ሕዝቅኤል 30 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 30:1-26

ስለ ግብፅ የወጣ ሙሾ

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር፤ እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ዋይ! በል፤ እንዲህም በል፤

“ወዮ ለዚያ ቀን!”

3ቀኑ ቅርብ ነው፤

የእግዚአብሔር ቀን ቅርብ ነው፤

የደመና ቀን፣

ለአሕዛብም የጥፋት ቀን ነው።

4በግብፅ ላይ ሰይፍ ይሆናል፤

በኢትዮጵያም ላይ ጭንቀት ይመጣል።

የታረዱት በግብፅ ሲወድቁ፣

ሀብቷ ይወሰዳል፤

መሠረቶቿም ይፈርሳሉ።

5ኢትዮጵያና ፉጥ፣ ልድያና መላው ዐረብ፣ ሊብያና30፥5 ዕብራይስጡ ኩብ ይላል። የቃል ኪዳኑ ምድር ሕዝብ ከግብፅ ጋር በአንድነት በሰይፍ ይወድቃሉ።

6“ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘የግብፅ ተባባሪዎች ይወድቃሉ።

የምትኵራራበት ብርታቷ ይወድቃል።

ከሚግዶል እስከ አስዋን፣

በውስጧ በሰይፍ ይወድቃሉ፤

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

7በባድማ መሬቶች መካከል፣

ባድማ ይሆናሉ፤

ከተሞቻቸውም፣

ከፈራረሱ ከተሞች መካከል ይሆናሉ።

8በግብፅ ላይ እሳት ስጭር፣

ረዳቶቿ ሁሉ ሲደቅቁ፣

በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

9“ ‘በዚያ ቀን ከእኔ ዘንድ መልእክተኞች በመርከብ ወጥተው ተዘልላ ከተቀመጠችበት ሁኔታ ለማውጣት ኢትዮጵያን ያስፈራሯታል፤ ግብፅ በጨለማ በምትዋጥበት ቀን ጭንቅ ይይዛቸዋል፤ ቀኑ በርግጥ ይመጣልና።

