ሕዝቅኤል 16 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 16:1-63

ኢየሩሳሌም ታማኝ ስላለመሆኗ የተሰጠ ተራዛሚ ተለዋጭ ዘይቤ

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ለኢየሩሳሌም አስጸያፊ ተግባሯን ፊት ለፊት ንገራት፤ 3እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን እንዲህ ይላታል፤ ዘርሽና ትውልድሽ ከከነዓን ምድር ነው፤ አባትሽ አሞራዊ፣ እናትሽም ኬጢያዊት ነበሩ። 4በተወለድሽበት ቀን ዕትብትሽ አልተቈረጠም፤ ንጹሕ እንድትሆኚ በውሃ አልታጠብሽም፤ በጨው አልታሸሽም፤ በጨርቅም አልተጠቀለልሽም። 5በርኅራኄ ዐይን ተመልክቶሽ ወይም ዐዝኖልሽ ከእነዚህ አንዱን እንኳ ያደረገልሽ ሰው አልነበረም፤ ይልቁንም በተወለድሽበት ቀን ተንቀሽ ስለ ነበር ሜዳ ላይ ተጣልሽ።

6“ ‘እኔም በዚያ ሳልፍ፣ በደምሽ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ስትንፈራገጪ አየሁሽ፤ በደምሽም ውስጥ ተኝተሽ ሳለሽ፣ “በሕይወት ኑሪ!”16፥6 ጥቂት የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ሰብዐ ሊቀናትና ሱርስቱ እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን “በሕይወት ኑሪ!” በደምሽ ውስጥ ተኝተሽ ሳለሽ “በሕይወት ኑሪ!” አልሁሽ ይላሉ። አልሁሽ። 7ሜዳ ላይ እንዳለ ቡቃያ አሳደግሁሽ፤ አንቺም አደግሽ፤ ብርቅ ዕንቍ ሆንሽ16፥7 ወይም የበሰልሽ ሆንሽ። ጡቶችሽ አጐጠጐጡ፤ ጠጕርሽም አደገ፤ ነገር ግን ከእናትሽ ማሕፀን እንደ ወጣሽ ዕርቃንሽን ነበርሽ።

8“ ‘ዳግመኛም በአጠገብሽ በማልፍበት ጊዜ ወደ አንቺ ተመለከትሁ፤ ለመፈቀርም እንደ ደረስሽ ባየሁ ጊዜ፣ የመጐናጸፊያዬን ዘርፍ በላይሽ ዘርግቼ ዕርቃንሽን ሸፈንሁ። ማልሁልሽ፤ ከአንቺም ጋር ቃል ኪዳን ተጋባሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ አንቺም የእኔ ሆንሽ።

9“ ‘በውሃ ዐጥቤ16፥9 ወይም በውሃ ዐጠብሁሽ ከደም አጠራሁሽ፤ ዘይትም ቀባሁሽ። 10ወርቀ ዘቦ አለበስሁሽ፤ ምርጥ ቈዳ ጫማም አደረግሁልሽ፤ ያማረ በፍታ አለበስሁሽ ውድ መደረቢያም አጐናጸፍሁሽ። 11በጌጣጌጥ አንቈጠቈጥሁሽ፤ በእጅሽ አንባር፣ በዐንገትሽም ድሪ አጠለቅሁልሽ፤ 12በአፍንጫሽ ቀለበት፣ በጆሮሽ ጕትቻ፣ በራስሽም ላይ ውብ አክሊል አደረግሁልሽ፤ 13በወርቅና በብር አጌጥሽ፤ ልብስሽም ያማረ በፍታ፣ ሐርና ወርቀ ዘቦ ነበር፤ ምግብሽም የላመ ዱቄት፣ ማርና የወይራ ዘይት ነበር። እጅግ ውብ ሆንሽ፤ ንግሥት ለመሆንም በቃሽ። 14እኔ ከሰጠሁሽ ሞገስ የተነሣ ውበትሽ ፍጹም በመሆኑ ዝናሽ በአሕዛብ መካከል ገነነ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር

