ሕዝቅኤል 40 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 40:1-49

አዲሱ ቤተ መቅደስ

1በተሰደድን በሃያ አምስተኛው ዓመት፣ በዓመቱ መጀመሪያ፣ በዐሥረኛው ቀን፣ ከተማዪቱ በወደቀች በዐሥራ አራተኛው ዓመት፣ በዚያው ዕለት የእግዚአብሔር እጅ በላዬ ነበር፤ እርሱም ወደዚያ ወሰደኝ። 2በእግዚአብሔር ራእይ ወደ እስራኤል ምድር አመጣኝ፤ ከፍ ባለ ተራራ ላይ አኖረኝ፤ ከተራራውም በስተ ደቡብ፣ ከተማ የሚመስሉ ሕንጻዎች ነበሩ። 3ወደዚያ ወሰደኝ፤ እነሆ መልኩ ናስ የሚመስል ሰው አየሁ፤ እርሱም የሐር ገመድና መለኪያ ዘንግ በእጁ ይዞ በመግቢያው በር ላይ ቆሞ ነበር። 4ሰውየውም እንዲህ አለኝ፤ “የሰው ልጅ ሆይ፤ በዐይንህ እይ፤ በጆሮህ ስማ፤ የማሳይህንም ሁሉ ልብ ብለህ አስተውል፤ ወደዚህ የመጣኸው ለዚህ ነውና ያየኸውንም ሁሉ ለእስራኤል ቤት ንገር።”

ወደ ውጩ አደባባይ የሚያወጣው የምሥራቅ በር

5የቤተ መቅደሱን ዙሪያ ሙሉ በሙሉ የከበበ ቅጥር አየሁ፤ በሰውየውም እጅ ርዝመቱ ስድስት ክንድ የሆነ መለኪያ ዘንግ አየሁ፤ እያንዳንዱ ክንድ፣ አንድ ክንድ ከስንዝር ነበር፤ እርሱም ቅጥሩን ለካው፤ ስፋቱ አንድ መለኪያ ዘንግ ሲሆን፣ ቁመቱም እንዲሁ አንድ መለኪያ ዘንግ ነበር።

6ከዚያም በምሥራቅ ትይዩ ወዳለው በር መጣ፤ ደረጃዎቹን ወጥቶ የበሩን መግቢያ መድረክ ለካ፤ ቁመቱም አንድ ዘንግ ነበር።40፥6 ከሰብዓ ሊቃናት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን የመጀመሪያው ጕበን ርዝመቱ አንድ ዘንግ ነበር ይላል። 7የዘብ ጠባቂ ቤቶች፣ ቁመታቸው አንድ መለኪያ ዘንግ፣ ወርዳቸውም አንድ መለኪያ ዘንግ ነበር፤ በቤቶቹም መካከል ያሉት ግንቦች ውፍረት አምስት ክንድ ነበር። ከቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ባለው መተላለፊያ በረንዳ አጠገብ በውስጥ በኩል ያለው የበሩ መድረክ ወለል አንድ ዘንግ ነበር።

8ከዚያም የመግቢያውን በር መተላለፊያውን በረንዳ ለካ፤ 9ቁመቱ40፥8-9 በብዙ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች በሰብዓ ሊቃናት፣ በቩልጌትና በሱርስቱም እንዲሁ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን በቤተ መቅደሱ ትይዩ ያለ፣ የመግቢያ በር ነው፤ አንድ ክንድ ነበር 9 ከዚያም የመግቢያ በሩን መተላለፊያ በረንዳ ለካው ይላሉ። ስምንት ክንድ፣ የዐምዶቹም ውፍረት ሁለት ክንድ ነበር። የመግቢያው በር መተላለፊያ በረንዳ፣ ከቤተ መቅደሱ ትይዩ ነው።