10“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነፆር እጅ፣

ስፍር ቍጥር የሌለውን የግብፅን ሕዝብ እደመስሳለሁ።

11ከአሕዛብ ሁሉ እጅግ ጨካኝ የሆኑት፣ እርሱና ሰራዊቱ፣

ምድሪቱን ለማጥፋት እንዲመጡ ይደረጋል፤

ሰይፋቸውን በግብፅ ላይ ይመዝዛሉ፤

ምድሪቱንም ሬሳ በሬሳ ያደርጋሉ፤

12የአባይን ወንዝ ውሃ አደርቃለሁ፤

ምድሪቱን ለክፉ ሰዎች እሸጣለሁ፤

በባዕዳን እጅ፣ ምድሪቷንና በውስጧ

ያለውን ሁሉ ባድማ አደርጋለሁ፤

እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ።

13“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ጣዖታትን አጠፋለሁ፤

በሜምፊስ30፥13 ዕብራይስጡ ኖፍ ይለዋል፤ እንዲሁም በ16 ያሉትን ምስሎች እደመስሳለሁ።

ከእንግዲህ በግብፅ ገዥ አይኖርም፣

በምድሪቱም ላይ ፍርሀት እሰዳለሁ።

14ጳትሮስን ባድማ አደርጋለሁ፤

በጣኔዎስ ላይ እሳት እለኵሳለሁ፤

በቴብስ30፥14 ዕብራይስጡ ይለዋል፤ እንዲሁም በ15 እና 16 ላይ ቅጣት አመጣለሁ።

15የግብፅ ምሽግ በሆነችው፣

በሲን ላይ መዓቴን አፈስሳለሁ፤

ስፍር ቍጥር የሌለውን የቴብስን ሕዝብ አጠፋለሁ።

16በግብፅ ላይ እሳት አነድዳለሁ፤

ሲን በጭንቅ ትናጣለች፤

ቴብስ በማዕበል ትወሰዳለች፤

ሜምፊስ በማያቋርጥ ጭንቀት ውስጥ ትገባለች።

17የሄልዮቱና30፥17 ዕብራይስጡ አዌን (ወይም ኦን) ይለዋል የቡባስቱ30፥17 ዕብራይስጡ ፊ ቢሴት ይላል ጕልማሶች፣

በሰይፍ ይወድቃሉ፤

ከተሞቹ ራሳቸውም ይማረካሉ።

18የግብፅን ቀንበር በምሰብርበት ጊዜ፣

በጣፍናስ ቀኑ ይጨልማል፤

ከዚያም የተኵራራችበት ብርታት ይንኰታኰታል።

በደመና ትሸፈናለች፤

መንደሮቿም ይማረካሉ።

19ስለዚህ በግብፅ ላይ ቅጣቴን አመጣለሁ፤

እነርሱም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

20በዐሥራ አንደኛው ዓመት፣ በመጀመሪያው ወር በሰባተኛው ቀን፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 21“የሰው ልጅ ሆይ፤ የግብፅን ንጉሥ የፈርዖንን ክንድ ሰብሬአለሁ፤ ይፈወስ ዘንድ ክንዱ አልተጠገነም፤ ወይም ሰይፍ መያዝ ይችል ዘንድ እጁ በመቃ አልታሰረም። 22ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በግብፅ ንጉሥ በፈርዖን ላይ ተነሥቻለሁ፤ ደኅናውንና የተሰበረውን፣ ሁለቱንም ክንዶቹን እሰብራለሁ፤ ሰይፉም ከእጁ እንዲወድቅ አደርጋለሁ። 23ግብፃውያንን በሕዝቦች መካከል እበትናቸዋለሁ፤ በአገሮችም መካከል እዘራቸዋለሁ። 24የባቢሎንን ንጉሥ ክንድ አበረታለሁ፤ ሰይፌንም አስይዘዋለሁ፤ የፈርዖንን ክንድ ግን እሰብራለሁ፤ እርሱም በፊቱ ክፉኛ እንደ ቈሰለ ሰው ያቃስታል። 25የባቢሎንን ንጉሥ ክንድ አበረታለሁ፤ የፈርዖን ክንድ ግን ይዝላል፤ ሰይፌን በባቢሎን ንጉሥ እጅ ሳስይዝ፣ እርሱም ሲነቀንቀው፣ ያኔ እግዚአብሔር መሆኔን ያውቃሉ። 26በሕዝቦች መካከል እበትናቸዋለሁ፤ በአገሮችም መካከል እዘራቸዋለሁ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ያውቃሉ።”

Thai New Contemporary Bible

เอเสเคียล 30:1-26

บทคร่ำครวญแด่อียิปต์

1พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าว่า 2“บุตรมนุษย์เอ๋ย จงกล่าวพยากรณ์ว่า ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า

“ ‘จงร่ำไห้และกล่าวว่า

“อนิจจา วันนั้นเอ๋ย!”

3เพราะว่าวันนั้นใกล้เข้ามาแล้ว

วันขององค์พระผู้เป็นเจ้าใกล้เข้ามา

เป็นวันแห่งเมฆครึ้ม

เป็นเวลาแห่งความพินาศของบรรดาประชาชาติ

4ดาบเล่มหนึ่งจะมาฟาดฟันอียิปต์

และความทุกข์ทรมานจะมากระหน่ำคูช30:4 คือ ตอนบนของลุ่มแม่น้ำไนล์ เช่นเดียวกับข้อ 5 และ 9

เมื่อผู้ที่ถูกสังหารล้มตายในอียิปต์

ทรัพย์สมบัติของอียิปต์จะถูกริบไป

และฐานรากของมันก็พังครืน

5คูช พูต ลิเดีย อาระเบียทั้งหมด ลิเบีย30:5 ภาษาฮีบรูว่าคับ และประชาชนของดินแดนแห่งพันธสัญญาจะล้มตายด้วยดาบพร้อมอียิปต์

6“ ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า

“ ‘บรรดาพันธมิตรของอียิปต์จะล้มตาย

และพลังอันภาคภูมิของมันจะสูญสลาย

จากมิกดลถึงอัสวาน

ผู้คนในอียิปต์จะล้มตายด้วยดาบ

พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น

7พวกเขาจะโดดเดี่ยว

อยู่ในแดนร้าง

นครต่างๆ ของพวกเขาจะพินาศ

อยู่ท่ามกลางนครที่ปรักหักพัง

8แล้วพวกเขาจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์

เมื่อเราจุดไฟเผาอียิปต์

และผู้ที่ช่วยเหลืออียิปต์ทุกคนจะถูกบดขยี้

9“ ‘ในวันนั้นผู้สื่อสารจะลงเรือจากเราไป เพื่อเขย่าขวัญคูชซึ่งอยู่อย่างทองไม่รู้ร้อน ความทุกข์ลำเค็ญจะเกาะกินใจของพวกเขาในวันหายนะของอียิปต์ เพราะวันนั้นจะมาถึงอย่างแน่นอน

