስት ክንድ ነበር። 2የመግቢያውም በር ወርድ ዐሥር ክንድ ሲሆን፣ በግራና በቀኝ በኩል ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች ወርድ አምስት ክንድ ነበር። ደግሞም የውስጡን መቅደስ ለካ፤ ርዝመቱ አርባ ክንድ፣ ወርዱም ሃያ ክንድ ነበር።

3ከዚያም ወደ ውስጥ ገባ፤ የመግቢያውን ዐምዶች ለካ፤ የእያንዳንዱም ወርድ ሁለት ክንድ ነበር። የመግቢያውም ወርድ ስድስት ክንድ ሲሆን፣ ግራና ቀኝ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች ወርድ ደግሞ ሰባት ክንድ ነበር። 4እርሱም የውስጠኛውን መቅደስ ርዝመት ለካ፤ ሃያ ክንድ ነበር፤ ወርዱም የውጪውን ግድግዳ ጨምሮ ሃያ ክንድ ነበር፤ እርሱም፣ “ይህ ቅድስተ ቅዱሳን ነው” አለኝ።

5ከዚያም የቤተ መቅደሱን ግንብ ለካ፤ ውፍረቱ ስድስት ክንድ ነው፤ በቤተ መቅደሱ ግንብ ዙሪያ ግራና ቀኝ ያለው የእያንዳንዱ ክፍል ወርድ አራት ክንድ ነበር። 6ግራና ቀኝ ያሉት ክፍሎች፣ ባለ ሦስት ደርብ ናቸው፤ በእያንዳንዱም ደርብ ላይ ሠላሳ ክፍሎች ነበሩ፤ በግንቡም ዙሪያ ግራና ቀኝ ያሉትን እነዚህን ክፍሎች ደግፈው የሚይዙ ተሸካሚዎች ነበሩ፤ ሆኖም ተሸካሚዎቹ ወደ ቤተ መቅደሱ ግንብ ዘልቀው አልገቡም ነበር። 7በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ያሉት ክፍሎች ስፋት በየደርቡ እየጨመረ የሚሄድ ነው። በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ያለው ሕንጻ አሠራሩ ከታች ወደ ላይ እየሰፋ የሚሄድ በመሆኑ፣ ወደ ላይ በተሄደ ቍጥር የክፍሎቹ ስፋት እየጨመረ የሚሄድ ነው። በመካከለኛው ደርብ በኩል አድርጎ ከታች ወደ ላይ የተዘረጋም ደረጃ አለ። 8ቤተ መቅደሱ ዙሪያውን ከፍ ብሎ የተሠራ መሠረት ያለው መሆኑን አየሁ፤ ይህ ግራና ቀኝ ላሉት ክፍሎች መሠረት ሲሆን፣ ርዝመቱ ስድስት ክንድ ነው፤ ይህም የዘንጉ ቁመት ነበር። 9በውጭ በኩል ያለው የግራና የቀኙ ክፍሎች ግንብ ውፍረት አምስት ክንድ ነበር፤ ክፍቱ ቦታ በቤተ መቅደሱና 10በካህናቱ ክፍሎች መካከል ያለ ሲሆን፣ ስፋቱ በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ሃያ ክንድ ነበር። 11ከክፍቱ ቦታ ግራና ቀኝ ወዳሉ ክፍሎች የሚያስገቡ በሮች ነበሩ። አንዱ በሰሜን በኩል ሲሆን፣ ሌላው በር ደግሞ በደቡብ በኩል ነው። ክፍቱን ቦታ ዙሪያውን የሚያገናኘው መሠረት ስፋቱ አምስት ክንድ ነው።

12በምዕራብ በኩል ከቤተ መቅደሱ ግቢ ትይዩ የሆነው ሕንጻ ወርድ ሰባ ክንድ ነበር። የሕንጻው ግንብ ውፍረት ዙሪያውን አምስት ክንድ ሲሆን፣ ርዝመቱ ዘጠና ክንድ ነበር።

13ከዚያም ቤተ መቅደሱን ለካ፤ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ ሲሆን፣ የቤተ መቅደሱ ግቢና ሕንጻ ከነግንቡ ደግሞ አንድ መቶ ክንድ ሆነ። 14በምሥራቅ በኩል የቤተ መቅደሱ ግቢ ስፋት፣ ከቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ያለውን ስፍራ ጨምሮ አንድ መቶ ክንድ ነበር።

15ከዚያም ከቤተ መቅደሱ በስተ ጀርባ ከግቢው ትይዩ ያለውን ሕንጻ ለካ፤ ይህም በግራና በቀኝ ያሉትን መተላለፊያዎች የሚጨምር ሲሆን፣ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ ነበር።

