ሕዝቅኤል 24 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 24:1-27

የድስቱ ምሳሌ

1በዘጠነኛው ዓመት፣ በዐሥረኛው ወር፣ በዐሥረኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ይህን ቀን፣ የዛሬውን ዕለት፣ ለይተህ መዝግብ፤ የባቢሎን ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በዚህ ቀን ከብቧታልና። 3ለዚህ ዐመፀኛ ቤት እንዲህ ብለህ ተምሳሌት ተናገር፤ ‘ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ብረት ድስት በእሳት ላይ ጣድ፤

ከጣድህም በኋላ ውሃ ጨምርበት።

4ሙዳ፣ ሙዳ ሥጋ፣

ምርጥ ምርጡን ቍርጥ ሁሉ፣ ጭንና ወርቹን ጨምርበት፤

የተመረጡ ዐጥንቶችንም ሙላበት።

5ከመንጋው ሙክቱን ውሰድ፤

ዐጥንቱን ለማብሰል ብዙ ማገዶ ከሥሩ ጨምር፤

ሙክክ እስከሚል ቀቅለው፤

ዐጥንቱም ይብሰል።

6“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤

“ ‘ለዛገችው ብረት ድስት

ዝገቷም ለማይለቅ፣

ደም ላፈሰሰችው ከተማ ወዮላት!

መለያ ዕጣ ሳትጥል

አንድ በአንድ አውጥተህ ባዶ አድርገው።

7“ ‘የሰው ደም በመካከሏ አለ፤

በገላጣ ዐለት ላይ አደረገችው እንጂ፣

ዐፈር ሊሸፍነው በሚችል፣

በመሬት ላይ አላፈሰሰችውም።

8ቍጣዬ እንዲነድድና ለመበቀል እንዲያመቸኝ፣

ይሸፈንም ዘንድ እንዳይችል፣

ደሟን በገላጣ ዐለት ላይ አፈሰስሁ።

9“ ‘ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ደም ላፈሰሰችው ከተማ ወዮላት!

እኔም ደግሞ የምትቃጠልበትን ማገዶ እቈልላለሁ።

10ማገዶውን ከምርበት፤

እሳቱን አንድድ፤

ቅመም ጨምረህበት፣

ሥጋውን በሚገባ ቀቅል፤

ዐጥንቱም ይረር።

11ጕድፉ እንዲቀልጥ፣

ዝገቱም በእሳት እንዲበላ፣

ባዶው ድስት እስኪሞቅ፣

መደቡም እስኪግል ከሰል ላይ ጣደው።

12ብዙ ጕልበት ቢፈስስበትም፣

የዝገቱ ክምር፣

በእሳት እንኳ፣ ሊለቅ አልቻለም።

13“ ‘የረከስሽው በብልግናሽ ነው፤ ቍጣዬ በአንቺ ላይ እስኪፈጸም ድረስ ከእንግዲህ ንጹሕ አትሆኚም፤ ከርኩሰትሽ ላነጻሽ ፈልጌ፣ መንጻት አልወደድሽምና።

14“ ‘እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ፤ የምሠራበትም ጊዜ ደርሷል፤ ወደ ኋላ አልልም፤ አልራራም፤ አላመነታምም። እንደ መንገድሽና እንደ ተግባርሽ ይፈረድብሻል፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

የሕዝቅኤል ሚስት መሞት

15የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 16“የሰው ልጅ ሆይ፤ የዐይንህ ማረፊያ የሆነውን ነገር በመቅሠፍት እወስድብሃለሁ፤ አንተ ግን ዋይታ አታሰማ፤ አታልቅስ፤ እንባህንም አታፍስስ፤ 17ድምፅህን ዝቅ አድርገህ በሐዘን አንጐራጕር እንጂ ለሞተው አታልቅስ። ጥምጥምህን ከራስህ አታውርድ፤ ጫማህንም አታውልቅ፤ አፍህ ድረስ አትሸፋፈን፤ የዕዝን እንጀራም አትብላ።”

