ሕዝቅኤል 38 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 38:1-23

በጎግ ላይ የተነገረ ትንቢት

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን በማጎግ ምድር በሚገኘው፣ በሞሳሕና በቶቤል ዋና አለቃ38፥2 ወይም የሮሽ አለቃ በጎግ ላይ አድርግ፤ በእርሱ ላይ ትንቢት ተናገር፤ 3እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የሞሳሕና የቶቤል ዋና አለቃ38፥3 ወይም የሮሽ አለቃ ጎግ ጎግ ሆይ፤ ተነሥቼብሃለሁ። 4ወደ ኋላ እመልስሃለሁ፤ መንጋጋህ ውስጥ መንጠቆ አስገብቼ ከመላው ሰራዊትህ ጋር፣ ፈረሶችህን፣ ፈረሰኞችህን ከነሙሉ ትጥቃቸው፣ ትልቅና ትንሽ ሰይፍ የያዙትን ሁሉ፣ ሰይፋቸውንም የወለወሉትን ሁሉ አስወጣለሁ። 5ጋሻ የያዙና የራስ ቍር የደፉት ሁሉ፣ ፋርስ፣ ኢትዮጵያና ፉጥ ከእነርሱ ጋር ይሆናሉ። 6ደግሞም ጎሜርን ከወታደሮቹ ጋር፣ ራቅ ካለው ሰሜንም የቴርጋማን ቤት ከወታደሮቹ ሁሉ ጋር ብዙ ሕዝቦችን ከአንተ ጋር አስወጣለሁ።”

7“ ‘አንተና በዙሪያህ የተሰበሰቡት ሁሉ ተነሡ፤ ተዘጋጁ፤ አንተም መሪያቸው ሁን። 8ከብዙ ቀን በኋላ ለጦርነት ትጠራለህ። በኋለኛው ዘመንም ከጦርነት ያገገመችውን፣ ሕዝቧ ከአያሌ አሕዛብ መካከል ወጥቶ የተሰበሰበውን፣ ለብዙ ጊዜ ባድማ በነበረው በእስራኤል ተራሮች ላይ የሰፈረውን ወገን ትወርራለህ። ከሕዝቦች መካከል ወጥተው፣ አሁን ሁሉም በሰላም ይኖራሉ። 9አንተና ወታደሮችህ ሁሉ፣ ከአንተም ጋር ያሉት ብዙ ሕዝቦች እንደ ማዕበል ትወጣላችሁ፤ ምድርን እንደሚሸፍን ደመናም ትሆናላችሁ።

10“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በዚያ ቀን ሐሳብ ወደ አእምሮህ ይመጣል፤ ክፋትንም ታውጠነጥናለህ። 11እንዲህም ትላለህ፤ “ቅጥር የሌላቸውን መንደሮች ምድር እወራለሁ፤ ሁሉም ያለ ቅጥር፣ ያለ በርና ያለ ብረት መወርወሪያ የሚኖረውን፣ ሰላማዊና ያለ ሥጋት የተቀመጠውን ሕዝብ እወጋለሁ፤ 12እዘርፋለሁ፤ እነጥቃለሁ፤ እንዲሁም ከአሕዛብ ተሰባስቦ እንደ ገና በሰፈረው፣ በከብትና በሸቀጥ በከበረው፣ በምድሪቱም መካከል በሚኖረው ሕዝብ ላይ እጄን አነሣለሁ።” 13ሳባና ድዳን፣ የተርሴስ ነጋዴዎችና መንደሮቿም ሁሉ38፥13 ወይም ጠንካራ መንደሮቿ እንዲህ ይሉሃል፤ “ልትዘርፍ መጣህን? ሰራዊትህን ያሰባሰብኸው ለመበዝበዝ፣ ወርቅና ብሩን አጋብሶ ለመሄድ፣ ከብቱንና ሸቀጡን ለመውሰድ፣ ብዙ ምርኮ ይዞ ለመመለስ ነውን?” ’

14“ስለዚህ የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር፤ ጎግንም እንዲህ በለው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በዚያ ቀን ሕዝቤ እስራኤል በሰላም መቀመጡን ዐውቀህ አትንቀሳቀስምን? 15በስተ ሰሜን ርቆ ከሚገኘው ቦታ ትመጣለህ፤ አንተና ከአንተም ጋር ብዙ ሕዝቦች፣ እጅግ ታላቅ ኀያል ሰራዊትም በፈረሶች ላይ ሆናችሁ ትመጣላችሁ። 16ምድርን እንደሚሸፍን ደመና ሆነህ በሕዝቤ በእስራኤል ላይ ትወጣለህ። ጎግ ሆይ፤ በፊታቸው ቅድስናዬን ስገልጥ ሕዝቦች እኔን ያውቁ ዘንድ በኋለኛው ዘመን በምድሬ ላይ አመጣሃለሁ።”

