ሕዝቅኤል 28 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 28:1-26

በጢሮስ ንጉሥ ላይ የተነገረ ትንቢት

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ለጢሮስ ገዥ እንዲህ በለው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ልብህ በትዕቢት ተወጥሮ፣

“እኔ አምላክ ነኝ፤

በአምላክ ዙፋን ላይ፣

በባሕሮችም ልብ ተቀምጫለሁ” አልህ።

ምንም እንኳ እንደ አምላክ ጠቢብ ነኝ ብለህ ብታስብም፣

አንተ ሰው እንጂ አምላክ አይደለህም።

3ከዳንኤል28፥3 ወይም ዳኔል፤ የዕብራይስጡን ቃል አጻጻፍ ስንመለከት ነቢዩ ዳንኤልን ሳይሆን ሌላን ሰው የሚያመለክት ነው። ይልቅ ጠቢብ ነህን?

ከአንተስ የተሰወረ ምስጢር የለምን?

4በጥበብህና በማስተዋልህ፣

የራስህን ሀብት አከማቸህ፤

ወርቅም ብርም፣

በግምጃ ቤትህ አጠራቀምህ።

5በንግድ ሥራ እጅግ ከመራቀቅህ የተነሣ፣

በሀብት ላይ ሀብት አካበትህ፤

ከሀብትህ ብዛት የተነሣም፤

ልብህ በትዕቢት ተወጠረ።

6“ ‘ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘እንደ አምላክ ጥበበኛ ነኝ፤ ብለህ

ስለምታስብ፣

7ከአሕዛብ መካከል እጅግ ጨካኞች የሆኑትን ባዕዳን፣

በአንተ ላይ አመጣለሁ፤

በጥበብህ ውበት ላይ ሰይፋቸውን ይመዝዛሉ፤

ታላቅ ክብርህንም ያረክሳሉ።

8ወደ ጕድጓድ ያወርዱሃል፤

በጥልቁም ባሕር ውስጥ፣

በባሕሮችም ልብ ውስጥ አስከፊ ሞት ትሞታለህ።

9ታዲያ በገዳዮችህ ፊት፣

“አምላክ ነኝ” ትላለህን?

በገዳዮችህ እጅ ስትገባ፣

አንተ ሰው እንጂ አምላክ አይደለህም።

10በባዕዳን እጅ፣

ያልተገረዙትን ሰዎች አሟሟት ትሞታለህ፤

እኔ ተናግሬአለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

11የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 12“የሰው ልጅ ሆይ፤ ስለ ጢሮስ ንጉሥ ሙሾ አውርድ፤ እንዲህም በለው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ጥበብን የተሞላህ፣ ፍጹም ውበትን የተላበስህ፣