18እኔም በማለዳ ለሕዝቡ ተናገርሁ፤ ሚስቴም ማታውኑ ሞተች፤ በማግስቱም ጧት እንደ ታዘዝሁ አደረግሁ።

19ሕዝቡም፣ “ይህን ስታደርግ ለእኛ የምታስተላልፈው መልእክት ምን እንደ ሆነ አትነግረንምን?” አሉኝ።

20እኔም እንዲህ አልኋቸው፤ “የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 21ለእስራኤል ቤት እንዲህ በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የኀይላችሁን ትምክሕት፣ የዐይናችሁ ማረፊያና የልባችሁ ደስታ የሆነውን መቅደሴን አረክሳለሁ። ትታችኋቸው የሄዳችሁ ወንድና ሴት ልጆቻችሁ በሰይፍ ይወድቃሉ። 22እኔ እንዳደረግሁም ታደርጋላችሁ፤ አፋችሁ ድረስ አትሸፋፈኑም፤ የዕዝን እንጀራም አትበሉም፤ 23ጥምጥማችሁን ከራሳችሁ አታወርዱም፤ ጫማችሁንም አታወልቁም። በኀጢአታችሁ ትመነምናላችሁ፤ እርስ በርስ ታቃስታላችሁ እንጂ ሐዘን አትቀመጡም፤ አታለቅሱምም። 24ሕዝቅኤል ምልክት ይሆናችኋል፤ እርሱ እንዳደረገው ታደርጋላችሁ፤ ይህ በሚሆንበት ጊዜ፣ እኔ ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።” ’

25“አንተም የሰው ልጅ ሆይ፤ ኀይላቸውን፣ ደስታቸውንና፣ ክብራቸውን፣ የዐይናቸው ማረፊያና የልባቸው ደስታ የሆኑትን ወንድና ሴት ልጆቻቸውን ጭምር በምወስድባቸው ቀን፣ 26በዚያን ቀን፣ ያመለጠ ሰው ይህን ወሬ ሊነግርህ ወደ አንተ ይመጣል፤ 27በዚያን ቀን አፍህ ተከፍቶ ከእርሱ ጋር ትነጋገራለህ፤ ከዚያም በኋላ እንደ ድዳ አትሆንም፤ ምልክትም ትሆናቸዋለህ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以西结书 24:1-27

锈锅的比喻

1第九年十月十日,耶和华对我说: 2“人子啊,今天是巴比伦王围攻耶路撒冷的日子,你要记下这日子。 3你要向叛逆的以色列人说比喻,告诉他们,主耶和华这样说,

“‘把锅放在火上,

里面倒进水,

4把羊腿、羊肩等上好的肉块放进锅里,

让锅里盛满精选的骨头。

5要从羊群中选一头上好的羊,

把柴堆在锅下,

烧开锅煮里面的骨头。’”

6主耶和华说:“这像锈锅一样充满血腥的城有祸了!要把肉从这锈迹斑斑的锅中一块块地取出来。 7这城沾满血腥,任凭受害者的血流在光秃秃的磐石上,而不是流在地上用土掩盖。 8我任凭这城把受害者的血洒在磐石上,不加掩盖,好激起我的烈怒,使她受报应。 9所以主耶和华说,‘血腥的城啊,你有祸了!我要预备大堆木柴, 10添在火上,燃起旺火,把肉煮烂,加入香料,烧焦骨头。 11然后,把倒空的锅放在炭火上烧热,把铜烧红,好熔化它的杂质,除净锈垢, 12却徒劳无功,因为锈垢太厚,就是用火也不能清除。 13耶路撒冷啊,淫荡使你污秽不堪,我要洁净你,你却不愿被洁净。所以,除非我向你倾尽一切愤怒,否则你的污秽将不能清除。 14我耶和华言出必行,决不宽容,也不留情,我必照你的所作所为来审判你。’这是主耶和华说的。”

15耶和华对我说: 16“人子啊,我要突然夺去你心爱的人,你不可悲伤,也不可流泪哭泣。 17你要默然哀叹,不可为死人办丧事,仍要缠着头巾,穿着鞋,不可蒙着脸,也不可吃丧家吃的饭。” 18早晨我把这事告诉百姓,晚上我的妻子便死了。次日早晨,我便遵照耶和华的吩咐行。

19百姓问我:“你可以告诉我们,你这样做跟我们有什么关系吗?” 20我告诉他们:“耶和华对我说, 21‘你告诉以色列人,我要使我的圣所,就是你们引以为傲、眼中所爱、心里所慕的受到亵渎。你们留下的儿女必死于刀下。 22那时,你们将像我的仆人一样不蒙脸,不吃丧家吃的饭。 23你们仍将裹着头巾,穿着鞋,不哭泣,也不悲伤。你们必因自己的罪恶而默然叹息,逐渐灭亡。 24以西结做的事都是你们的预兆,你们也将做他做的。当这事发生时,你们就知道我是主耶和华了。’

25“人子啊,有一天我要夺去他们所喜悦、所夸耀、眼中所爱、心里所慕的堡垒,也要夺去他们的儿女。 26那日,幸存的人必来告诉你这个消息。 27那时,你必开口向那人说话,不再沉默。你必成为他们的预兆,他们就知道我是耶和华。”