17“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “በቀደመው ዘመን በባሪያዎቼ በእስራኤል ነቢያት ስለ እርሱ የተናገርሁለት ያ ሰው አንተ አይደለህምን? በዚያን ወቅት አንተን በእነርሱ ላይ እንደማመጣባቸው ለብዙ ዓመታት ትንቢት ተናገሩ።” 18በዚያን ጊዜ እንዲህ ይሆናል፤ “ጎግ የእስራኤልን ምድር ሲወጋ፣ ብርቱ ቍጣዬ ይነሣሣል፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር19በዚያን ጊዜ በቅናቴና በሚያስፈራው ቍጣዬ በእስራኤል ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ይሆናል ብዬ ተናግሬአለሁ። 20የባሕር ዓሦች፣ የሰማይ ወፎች፣ የምድር አራዊት፣ በምድር ላይ የሚሳብ ማንኛውም ፍጡር፣ እንዲሁም በምድር ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ፣ በፊቴ ይንቀጠቀጣሉ፤ ተራሮች ይገለባበጣሉ፤ ገደሎች ይናዳሉ፤ 21በተራሮቼም ሁሉ በጎግ ላይ ሰይፍ እጠራለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ የእያንዳንዱም ሰው ሰይፍ በወንድሙ ላይ ያርፋል። 22በቸነፈርና በደም መፋሰስ እፈርድበታለሁ፤ የዝናብ ዶፍ፣ የበረዶ ድንጋይ፣ የሚያቃጥል ድኝ፣ በእርሱና በወታደሮቹ፣ ከእርሱም ጋር ባሉት ሕዝቦች ላይ አወርዳለሁ። 23በዚህም ታላቅነቴንና ቅድስናዬን አሳያለሁ፤ በብዙ ሕዝቦች ፊት ራሴን አሳውቃለሁ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።” ’

Thai New Contemporary Bible

เอเสเคียล 38:1-23

คำพยากรณ์กล่าวโทษโกก

1พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าว่า 2“บุตรมนุษย์เอ๋ย จงมุ่งหน้าประณามโกกแห่งดินแดนมาโกก เจ้านายคนสำคัญแห่ง38:2 หรือเจ้านายแห่งโรชเมเชคและทูบัล จงพยากรณ์กล่าวโทษเขา 3และกล่าวว่า ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า โกกเจ้านายคนสำคัญแห่งเมเชค38:3 หรือโกกเจ้านายแห่งโรช เมเชคและทูบัลเอ๋ย เราเป็นศัตรูกับเจ้า 4เราจะทำให้เจ้าหันกลับ จะเอาเบ็ดเกี่ยวขากรรไกรของเจ้า และลากเจ้าออกไปพร้อมกองทัพทั้งปวงของเจ้าคือม้าและพลม้าซึ่งมีอาวุธครบมือ ทั้งกองกำลังมหึมาที่ถือโล่น้อยใหญ่และทุกคนที่กวัดแกว่งดาบ 5เปอร์เซีย คูช38:5 คือ ตอนบนของลุ่มแม่น้ำไนล์ และพูตจะไปด้วย ทุกคนล้วนถือโล่และสวมหมวกเกราะ 6พร้อมทั้งโกเมอร์กับทหารทั้งปวง และทั้งเบธโทการมาห์จากภาคเหนืออันไกลโพ้นกับทหารทั้งปวง มีหลายประชาชาติที่ร่วมกับเจ้า

7“ ‘เจ้ากับกองกำลังทั้งปวงที่ชุมนุมกันรอบเจ้า จงเตรียมพร้อมและรับคำสั่งเกี่ยวกับพวกเขา 8หลายวันผ่านไปเจ้าจะถูกเรียกมารบ อีกหลายปีข้างหน้าเจ้าจะบุกดินแดนซึ่งว่างเว้นจากสงคราม ซึ่งประชากรดินแดนนั้นถูกรวบรวมมาจากหลายชาติสู่ภูเขาต่างๆ ของอิสราเอลซึ่งถูกทิ้งร้างมานาน พวกเขาถูกพามาจากชาติต่างๆ บัดนี้เขาทั้งหมดอาศัยอยู่อย่างปลอดภัย 9เจ้ากับกองทหารทั้งปวงและชนหลายชาติที่ร่วมกับเจ้าจะยกพลขึ้นไปรุกกระหน่ำอย่างพายุ เจ้าจะเป็นเหมือนเมฆปกคลุมดินแดนนั้น