15“ ‘ነገር ግን በውበትሽ ተመካሽ፤ ዝናሽንም ለአመንዝራነት ተጠቀምሽበት፤ ከዐላፊ አግዳሚው ጋር ያለ ገደብ አመነዘርሽ፣ ውበትሽም ለማንም ሆነ።16፥15 ከአብዛኛዎቹ የጥንት የዕብራይስጥ ቅጆች ጋር ተመሳሳይ ሲሆን አንድ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጅ ግን (አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት የጥንት ቅጆችን ይመ) ከዐላፊ አግዳሚ… አመነዘርሽ፤ እንዲህ ያለው ነገር መሆን የለበትም ይላል። 16ከልብስሽ አንዳንዱን ወስደሽ የምታመነዝሪበትን መስገጃ ስፍራ አስጌጥሽበት፤ እንዲህ ዐይነት ነገር ከዚህ ቀደም አልታየም፤ ወደ ፊትም አይኖርም። 17ከሰጠሁሽ ወርቄና ብሬ የተሠራውን ምርጥ ጌጣጌጥ ወስደሽ የወንድ ምስሎች ለራስሽ አበጀሽ፤ ከእነርሱም ጋር ዝሙት ፈጸምሽ። 18ወርቀ ዘቦ ልብስሽን ወስደሽ ደረብሽላቸው፤ ዘይቴንና ዕጣኔንም በፊታቸው አቀረብሽ። 19እንድትበዪ የሰጠሁሽን ምግብ ይኸውም ምርጡን ዱቄት፣ ማሩንና የወይራ ዘይቱን መልካም መዐዛ ያለው ዕጣን አድርገሽ አቀረብሽላቸው፤ እንዲህ ያለ ነገር ተፈጽሟል፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር

20“ ‘ለእኔ የወለድሻቸውን ወንዶችና ሴቶች ልጆችሽን እንዲበሏቸው ለምስሎቹ ሠዋሽላቸው፤ አመንዝራነትሽ አንሶ ነውን? 21ልጆቼን ዐርደሽ ለጣዖት መሥዋዕት አድርገሽ አቀረብሻቸው።16፥21 ወይም በእሳት ውስጥ አሳለፋችኋቸው 22በእነዚህ አስጸያፊ ተግባሮችሽና አመንዝራነትሽ ሁሉ፣ ከእናትሽ ማሕፀን እንደ ወጣሽ ዕርቃንሽን ሆነሽ በደምሽ ውስጥ ስትንፈራገጪ የነበርሽበት የሕፃንነትሽ ወራት ትዝም አላለሽ።

23“ ‘ወዮ! ወዮልሽ! ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከሌላው ክፋትሽ ሁሉ በተጨማሪ፣ 24ለራስሽ ጕብታን አበጀሽ፤ በየአደባባዩም የማምለኪያ ኰረብታ ሠራሽ። 25በየመንገዱ መጠምዘዣ ላይም የመስገጃ ኰረብታ አበጀሽ፤ ገላሽን ለዐላፊ አግዳሚው በማቅረብና አመንዝራነትሽን በማበራከት ውበትሽንም አረከስሽ። 26ዘማውያን ከሆኑ ግብፃውያን ጎረቤቶችሽ ጋር አመነዘርሽ፤ ገደብ በሌለው የዝሙት ተግባርሽም ለቍጣ አነሣሣሽኝ። 27ስለዚህ ክንዴን በአንቺ ላይ አንሥቼ ድርጎሽን ቀነስሁ፤ ከክፉ መንገድሽም የተነሣ በብልግናሽ ለሚያፍሩ ጠላቶችሽ ለፍልስጥኤማውያን ሴቶች ልጆች አሳልፌ ሰጠሁሽ። 28ገና ስላልረካሽም ከአሦራውያን ጋር ደግሞ አመነዘርሽ፤ ከዚያም በኋላ እንኳ አልረካሽም። 29ርኩሰትሽንም እስከ ነጋዴዎች ምድር እስከ ባቢሎን16፥29 ወይም ካላዲያ ድረስ አበዛሽ፤ ያም ሆኖ አልረካሽም።

