ሕዝቅኤል 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 4:1-17

የኢየሩሳሌም መከበብ ምሳሌ

1“አንተ፣ የሰው ልጅ ሆይ፤ አንድ የሸክላ ጡብ ወስደህ ከፊት ለፊትህ አስቀምጥ፤ የኢየሩሳሌምን ከተማ ካርታ ሥራበት። 2ከዚያም በወታደር እንደሚከበብ ክበባት፤ ምሽግ ሥራባት፤ ዐፈር ደልድልባት፤ ጦር ሰፈሮችን ቀብቅብባት፤ ቅጥር መደርመሻ ግንዶችንም በዙሪያዋ አስቀምጥባት። 3የብረት ምጣድ ወስደህ በአንተና በከተማዪቱ መካከል እንደ ብረት ቅጥር አቁመው፤ ፊትህንም ወደ እርሷ አዙር፤ የተከበበች ትሆናለች፤ አንተም ትከብባታለህ። ይህም ለእስራኤል ቤት ምልክት ይሆናል።

4“አንተ በግራ ጐንህ ተኛ፤ የእስራኤልም ቤት ኀጢአት በአንተ ላይ4፥4 ወይም በአንተ በኩል ይሁን ይሁን፤ በዚህ ጐንህ በተኛህበት ቀን ቍጥር ኀጢአታቸውን ትሸከማለህ። 5እነርሱ ኀጢአት ባደረጉባቸው ዓመታት መጠን የቀን ቍጥር መድቤብሃለሁ። ስለዚህ ሦስት መቶ ዘጠና ቀን የእስራኤልን ቤት ኀጢአት ትሸከማለህ።

6“ይህን ከፈጸምህ በኋላ ደግሞ በቀኝ ጐንህ ተኝተህ የይሁዳን ቤት ኀጢአት ትሸከማለህ፤ ለእያንዳንዱ ዓመት አንድ አንድ ቀን በማድረግ አርባ ቀን መድቤብሃለሁ። 7ፊትህን ወደ ኢየሩሳሌም ከበባ ታዞራለህ፣ በዕራቍት ክንድህ ትንቢት ተናገርባት። 8የከበባህን ወራት እስክትፈጽም ድረስ ከአንዱ ጐን ወደ ሌላው መገላበጥ እንዳትችል በገመድ አስርሃለሁ።

9“ስንዴና ገብስ፣ ባቄላና ምስር እንዲሁም ዘንጋዳና ጠመዥ ወስደህ በአንድ ሸክላ ውስጥ አስቀምጥ፤ ከዚያም ለራስህ እንጀራ ጋግር፤ ሦስት መቶ ዘጠና ቀን በጐንህ በምትተኛበት ጊዜ ትመገበዋለህ። 10በየቀኑ የምትበላውን እህል ሃያ ሃያ ሰቅል መዝነህ አስቀምጥ፤ በተወሰነ ጊዜ ትበላዋለህ፤ 11የምትጠጣውንም ውሃ አንድ4፥11 አንድ ስድስተኛ (1/6ኛ) ኢን ግማሽ ሊትር ያህል ነው። ስድስተኛ ኢን ለክተህ አስቀምጥ፤ በተወሰነ ጊዜ ትጠጣዋለህ። 12የገብስ ዕንጎቻ እንደምትበላ አድርገህ ትበላለህ፤ የሰውንም ዐይነ ምድር አንድደህ በሕዝብ ፊት ጋግረው።” 13እግዚአብሔርም፣ “በዚህ ሁኔታ የእስራኤል ሕዝብ እነርሱን በምበትንበት በአሕዛብ መካከል ርኩስ ምግብ ይበላሉ” አለ።

14እኔም፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ወይኔ! ከቶ ረክሼ አላውቅም፤ ከልጅነቴ ጀምሮ እስከ ዛሬ ጥንብ ወይም አውሬ የጣለውን በልቼ አላውቅም፤ ርኩስ ሥጋም በአፌ አልገባም” አልሁ።

15እርሱም፣ “መልካም ነው፤ በሰው ዐይነ ምድር ሳይሆን፤ እንጀራህን በኩበት እንድትጋግር ፈቅጄልሃለሁ” አለኝ።

16ደግሞም እንዲህ አለኝ፤ “የሰው ልጅ ሆይ፤ የኢየሩሳሌምን የምግብ ምንጭ አደርቃለሁ፤ ሕዝቡም የተወሰነ ምግብ በጭንቀት ይበላል፤ የተመጠነ ውሃም በሥጋት ይጠጣል። 17የምግብና የውሃ ዕጥረት ስለሚኖር፣ እርስ በርስ ሲተያዩ ይደነግጣሉ፤ ከኀጢአታቸውም የተነሣ4፥17 ወይም በኀጢአታቸው መንምነው ይጠፋሉ መንምነው ይጠፋሉ።