የውጩ መቅደስና የውስጡ መቅደስ ከአደባባዩ ትይዩ ያለው መተላለፊያ በረንዳ፣ 16እንዲሁም መድረኮቹና ጠበብ ያሉት መስኮቶች፣ በሦስቱም ዙሪያ ያሉት መተላለፊያዎች፣ ከመድረኩ በላይና ራሱ መድረኩም ጭምር ሁሉም በዕንጨት ተለብዶ ነበር። ወለሉ፣ እስከ መስኮቶቹ ያለው ግንብና መስኮቶቹ ተለብደዋል። 17ከውስጡ መቅደስ መግቢያ በላይ ያለው ውስጡና ውጩ እንዲሁም በውስጡ መቅደስና በውጩ መቅደስ መካከል ያለው ሁሉ ዙሪያውን 18ኪሩቤልና የዘንባባ ዛፍ ተቀርጸውበት ነበር፤ የዘንባባ ዛፎቹ የተቀረጹት በኪሩብና በኪሩብ መካከል ነበር። እያንዳንዱም ኪሩብ ሁለት ፊት ነበረው፤ 19የሰው ፊት ያለው ኪሩብ በአንድ በኩል ወዳለው ዘንባባ የዞረ ሲሆን፣ የአንበሳ ፊት ያለውም በሌላ በኩል ወዳለው ዘንባባ ዞሮ ነበር። ሁሉም በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ላይ ተቀርጸው ነበር። 20ከወለሉ አንሥቶ ከመግቢያው በላይ እስካለው ስፍራ ድረስ፣ የውስጡ መቅደስ የውጭ ግድግዳ ላይ ኪሩቤልና የዘንባባ ዛፍ ተቀርጿል።

21የውስጡ መቅደስ በር መቃን ባለ አራት ማእዘን ነበር፤ ከቅድስተ ቅዱሳኑም ፊት ለፊት ያለው በር እንዲሁ ባለ አራት ማእዘን ነበር። 22ሦስት ክንድ ቁመት፣ ሁለት ክንድ41፥22 ሰብዐ ሊቃናቱ እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ርዝመቱ ሁለት ወርድ ይላል ወርድ፣ ሁለት ክንድ ርዝመት ያለው የዕንጨት መሠዊያ ነበር፤ ማእዘኖቹ፣ መሠረቱና41፥22 ሰብዐ ሊቃናቱ እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ርዝመቱ ይላል ጐኖቹ ሁሉ ከዕንጨት የተሠሩ ነበሩ። ሰውየውም፣ “ይህች በእግዚአብሔር ፊት ያለች ገበታ ናት” አለኝ። 23የውስጡ መቅደስና ቅድስተ ቅዱሳኑ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት በር አላቸው፤ 24እያንዳንዱ በር መካከሉ ላይ በመታጠፊያ የተያያዙ መዝጊያዎች አሉት። 25በግንቦቹ ላይ እንዳለው ሁሉ በውስጡ መቅደስ በሮችም ላይ ኪሩቤልና የዘንባባ ዛፎች ተቀርጸዋል፤ በመተላለፊያ በረንዳውም ፊት ለፊት የዕንጨት መዝጊያ ተንጠልጥሏል። 26በመተላለፊያ በረንዳውም ግራና ቀኝ ግንብ ላይ የዘንባባ ዛፍ ቅርጽ ያለባቸው ጠባብ መስኮቶች ነበሩ። ግራና ቀኝ ያሉት ክፍሎችም በደረጃው በኩል የሚሸፍን ጣሪያ ነበራቸው።

Persian Contemporary Bible

حزقيال 41:1-26

1آنگاه آن مرد مرا به اتاق اول خانهٔ خدا يعنی قدس برد. او اول راه ورودی قدس را اندازه گرفت: از بيرون به داخل سه متر و 2پهنای آن پنج متر بود. ديوارهای طرفين آن هر يک به عرض دو متر و نيم بودند. بعد خود قدس را اندازه گرفت؛ طول آن بيست متر و عرض آن ده متر بود.

3سپس به اتاق اندرون كه پشت قدس بود رفت و راه ورودی آن را اندازه گرفت؛ از بيرون به داخل يک متر و پهنای آن سه متر بود. ديوارهای طرفين آن هر يک به عرض يک متر و نيم بودند. 4سپس اتاق اندرونی را اندازه گرفت؛ ده مترمربع بود. او به من گفت: «اين قدس‌الاقداس است.»