10“ ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า

“ ‘เราจะนำกองกำลังทั้งหลายของอียิปต์มาถึงจุดจบ

โดยน้ำมือของกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลน

11เขากับกองทัพซึ่งเป็นผู้อำมหิตที่สุดในหมู่ประชาชาติ

จะถูกนำมาทำลายดินแดนแห่งนี้

เขาจะชักดาบออกห้ำหั่นอียิปต์

และทำให้คนตายเกลื่อนแผ่นดิน

12เราจะทำให้ลำน้ำไนล์เหือดแห้ง

และขายดินแดนอียิปต์ให้แก่คนชั่ว

เราจะทำให้ทุกสิ่งทุกอย่างในดินแดนนั้นเริศร้าง

โดยน้ำมือของชาวต่างชาติ

เราผู้เป็นพระยาห์เวห์ได้ลั่นวาจาไว้

13“ ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า

“ ‘เราจะทำลายบรรดารูปเคารพ

และทำให้เทวรูปต่างๆ ในเมมฟิสถึงกาลอวสาน

จะไม่มีเจ้านายอีกต่อไปในอียิปต์

และเราจะบันดาลให้ความหวาดหวั่นแพร่สะพัดไปทั่วดินแดนนั้น

14เราจะทำให้อียิปต์ตอนบนเริศร้าง

จะจุดไฟเผาโศอัน

และลงโทษเธเบส

15เราจะระบายโทสะแก่เปลูเซียม

ซึ่งเป็นที่มั่นของอียิปต์

และทำลายกองกำลังต่างๆ ของเธเบส

16เราจะจุดไฟเผาอียิปต์

เปลูเซียมจะทุรนทุรายด้วยความทุกข์ทรมาน

เธเบสจะถูกพายุซัดกระหน่ำ

เมมฟิสจะทุกข์ลำเค็ญอยู่ตลอดเวลา

17คนหนุ่มของเมืองเฮลิโอโปลิสและบูบาสทิส

จะล้มตายด้วยดาบ

และนครต่างๆ จะตกเป็นเชลย

18ที่ทาห์ปานเหส กลางวันแสกๆ จะมืดครึ้ม

เมื่อเราทำลายแอกของอียิปต์

ที่นั่นพละกำลังอันภาคภูมิของมันจะถึงกาลอวสาน

จะมีเมฆปกคลุมทั่วเมืองนั้น

และหมู่บ้านต่างๆ จะตกเป็นเชลย

19เราจะลงโทษอียิปต์เช่นนี้แหละ

แล้วพวกเขาจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์’ ”

20ในวันที่เจ็ดเดือนที่หนึ่งปีที่สิบเอ็ด พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าว่า 21“บุตรมนุษย์เอ๋ย เราได้หักแขนของฟาโรห์กษัตริย์แห่งอียิปต์ ไม่มีการพันผ้ารักษาหรือเข้าเฝือกเพื่อให้มันกลับแข็งแรงพอที่จะจับดาบได้อีก 22ฉะนั้นพระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่าเราเป็นศัตรูกับฟาโรห์กษัตริย์แห่งอียิปต์ เราจะหักแขนของเขาทั้งสองข้าง ทั้งข้างที่ยังดีและข้างที่หัก เราจะทำให้ดาบร่วงจากมือของเขา 23เราจะทำให้ชาวอียิปต์กระจัดกระจายออกไปตามชนชาติต่างๆ และไปยังนานาประเทศ 24เราจะทำให้แขนของกษัตริย์บาบิโลนแข็งแกร่งและเอาดาบของเราใส่มือเขา แต่เราจะหักแขนของฟาโรห์และเขาจะร้องครวญครางต่อหน้ากษัตริย์บาบิโลนเหมือนคนบาดเจ็บใกล้ตาย 25เราจะทำให้แขนของกษัตริย์บาบิโลนแข็งแกร่ง ส่วนแขนของฟาโรห์จะกะปลกกะเปลี้ย แล้วพวกเขาจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์ เมื่อเราเอาดาบใส่มือกษัตริย์บาบิโลน แล้วเขาก็กวัดแกว่งมันฟาดฟันอียิปต์ 26เราจะทำให้ชาวอียิปต์กระจัดกระจายออกไปตามชนชาติต่างๆ และไปยังนานาประเทศ แล้วพวกเขาจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์”