የፍጹምነት ምሳሌ ነበርህ።

13በእግዚአብሔር የአትክልት ቦታ፣

በዔድን28፥13 ወይም ላፒስ ላዙሊ ነበርህ፤

እያንዳንዱ የከበረ ድንጋይ አስጊጦህ ነበር፤

ሰርድዮን፣ ቶጳዝዮን፣ አልማዝ፣

መረግድ፣ ኢያሰጲድ፣ ሰንፔር፣

በሉር፣ ቢረሌና የከበረ ዕንቍ።28፥13 ከእነዚህ የከበሩ ድንጋዮች መካከል አንዳንዶቹ ትክክለኛ ማንነታቸው ተለይቶ አይታወቅም

ልብስህም የሚያብረቀርቅ ዕንወርቅ ነበር፤

የተዘጋጁትም አንተ በተፈጠርህበት ዕለት ነበር።

14ጠባቂ ኪሩብ ሆነህ ተቀብተህ ነበር፤

ለዚሁም ሾምሁህ፤

በእግዚአብሔር ቅዱስ ተራራ ላይ ነበርህ፤

በእሳት ድንጋዮች መካከል ተመላለስህ።

15ከተፈጠርህበት ቀን ጀምሮ፣

ክፋት እስከ ተገኘብህ ድረስ፣

በመንገድህ ነቀፌታ አልነበረብህም።

16ንግድህ ስለ ደረጀ፣

በዐመፅ ተሞላህ፣

ኀጢአትም ሠራህ፤

ስለዚህ ከእግዚአብሔር ተራራ በውርደት አሳደድሁህ፤

ጠባቂ ኪሩብ ሆይ፤ ከእሳት ድንጋዮች

መካከል አስወጣሁህ።

17በውበትህ ምክንያት፣

ልብህ ታበየ፤

ከክብርህ ታላቅነት የተነሣም፣

ጥበብህን አረከስህ።

ስለዚህ ወደ ምድር ወረወርሁህ፤

ለነገሥታት ትዕይንት አደረግሁህ።

18በኀጢአትህና በተጭበረበረው ንግድህ ብዛት፣

መቅደስህን አረከስህ።

ስለዚህ እሳት ከአንተ እንዲወጣ አደረግሁ፤

እርሱም በላህ፤

በሚመለከቱህ ሁሉ ፊት፣

በምድር ላይ ዐመድ አደረግሁህ።

19የሚያውቁህን አሕዛብ ሁሉ፣

ሁኔታህ አስደንግጧቸዋል፤

መጨረሻህ የሚያሳዝን ሆነ፤

ከእንግዲህ ህልውና የለህም።’ ”

በሲዶን ላይ የተነገረ ትንቢት

20የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 21“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን ወደ ሲዶና አዙር፤ ትንቢትም ተናገርባት፤ 22እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ሲዶን ሆይ፤ በአንቺ ላይ ተነሥቻለሁ፤

በውስጥሽ እከብራለሁ፤

ቅጣትን ሳመጣባት፣

ቅድስናዬንም በውስጧ ስገልጥ፣

እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

23በእርሷ ላይ መቅሠፍት አመጣለሁ፤

በመንገዶቿ ላይ ደም እንዲፈስስ አደርጋለሁ፤

ከየአቅጣጫው በሚመጣ ሰይፍ፣

የታረዱት በውስጧ ይወድቃሉ፤

ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

24“ ‘ከእንግዲህ ወዲያ የእስራኤል ሕዝብ የሚያሠቃይ አሜከላና የሚወጋ እሾኽ የሆኑ ጎረቤቶች አይኖሯቸውም፤ ከዚያም እኔ ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

25“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የእስራኤልን ሕዝብ ከተበተኑባቸው አገሮች መካከል በምሰበስብበት ጊዜ፣ አሕዛብ እያዩ ቅድስናዬን በመካከላቸው እገልጣለሁ፤ ከዚያም በገዛ ምድራቸው ይኖራሉ፤ ይህም ለባሪያዬ ለያዕቆብ የሰጠሁት ነው። 26በዚያም በሰላም ይኖራሉ፤ ቤቶች ይሠራሉ፤ የወይን ተክል ቦታም ያበጃሉ። ያጣጣሏቸው ጎረቤቶቻቸውን ሁሉ በምቀጣበት ጊዜ እነርሱ በሰላም ይኖራሉ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