10በምሥራቁ በር ግራና ቀኝ መጠናቸው እኩል የሆነ ሦስት ሦስት የዘብ ቤቶች ነበሩ፤ በመካከላቸው ወጣ ወጣ ብለው የሚታዩትም ግንቦች ተመሳሳይና እኩል ነበሩ። 11ከዚያም የበሩን ስፋት ለካ፤ ወርዱ ዐሥር ክንድ፣ ርዝመቱም ዐሥራ ሦስት ክንድ ነበር። 12በእያንዳንዱ ዘብ ቤት ፊት ለፊት ከፍታው አንድ ክንድ የሆነ መከለያ የግንብ ዐጥር አለ፤ የዘብ ቤቶቹም ስፋት እኩል በኩል ስድስት ክንድ ነበር። 13ከዚያም ከዘብ ቤቱ የኋላ ግድግዳ ጀምሮ እስከ ሌላው ጫፍ ድረስ ያለውን የመግቢያ በር ለካ፤ ከአንዱ መከለያ ግድግዳ እስከ ሌላው መከለያ ግድግዳ ያለው ርቀት ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 14በመግቢያው በር ዙሪያ ባሉት ወጣ ወጣ ባሉት ግንቦች ሁሉ ፊት ለፊት ያለውን ቦታ ለካ፤ ስድሳ ክንድም ነበር። የተለካውም ከአደባባዩ40፥14 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ወጣ ያለ ግንብ ይለዋል። ፊት ለፊት እስካለው መተላለፊያ በረንዳ40፥14 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። ድረስ ነበር። 15ከበሩ መግቢያ እስከ መተላለፊያ በረንዳው መጨረሻ ድረስ ያለው ርቀት አምሳ ክንድ ነበር። 16ክፍሎቹ እንደ መተላለፊያ በረንዳዎቹ ከግራና ከቀኝ በኩል ትንንሽ መስኮቶች አሏቸው። በዙሪያው ያሉ መስኮቶች በመግቢያው በር ፊት ለፊት የነበሩ ሲሆን፣ በእያንዳንዱ ክፍል ግራና ቀኝ ግድግዳ ላይ ደግሞ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጾበታል።

የውጩ አደባባይ

17ከዚያም ወደ ውጩ አደባባይ አመጣኝ፤ እዚያም በአደባባዩ ዙሪያ የተሠሩ ክፍሎችና ድንጋይ የተነጠፈበት መመላለሻ አየሁ፤ በመመላለሻውም ዙሪያ ሠላሳ ክፍሎች ነበሩ። 18የታችኛው ንጣፍ ወለል ከመግቢያው በር ጋር ተያይዞ የተሠራ ሲሆን፣ ስፋቱ እንደ በሮቹ ርዝመት መጠን ነበር። 19ከዚያም ከታችኛው መግቢያ በር ፊት ጀምሮ እስከ ውስጠኛው አደባባይ ፊት ድረስ ያለውን ርቀት ለካ፤ በምሥራቅም ሆነ በሰሜን በኩል ያለው ርቀት አንድ መቶ ክንድ ነበር።

የሰሜኑ በር

20ከዚያም በሰሜን ትይዩ ያለውን፣ ወደ ውጩ አደባባይ የሚያመራውን በር ርዝመትና ወርድ ለካ። 21እንደ መጀመሪያው በር ሁሉ ይኸኛውም በየጐኑ ያሉት ሦስት ሦስት የዘብ ቤቶች፣ በየመካከሉ ወጣ ወጣ ያሉ ግንቦችና መተላለፊያ በረንዳዎቹ መጠናቸው እኩል ነበር። ርዝመቱ አምሳ ክንድ፣ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 22መስኮቶቹ፣ መተላለፊያ በረንዳዎቹና የዘንባባ ዛፍ ቅርጾቹ ልካቸው በምሥራቁ በር ካሉት ጋር ተመሳሳይ ነበር። ወደዚያ የሚያመሩ ሰባት ደረጃዎች አሉ፤ መተላለፊያ በረንዳዎቹም ከእነርሱ ጋር ትይዩ ነበር። 23ልክ በምሥራቅ በኩል እንዳለው ሁሉ፣ ከሰሜኑ በር ጋር ትይዩ የሆነ ወደ ውስጠኛው አደባባይ የሚያመራ በር አለ። ከአንዱ በር እስከ ሌላኛው በር ያለውን ለካው፤ ይህም አንድ መቶ ክንድ ነበር።