10“ ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า ในวันนั้นความคิดจะแวบเข้ามาในใจของเจ้าและเจ้าจะคิดก่อการร้าย 11เจ้าจะกล่าวว่า “เราจะบุกดินแดนซึ่งหมู่บ้านต่างๆ ไม่มีปราการ เราจะโจมตีชนชาติซึ่งรักสงบและไม่ระแวงภัย เขาทั้งปวงอาศัยอยู่โดยปราศจากกำแพง ประตู และดาลประตู 12เราจะปล้นและริบข้าวของ และรบกับที่ปรักหักพังซึ่งบัดนี้มีคนอยู่อาศัย และสู้กับประชากรที่รวบรวมมาจากชาติต่างๆ ซึ่งร่ำรวยด้วยฝูงสัตว์และผลผลิตต่างๆ ที่อาศัยอยู่ใจกลางดินแดนนั้น” 13เชบากับเดดาน และบรรดาพ่อค้าวาณิชของทารชิชและหมู่บ้านทั้งหมดของมัน38:13 หรือสิงห์ที่เข้มแข็งของมันจะกล่าวแก่เจ้าว่า “ท่านมาปล้นชิงหรือ ท่านระดมพลมาริบข้าวของหรือ มาขนเงินทอง ริบฝูงสัตว์ ผลผลิตต่างๆ และยึดของเชลยไปมากมายหรือ?” ’

14“ฉะนั้นบุตรมนุษย์เอ๋ย จงพยากรณ์และกล่าวแก่โกกว่า ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า ในวันนั้นเมื่ออิสราเอลประชากรของเราอาศัยอยู่อย่างสงบ เจ้าจะไม่สังเกตเห็นหรือ? 15เจ้าจะมาจากถิ่นของเจ้าในภาคเหนือไกลโพ้น ทั้งเจ้าและชาติต่างๆ ที่ร่วมกับเจ้า ทุกคนล้วนขี่ม้ามาเป็นกองกำลังยิ่งใหญ่และเป็นกองทัพเข้มแข็งยิ่งนัก 16เจ้าจะบุกมาสู้กับอิสราเอลประชากรของเราเหมือนเมฆปกคลุมดินแดน โกกเอ๋ย ในกาลข้างหน้าเราจะนำเจ้ามาสู้รบกับดินแดนของเรา เพื่อชนชาติทั้งหลายจะรู้จักเราเมื่อเราสำแดงความบริสุทธิ์ของเราผ่านทางเจ้าต่อหน้าต่อตาพวกเขา

17“ ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เจ้าเป็นผู้นั้นไม่ใช่หรือที่เรากล่าวถึงในสมัยก่อนผ่านทางผู้รับใช้ของเรา คือบรรดาผู้เผยพระวจนะของอิสราเอล? ในเวลานั้นพวกเขาพยากรณ์อยู่หลายปีว่าเราจะนำเจ้ามาสู้กับพวกเขา 18ในวันนั้นจะเกิดเหตุการณ์ดังนี้คือ เมื่อโกกโจมตีดินแดนอิสราเอล เราจะบันดาลโทสะรุนแรง พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น 19โดยความร้อนใจและความเดือดดาล เราขอประกาศว่าเมื่อถึงเวลานั้น จะเกิดแผ่นดินไหวอย่างร้ายแรงในดินแดนอิสราเอล 20ปลาในทะเล นกในอากาศ สัตว์บก สัตว์เลื้อยคลานทุกชนิดและมนุษย์บนพื้นผิวโลกจะสั่นสะท้านต่อหน้าเรา ภูเขาทั้งหลายจะคว่ำทลาย หน้าผาแตกเป็นเสี่ยงๆ และกำแพงทุกแห่งทลายราบกับพื้น 21เราจะเกณฑ์ดาบเล่มหนึ่งมาสู้กับโกกบนภูเขาทุกแห่งของเรา พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น ดาบของทุกคนจะฟาดฟันกับพี่น้องของตน 22เราจะลงโทษเขาด้วยโรคระบาดและการนองเลือด เราจะเทฝนห่าใหญ่ ลูกเห็บ และไฟกำมะถันลงใส่โกกและกองทหารของเขาตลอดจนชนชาติต่างๆ ที่ร่วมกับเขา 23เราจะแสดงความยิ่งใหญ่และความบริสุทธิ์ของเราเช่นนี้ และเราจะสำแดงตนให้เป็นที่รู้จักต่อหน้าต่อตาชนชาติทั้งหลาย เมื่อนั้นพวกเขาจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์’