Het Boek

Ezechiël 28:1-26

De vernietiging van de koning van Tyrus

1Dit is de volgende boodschap, die de Here mij gaf: 2-3 ‘Mensenzoon, vertel de heerser van Tyrus dat de Oppermachtige Here zegt: “U bent zo trots, dat u denkt dat u God bent. U denkt: op de troon van een god zit ik hier op dit eiland, omringd door de zeeën. Maar u bent slechts een mens, geen god, ook al zegt u dat u zo wijs bent als God. Maar u denkt dat u wijzer bent dan Daniël, dat er geen geheimen voor u bestaan. 4Uw wijsheid en inzicht hebt u gebruikt voor het binnenhalen van grote rijkdommen, goud, zilver en vele andere schatten. 5Ja, uw deskundigheid heeft u erg rijk, maar ook buitengewoon trots gemaakt.” 6Daarom zegt de Oppermachtige Here: “Omdat u denkt zo wijs als een god te zijn, 7zal een vijandelijk leger het zwaard trekken tegen uw enorme wijsheid, u van uw roem beroven en uw schoonheid vernietigen! 8Het zal u naar uw graf brengen en u zult sterven als iemand die zwaargewond in de strijd sneuvelt, daar op uw eiland midden in de zee. 9Zult u dan nog in het bijzijn van uw vijanden blijven volhouden dat u een god bent? Voor degenen die u aanvallen, zult u in elk geval geen god zijn, maar gewoon een mens! 10U zult door toedoen van buitenlanders de dood van een onreine sterven. Want Ik heb gesproken,” zegt de Oppermachtige Here.’

11En de Here vervolgde zijn boodschap met de woorden: 12‘Mensenzoon, zing een klaaglied over de koning van Tyrus. Vertel hem dat de Oppermachtige Here zegt: “U vormde het toonbeeld van wijsheid en volkomen schoonheid. 13U was in Eden, de tuin van God, uw kleding was bezaaid met waardevolle stenen: robijn, topaas, jaspis, kristal, onyx, turkoois, saffier, hematiet en smaragd, alle in prachtige zettingen van zuiver goud. Op de dag dat u werd geschapen, werden ze al voor u klaargelegd. 14Ik benoemde u tot de gezalfde, beschermende cherub. U had toegang tot de heilige berg van God. U liep tussen de vlammende stenen. 15U was volmaakt in alles wat u deed, vanaf de dag dat u werd geschapen tot op het moment dat het kwaad in u werd aangetroffen. 16Door uw wereldwijde handel werd u steeds meer besmet door onrechtvaardigheid en zondigde u. Daarom verjoeg Ik u van de berg van God. Ik verbande u, beschermende cherub, en tussen de vlammende stenen was niet langer plaats voor u. 17Uw hart was vol trots wegens al uw schoonheid, u misbruikte uw wijsheid ter wille van uw machtspositie. Daarom heb Ik u op de aarde neergeworpen en u hulpeloos blootgesteld aan de minachtende blikken van koningen. 18Uit winstbejag ontwijdde u uw heiligheid, daarom liet Ik vuur opvlammen uit uw eigen daden. Dat vuur verbrandde u tot as op aarde voor de ogen van allen die naar u keken. 19Alle volken die u kennen, zijn met stomheid geslagen door uw lot, u bent een afschrikwekkend voorbeeld. U bent voor altijd vernietigd.” ’

20Hierna kreeg ik een volgende boodschap van de Here: 21‘Mensenzoon, kijk in de richting van de stad Sidon en profeteer tegen haar met de woorden: 22de Oppermachtige Here zegt: “Ik ben uw vijand, Sidon, en Ik zal mijn heerlijkheid aan u openbaren. Als Ik u vernietig en mijn heiligheid aan u toon, zullen allen die daar getuige van zijn, weten dat Ik de Here ben. 23Ik zal een epidemie op u afsturen en een verwoestend leger, de gewonden zullen in uw straten worden gedood door strijders die van alle kanten komen. Dan zult u erkennen dat Ik de Here ben. 24Niet langer zullen u en andere kwaadwillige buurstaten Israël prikken en verwonden als dorens en distels.

25De Israëlieten zullen opnieuw in een eigen land wonen, het land dat Ik hun voorvader Jakob gaf. Want Ik zal hen verzamelen vanuit de verre landen, waarover Ik hen verstrooide. Ik zal de volken van de wereld te midden van mijn volk mijn heiligheid laten zien. 26Zij zullen weer veilig in Israël wonen en daar hun huizen bouwen en wijngaarden planten. Wanneer Ik over de naburige volken die hen met zoʼn grote kwaadaardigheid behandelden, het oordeel laat komen, zullen zij weten dat Ik, de Here, hun God ben.” ’