የደቡቡ በር

24ከዚያም ወደ ደቡብ አቅጣጫ መራኝ፤ እዚያም ፊቱን ወደ ደቡብ ያደረገ በር አየሁ፤ እርሱም የውስጠኛውን ግድግዳና መተላለፊያ በረንዳውን ለካ፤ የእነዚህም መጠን እንደ ሌሎቹ በሮች ነበር። 25የመግቢያው በርና መተላለፊያ በረንዳው እንደ ሌሎቹ ሁሉ በዙሪያው ጠባብ መስኮቶች ነበሩት፤ ርዝመቱ አምሳ ክንድ፤ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 26ከመተላለፊያ በረንዳው ትይዩ የሆኑ ሰባት ደረጃዎች ወደ መግቢያው በር ያመራሉ፤ ወጣ ወጣ ብለው በሚታዩ ግድግዳዎችም ላይ የዘንባባ ቅርጽ አለ። 27ውስጠኛው አደባባይ ደግሞ ከደቡብ ጋር ትይዩ የሆነ በር አለው፤ እርሱም ከዚህ በር አንሥቶ በደቡብ አቅጣጫ እስካለው እስከ ውጭው በር ድረስ ለካው፤ ይህም አንድ መቶ ክንድ ሆነ።

ወደ ውስጠኛው አደባባይ የሚያስገቡ በሮች

28ከዚያም በደቡብ በር በኩል ወደ ውስጠኛው አደባባይ አመጣኝ፤ የደቡብንም በር ለካው፤ መጠኑም እንደ ሌሎቹ በሮች ነበር። 29የዘብ ቤቶቹ፣ በየመካከሉ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦችና መተላለፊያ በረንዳዎቹ መጠናቸው ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር። መግቢያው በርና መተላለፊያ በረንዳዎቹ በዙሪያቸው መስኮቶች ነበሯቸው። ርዝመቱ አምሳ ክንድ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 30በውስጠኛው አደባባይ ዙሪያ ያሉት የመግቢያው በር መተላለፊያ በረንዳዎቹ ርዝመት ሃያ አምስት ክንድ ሲሆን፣ ወርዳቸው ደግሞ አምስት ክንድ ነበር። 31መተላለፊያ በረንዳው ከውጭው አደባባይ ጋር ትይዩ ነው፤ የዘንባባ ዛፎች በዐምዶቹ ላይ ተቀርጸዋል፤ እስከ መግቢያው ድረስም ስምንት ደረጃዎች ነበሩት።

32ከዚያም በምሥራቅ በኩል ወደ ውስጠኛው አደባባይ አመጣኝ፤ መግቢያ በሩንም ለካው፤ መጠኑም ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር። 33የዘብ ቤቶቹ፣ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦችና መተላለፊያ በረንዳዎቹ መጠናቸው ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር፤ መግቢያው በርና መተላለፊያ በረንዳው ዙሪያውን መስኮቶች ነበሩት፤ የዚህም ርዝመቱ አምሳ ክንድ፣ ወርዱ ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 34መተላለፊያ በረንዳው ከውጩ አደባባይ ትይዩ ነው፤ በዐምዶቹ ላይ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጿል፤ እስከ መግቢያ ድረስም ስምንት ደረጃዎች ነበሩት።

35ከዚያም ወደ ሰሜን በር አመጣኝ፤ ለካውም፤ መጠኑም ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር። 36የዘብ ቤቶቹ፣ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦቹና መተላለፊያ በረንዳው መጠናቸው ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ነበር፤ በዙሪያውም መስኮቶች ነበሩት። የዚህም ርዝመቱ አምሳ ክንድ ወርዱም ሃያ አምስት ክንድ ነበር። 37መተላለፊያ በረንዳው40፥37 ሰብዓ ሊቃናቱም (በተጨማሪ 31 እና 34 ይመ) እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን መቃኖች ይላል። ከውጩ አደባባይ ትይዩ ነው፤ በዐምዶቹም ላይ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጿል፤ እስከ መግቢያው ድረስም ስምንት ደረጃዎች ነበሩት።