Thai New Contemporary Bible

เอเสเคียล 4:1-17

สัญลักษณ์ของการล้อมกรุงเยรูซาเล็ม

1“บัดนี้ บุตรมนุษย์เอ๋ย จงเอาดินเหนียวแผ่นหนึ่งมาวางไว้ตรงหน้าเจ้า และวาดกรุงเยรูซาเล็มลงบนดินนั้น 2แล้วจงล้อมรอบแผ่นดินเหนียวนั้นด้วยอุปกรณ์ที่ใช้ล้อมเมือง ก่อเชิงเทิน ตั้งค่ายประชิดเมือง และวางเครื่องกระทุ้งโดยรอบ 3แล้วเอากระทะเหล็กมาตั้งเป็นเสมือนกำแพงเหล็กกั้นระหว่างเจ้ากับตัวเมือง จงหันหน้าเข้าหาเมืองนั้น เมืองนั้นจะตกอยู่ในวงล้อมของเจ้า นี่เป็นหมายสำคัญแก่พงศ์พันธุ์อิสราเอล

4“จากนั้นจงนอนตะแคงซ้าย แบกรับบาปของพงศ์พันธุ์อิสราเอลไว้บนเจ้า4:4 หรือข้างตัวเจ้าตลอดจำนวนวันที่เจ้านอนตะแคง 5เรากำหนดวันให้เจ้าตามจำนวนปีของความบาปของพวกเขา ฉะนั้นเจ้าจะแบกบาปของ พงศ์พันธุ์อิสราเอลอยู่ 390 วัน

6“เมื่อครบกำหนดแล้ว เจ้าต้องนอนลงอีก คราวนี้ให้นอนตะแคงขวาและแบกรับบาปของพงศ์พันธุ์ยูดาห์ เรากำหนดไว้สี่สิบวัน หนึ่งวันสำหรับหนึ่งปี 7จงหันหน้าเข้าหาเครื่องล้อมกรุงเยรูซาเล็ม จงชูแขนอันเปลือยเปล่าใส่กรุงนั้นแล้วพยากรณ์ 8เราจะเอาเชือกมัดเจ้าไว้ เพื่อเจ้าจะพลิกตัวไม่ได้จนกว่าจะครบกำหนดวันล้อมเมือง

9“จงเอาข้าวสาลี ข้าวบาร์เลย์ ถั่วและถั่วแดง ข้าวฟ่าง และข้าวสแปลต์เก็บไว้ในโอ่งเพื่อใช้ทำขนมปังให้ตนเอง ซึ่งเจ้าจะต้องกินระหว่างที่เจ้านอนตะแคงตลอด 390 วัน 10จงตวงอาหารออกมาวันละประมาณ 200 กรัม4:10 ภาษาฮีบรูว่า20 เชเขลและกินอาหารนี้ตามมื้อที่กำหนดในแต่ละวัน 11และจงตวงน้ำประมาณ 0.6 ลิตร4:11 ภาษาฮีบรูว่าหนึ่งในหกฮินดื่มตามเวลาที่กำหนด 12จงกินอาหารนี้เหมือนกินขนมข้าวบาร์เลย์ จงปิ้งกินต่อหน้าผู้คน โดยใช้อุจจาระมนุษย์เป็นเชื้อเพลิง” 13องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “ชนชาติอิสราเอลจะกินอาหารที่เป็นมลทินเช่นนี้ท่ามกลางประชาชาติต่างๆ ซึ่งเราจะขับไล่เขาไปนั้น”

14แล้วข้าพเจ้าจึงกราบทูลว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต อย่าให้เป็นเช่นนั้นเลย! ข้าพระองค์ไม่เคยปล่อยตัวเป็นมลทินเลย ตั้งแต่เด็กมาจนบัดนี้ข้าพระองค์ไม่เคยรับประทานสัตว์ใดที่ตายเอง หรือที่ถูกสัตว์ป่าขย้ำ ไม่เคยมีเนื้อสัตว์มลทินใดๆ เข้าปากข้าพระองค์เลย”

15พระองค์ตรัสว่า “เอาเถิด เราอนุญาตให้เจ้าปิ้งขนมปังโดยใช้มูลโคแทนอุจจาระมนุษย์”

16แล้วพระองค์ตรัสกับข้าพเจ้าว่า “บุตรมนุษย์เอ๋ย เราจะตัดแหล่งเสบียงในเยรูซาเล็ม ผู้คนจะกินอาหารปันส่วนด้วยความหวาดวิตก และดื่มน้ำปันส่วนด้วยความสิ้นหวัง 17เพราะน้ำและอาหารจะหายาก พวกเขาจะมองตากันด้วยความอกสั่นขวัญแขวน และจะซูบซีดไปเพราะ4:17 หรือในบาปของตน