5بعد ديوار خانهٔ خدا را اندازه گرفت. ضخامتش سه متر بود. دور تا دور قسمت بيرونی اين ديوار يک رديف اتاقهای كوچک به عرض دو متر وجود داشت.

6‏-7اين اتاقها در سه طبقه ساخته شده و هر طبقه شامل سی اتاق بود. قسمت بيرونی ديوار خانهٔ خدا به صورت پله بود و سقف اتاقهای طبقهٔ اول و دوم به ترتيب روی پلهٔ اول و دوم قرار می‌گرفت. به طوری كه اتاقهای طبقهٔ سوم از اتاقهای طبقهٔ دوم، و اتاقهای طبقهٔ دوم از اتاقهای طبقهٔ اول، بزرگتر بودند. بدين ترتيب سنگينی اتاقها روی پله‌ها قرار می‌گرفت و به ديوار خانهٔ خدا فشار وارد نمی‌شد. در دو طرف خانهٔ خدا در قسمت بيرونی اتاقها، پله‌هايی برای رفتن به طبقات بالا درست شده بود.

8‏-11ضخامت ديوار بيرونی اين اتاقها دو متر و نيم بود. يک در از طرف شمال خانهٔ خدا و يک در از طرف جنوب آن به سوی اين اتاقها باز می‌شد. من متوجه شدم كه دور تا دور خانهٔ خدا يک سكو، همكف با اتاقهای مجاور وجود داشت كه سه متر بلندتر از زمين بود و با پهنای دو متر و نيم دور تا دور خانهٔ خدا را فرا گرفته بود. در دو طرف خانهٔ خدا در حياط داخلی، به فاصلهٔ ده متر دورتر از سكوها، يک سری اتاق به موازات اتاقهای مجاور خانهٔ خدا ساخته شده بود.

12يک ساختمان در سمت غربی و روبروی حياط خانهٔ خدا قرار داشت كه عرض آن سی و پنج متر، و طولش چهل و پنج متر و ضخامت ديوارهايش دو متر و نيم بود.

13سپس آن مرد از بيرون، طول خانهٔ خدا را اندازه گرفت؛ اندازهٔ آن پنجاه متر بود. در ضمن، از پشت ديوار غربی خانهٔ خدا تا انتهای ديوار ساختمان واقع در غرب خانهٔ خدا، كه در واقع شامل حياط پشتی خانهٔ خدا و تمام عرض آن ساختمان می‌شد، پنجاه متر بود. 14پهنای حياط داخلی جلو خانهٔ خدا نيز پنجاه متر بود. 15او طول ساختمان واقع در سمت غربی خانهٔ خدا را نيز اندازه گرفت. آن هم با احتساب ديوارهای دو طرفش، پنجاه متر بود.

اتاق ورودی خانهٔ خدا، قدس و قدس‌الاقداس، 16همه از كف تا پنجره‌ها روكش چوب داشتند. پنجره‌ها نيز پوشانده می‌شدند. 17‏-18بر ديوارهای داخلی خانهٔ خدا تا قسمت بالای درها نقشهای فرشته و نخل، به طور يک در ميان، حكاكی شده بودند. هر كدام از فرشتگان دو صورت داشت: 19‏-20يكی از دو صورت كه شبيه صورت انسان بود رو به نقش نخل يک سمت، و صورت ديگر كه مثل صورت شير بود رو به نقش نخل سمت ديگر بود. دور تا دور ديوار داخلی خانهٔ خدا به همين شكل بود.

21چارچوب درهای قدس مربع شكل بود و چارچوب در قدس‌الاقداس نيز شبيه آن بود. 22يک قربانگاه چوبی به ارتفاع يک متر و نيم و مساحت يک مترمربع، در آنجا قرار داشت. گوشه‌ها، پايه و چهار طرف آن همه از چوب بود. آن مرد با اشاره به قربانگاه چوبی به من گفت: «اين ميزی است كه در حضور خداوند می‌باشد.»

23در انتهای راه ورودی قدس يک در بود و نيز در انتهای راه ورودی قدس‌الاقداس در ديگری وجود داشت. 24اين درها دو لنگه داشتند و از وسط باز می‌شدند. 25درهای قدس نيز مانند ديوارها با نقشهای فرشتگان و نخلها تزيين شده بودند. بر بالای قسمت بيرونی اتاق ورودی، يک سايبان چوبی قرار داشت. 26بر ديوارهای دو طرف اين اتاق نيز نقشهای نخل حكاكی شده بود، و پنجره‌هايی در آن ديوارها قرار داشت. اتاقهای مجاور خانهٔ خدا نيز دارای سايبان بودند.