መሥዋዕት የሚዘጋጅባቸው ክፍሎች

38በእያንዳንዱ የውስጥ መግቢያ በር መተላለፊያ በረንዳ አጠገብ የሚቃጠል መሥዋዕት የሚታጠብበት በር ያለው ክፍል አለ። 39በመግቢያው በር ላይ ባለው መተላለፊያ በረንዳው ሥር በግራና በቀኝ የሚቃጠል መሥዋዕት፣ የኀጢአትና የበደል መሥዋዕት የሚታረዱበት ሁለት ሁለት ጠረጴዛዎች አሉ። 40ከመግቢያው በር ላይ ባለው መተላለፊያ በረንዳ በስተ ውጭው ግንብ ወደ ሰሜን በር መግቢያ ላይ ባሉት ደረጃዎች አጠገብ ከግራና ከቀኝ ሁለት ሁለት ጠረጴዛዎች ይገኛሉ። 41ስለዚህ በአንዱ በር በኩል አራት፣ በሌላውም በኩል አራት ጠረጴዛዎች፤ መሥዋዕቱ የሚታረድባቸው በድምሩ ስምንት ጠረጴዛዎች አሉ ማለት ነው። 42ለሚቃጠለው መሥዋዕት መገልገያ የሆኑ፣ ከተጠረበ ድንጋይ የተሠሩ አራት ጠረጴዛዎች ነበሩ፤ የእያንዳንዳቸው ርዝመት፣ ወርድና ቁመት አንድ ክንድ ተኩል ነበር፤ በእነዚህም ላይ ለሚቃጠለው መሥዋዕትና ለሌላውም መሥዋዕት ማረጃ የሚሆኑ መሣሪያዎች ይቀመጡባቸው ነበር። 43እንዲሁም አንዳንድ ስንዝር የሚሆኑ ሁለት ጣት ያላቸው ሜንጦዎች በግንቡ ዙሪያ ተንጠልጥለው ነበር፤ ጠረጴዛዎቹም የመሥዋዕቱ ሥጋ ማስቀመጫ ነበሩ።

ለካህናት የተመደቡ ክፍሎች

44በውስጠኛው አደባባይ፣ ከውስጠኛው በር ውጭ፣ ሁለት ክፍሎች ነበሩ፤ አንዱ40፥44 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን የመዘመራን ክፍሎች ነበሩ ይላል። በደቡብ40፥44 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን በምሥራቅ ይላል። ትይዩ በሰሜን በር በኩል ሲሆን፣ ሌላው በሰሜን ትይዩ በደቡብ በር በኩል ነበር። 45እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “በደቡብ ትይዩ ያለው ክፍል በቤተ መቅደስ ውስጥ ለሚያገለግሉ ካህናት ሲሆን፣ 46በሰሜን ትይዩ ያለው ክፍል ደግሞ በመሠዊያው ላይ ለሚያገለግሉ ካህናት ነው። እነዚህም የሳዶቅ ልጆች ሲሆኑ፣ በእግዚአብሔር ፊት ቀርበው ማገልገል የሚችሉ ሌዋውያን እነርሱ ብቻ ናቸው።”

47ከዚያም አደባባዩን ለካው፤ ርዝመቱ አንድ መቶ ክንድ፣ ወርዱ መቶ ክንድ እኩል በእኩል ባለ አራት ማእዘን ነበር። መሠዊያውም በቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ነበር።

ቤተ መቅደሱ

48ወደ ቤተ መቅደሱም መተላለፊያ በረንዳ አመጣኝ፤ የመተላለፊያ በረንዳዎቹን ዐምዶች ለካ፤ በአንዱ በኩል አምስት ክንድ በሌላውም እንዲሁ አምስት ክንድ ነበር። የመግቢያው በር ርዝመት ዐሥራ አራት ክንድ ሲሆን፣ ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች ስፋት በአንዱ በኩል ሦስት ክንድ፣ በሌላውም እንዲሁ ሦስት ክንድ ነበሩ።40፥48 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ወጣ ወጣ ያሉት ግንቦች መግቢያ… ነበሩ ይላል። 49የመተላለፊያው በረንዳ ርዝመት ሃያ ክንድ፣ ከፊት እስከ ኋላ ያለውም ወርድ ዐሥራ ሁለት40፥49 ሰብዓ ሊቃናቱም እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ዐሥራ አንድ ይላል። ክንድ ነበር። ወደ ቤተ መቅደሱም የሚያደርሱ ዐሥር ደረጃዎች የነበሩ ሲሆን፣ በየዐምዱም ጐንና ጐን ምሰሶዎች ነበሩ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以西结书 40:1-49

新圣殿的异象

1在我们被掳的第二十五年,就是耶路撒冷沦陷的第十四年一月十日,耶和华的灵降在我身上。 2在异象中上帝把我带到以色列的一座高山上,山的南面仿佛有一座城。 3祂把我带到那里。城的入口站着一个面色如铜的人,手中拿着一条麻绳和一根量竿。 4那人对我说:“人子啊,你要留心用眼看,专心用耳听,注意我指示你的一切,因为我带你来这里正是为了要指示你。你要把所见到的一切告诉以色列人。”

