ሕዝቅኤል 35 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 35:1-15

በኤዶም ላይ የተነገረ ትንቢት

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን ወደ ሴይር ተራራ አዙር፤ ትንቢትም ተናገርበት፤ 3እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የሴይር ተራራ ሆይ፤ በአንተ ላይ ተነሥቻለሁ፤ እጄን በአንተ ላይ እዘረጋለሁ፤ ባድማና ጠፍ አደርግሃለሁ። 4ከተሞችህን ፍርስራሽ አደርጋቸዋለሁ፤ ባድማ ትሆናለህ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃለህ።

5“ ‘እስራኤላውያን ቅጣታቸው እጅግ መራራ ከሆነ ደረጃ ላይ ደርሶ ፍዳቸውን በሚቀበሉበት ጊዜ፣ የጥንቱን ቂም ቋጥረህ ለሰይፍ ስለ ዳረግሃቸው፤ 6በሕያውነቴ እምላለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ለደም ማፍሰስ አሳልፌ እሰጥሃለሁ፤ እርሱም ያሳድድሃል። ደም ማፍሰስን ስላልጠላህ፣ ደም ማፍሰስ ያሳድድሃል። 7የሴይርን ተራራ ባድማና ጠፍ አደርጋለሁ፤ በእርሱም ላይ የሚወጡትንና የሚወርዱትን አስቀራለሁ። 8ተራሮችህን በሬሳ እሞላለሁ፤ በሰይፍ የተገደሉት ሁሉ በተራሮችህ፣ በሸለቆዎችህና በውሃ መውረጃዎችህ ሁሉ ላይ ይወድቃሉ። 9ለዘላለም ባድማ አደርግሃለሁ፤ ከተሞችህ መኖሪያ አይሆኑም። ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።

10“ ‘እኔ እግዚአብሔር በዚያ እያለሁ፣ “እነዚህ ሁለት ሕዝቦችና ሁለት አገሮች የእኛ ይሆናሉ፤ እኛም እንወርሳቸዋለን።” ብለሃልና፤ 11ስለዚህ በሕያውነቴ እምላለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከጥላቻችሁ የተነሣ በእነርሱ ላይ በገለጣችሁት ቍጣና ቅናት ልክ እፈርድባችኋለሁ፤ በእናንተም ላይ በምፈርድበት ጊዜ፣ ማንነቴ በእነርሱ መካከል እንዲታወቅ አደርጋለሁ። 12ከዚያም ስለ እስራኤል ተራሮች፣ “ጠፍ ሆነዋል፤ ቦጫጭቀን እንድንበላቸው ለእኛ ተሰጥተዋል” ብለህ በንቀት የተናገርኸውን እኔ እግዚአብሔር እንደ ሰማሁ በዚያን ጊዜ ታውቃለህ። 13በእኔ ላይ ታብየሃል፤ በድፍረትም በእኔ ላይ ተናግረሃል፤ እኔም ሰምቼዋለሁ። 14ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ መላዪቷ ምድር በምትደሰትበት ጊዜ፣ አንተን ባድማ አደርግሃለሁ። 15የእስራኤል ቤት ርስት ባድማ በሆነች ጊዜ ስለ ተደሰትህ፣ እኔም እንዲሁ አደርግብሃለሁ። የሴይር ተራራ ሆይ፤ አንተና መላዋ ኤዶም ባድማ ትሆናላችሁ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以西結書 35:1-15

預言以東受懲罰

1耶和華對我說: 2「人子啊,你要面向西珥山,發預言斥責它, 3告訴它,主耶和華這樣說,『西珥山啊,我要與你為敵,伸手攻擊你,使你荒涼不堪。 4我要使你的城邑淪為廢墟,一片荒涼,這樣你就知道我是耶和華。 5因為你永懷仇恨,在以色列人遭遇危難、因罪惡受盡刑罰的時候,把他們交在刀下。 6所以主耶和華說,我憑我的永恆起誓,你既然不憎恨殺人流血之事,殺人流血之事必臨到你。 7我要使西珥山荒涼不堪,消滅一切來往此地的人, 8我要使喪身刀下的人遍佈你的高山、丘陵、山谷和溪流。 9我要使你永遠荒廢,你的城邑杳無人跡,這樣你就知道我是耶和華。

10「『因為你曾說,猶大以色列必歸我,即使上帝在那裡,我們也要吞併他們。 11所以主耶和華說,我憑我的永恆起誓,你憎恨他們,滿腹怒氣和嫉妒,我也必這樣對待你。我審判你的時候,以色列人就會認識我。 12那時,你必知道我耶和華聽見了你譭謗以色列山嶺的一切話,你說,這些山嶺荒廢了,歸我們所有了。 13你妄自尊大,肆意譭謗我,我都聽見了。 14主耶和華這樣說,普天下歡樂的時候,我要使你荒涼。 15你既因以色列的荒涼而幸災樂禍,我要讓你遭受同樣的下場。西珥山啊,你和以東都要荒涼。這樣,你們就知道我是耶和華。』