外院的门

5我看见殿的四周有墙,那人拿了一根三米长的量竿测量这墙,量出墙厚一竿,高一竿。

6然后,他带我到殿的东门,走上石阶,来到门口。他量了门洞,宽一竿。 7门内有守卫室,长度和宽度都是一竿。室与室之间相距二点二米,通往圣殿的内门洞宽一竿, 8通往圣殿的门廊宽度也是一竿, 9连墙柱在内共四点二米宽,墙柱宽一点零五米。 10东门内共有六间守卫室,每边三间,大小面积都是一样,两边的墙尺寸也相同。 11通道尽头有一道门廊,宽五米,长六点五米。 12两边守卫室前面的矮墙高五十厘米,守卫室都是三米宽的正方形。 13他又量门廊的宽度,即这边守卫室的屋顶到对面守卫室的屋顶,是十二点五米。 14他从门口的墙量到外院的墙柱,是三十米。 15由门口到通道尽头的内廊共二十五米, 16守卫室、墙柱上和门廊周围都有格子窗,墙柱上刻着棕树。

外院

17他带我到外院,外院靠墙的四周是铺石地,上面共有三十间厢房。 18铺石地在门口的两边,比内院低,宽度与入口的长度一样。 19他从外院的内门口量到内院的门口,距离是五十米。

北门

20他又量了外院的北门, 21通道两边各有三间守卫室,墙和廊子长度和宽度跟东门一样,分别是二十五米和十二点五米。 22它的窗户、门廊、墙柱上雕刻的棕树都和东门的尺寸相同。登上七级石阶便到达门口,通道的尽头是门廊。 23内院的北门与外院的北门相对,正如它的东门和外院的东门相对,门与门之间的距离是五十米。

南门

24他又带我到南门,量了墙柱和门廊,都与其他门的尺寸相同, 25通道与门廊四周的窗户也和其他的门一样,通道长二十五米,宽十二点五米。 26登上七级石阶便到门廊,两边的墙柱也同样刻着棕树。 27内院也有南门,与外院南门之间的距离是五十米。

内院的门

28他带我从南门走进内院,量了南门,跟其他门的尺寸一样。 29守卫室、墙柱和门廊都和其他的尺寸一样,通道与门廊四周有窗户,通道长二十五米,宽十二点五米。 30内院周围的门廊都是长十二点五米,宽二点五米。 31这些门廊靠外院,两边的墙柱刻着棕树,上去的石阶共有八级。

32他又带我从东门进入内院,量了东门,跟其他门的尺寸一样, 33守卫室、墙柱、门廊和其他门的尺寸一样,通道与门廊的四周也有窗户,通道长二十五米,宽十二点五米。 34门廊靠外院,两边的墙柱刻着棕树,那里的石阶共有八级。

35他又带我到北门,量了北门,跟其他门的尺寸一样。 36守卫室、墙柱、门廊和其他门的尺寸一样,通道长二十五米,宽十二点五米,四周有窗户。 37门廊靠外院,两边的墙柱刻着棕树,那里的石阶共有八级。

厢房

38门口的墙柱旁边有一个房间,供祭司洗燔祭牲。 39门廊两边各有两张用来屠宰燔祭牲、赎罪祭牲和赎过祭牲的桌子。 40内院北门的两边各有两张桌子, 41即里外各有四张桌子,共八张,供祭司屠宰祭牲之用。 42另有四张用石头凿成的桌子用来预备燔祭牲,屠宰燔祭牲及其他祭牲的器具都放在桌上。桌子长宽各七十五厘米,高五十厘米。 43廊内四周挂着七点五厘米长的双钩。桌上放着祭肉。

44在内院有歌乐手用的厢房,一间向南,在北门旁,一间向北,在南门旁。 45他对我说:“向南的厢房是给殿内供职的祭司用的, 46向北的厢房是给坛前供职的祭司用的。他们都是撒督的子孙,利未的后裔,在耶和华面前专职事奉。” 47他量了殿前的院子,是五十米宽的正方形,祭坛在殿的前面。

圣殿

48他带我来到殿前通往圣所的门廊,量了两旁的墙柱,各二点五米宽,门两边的墙一点五米厚, 49门廊长十米,宽四点九米。上门廊靠近墙柱的石级两旁各有一根柱子。