30“ ‘እንደ ዐይን አውጣ አመንዝራ ይህን ሁሉ መፈጸምሽ ምን ዐይነት ደካማ ልብ ቢኖርሽ ነው! ይላል ጌታ እግዚአብሔር31በየመንገዱ መጠምዘዣ ላይ ጕብታሽን ባበጀሽና በየአደባባዩም መስገጃ ኰረብታ በሠራሽ ጊዜ እንደ ማንኛውም ዝሙት ዐዳሪ አልነበርሽም፤ ምክንያቱም ዋጋ አላስከፈልሽም።

32“ ‘አንቺ ከገዛ ባሏ ይልቅ ሌሎችን የምታስተናግድ አመንዝራ ነሽ! 33ማንኛዋም አመንዝራ ሴት ዋጋ ይከፈላታል፤ አንቺ ግን ለወዳጆችሽ ሁሉ ስጦታ ታበረክቻለሽ፤ ከየአቅጣጫው መጥተው ከአንቺ ጋር ያመነዝሩ ዘንድ እጅ መንሻ ታቀርቢላቸዋለሽ። 34ስለዚህ ያንቺ ግልሙትና ከሌሎቹ የተለየ ነው፤ ማመንዘር የሚሻ ማንም ሰው፣ አንቺን አሳድዶ ማግባባት አያስፈልገውም። ዋጋ ትከፍያለሽ እንጂ አይከፈልሽም፤ አንቺ የሌሎች ፍጹም ተቃራኒ ነሽ።

35“ ‘አንቺ አመንዝራ ሆይ፤ እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ! 36ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ሀብትሽን16፥36 ወይም ምኞትሽን ስላፈሰስሽ፣ ከወዳጆችሽ ጋር ያለ ገደብ ስላመነዘርሽና ዕርቃንሽን ስለ ገለጥሽ፣ ስለ አስጸያፊዎቹ ጣዖቶችሽ ሁሉና ለእነርሱም የልጆችሽን ደም ስላቀረብሽ፣ 37በዚህ ምክንያት ደስ የተሰኘሽባቸውን ወዳጆችሽን፣ የወደድሻቸውንና የጠላሻቸውን ሁሉ እሰበስባለሁ፤ ከየአቅጣጫው ሁሉ በዙሪያሽ እሰበስባቸዋለሁ፤ በፊታቸው ዕርቃንሽን እገልጣለሁ፤ እነርሱም ኀፍረተ ሥጋሽን ሁሉ ያያሉ። 38ለአመንዝራና ለነፍሰ ገዳይ ሴቶች የሚገባውን ፍርድ እፈርድብሻለሁ፤ በመዓቴና በቅናቴ እስከ ደም እበቀልሻለሁ። 39ለወዳጆችሽ አሳልፌ እሰጥሻለሁ፤ እነርሱም ጕብታሽንና የማምለኪያ ኰረብታሽን ያፈርሳሉ፤ ልብስሽን ይገፉሻል፤ ምርጥ ጌጣጌጥሽን ይቀሙሻል፤ ዕርቃንሽንና ባዶ እጅሽን ያስቀሩሻል። 40ሕዝብ ያነሣሡብሻል፤ በድንጋይ ይወግሩሻል፤ በሰይፍ ይቈራርጡሻል፤ 41ቤቶችሽን ያቃጥላሉ፤ በብዙ ሴቶችም ፊት ቅጣት ያመጡብሻል። ግልሙትናሽን አስተውሻለሁ፤ ከእንግዲህም ለወዳጆችሽ ዋጋ አትከፍዪም። 42በዚህም በአንቺ ላይ የነበረው ቍጣዬ ይበርዳል፤ የቅናቴ ቍጣም ከአንቺ ይርቃል። እኔም ዝም እላለሁ፤ ከእንግዲህም አልቈጣም።

43“ ‘በእነዚህ ነገሮች አስቈጣሽኝ እንጂ የልጅነትሽን ወራት አላሰብሽም፤ ስለዚህ የሥራሽን እከፍልሻለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። በሌላው አስጸያፊ ተግባርሽ ሁሉ ላይ ዘማዊነትን አልጨመርሽምን?

44“ ‘በምሳሌ የሚናገር ሁሉ፣ “ሴት ልጅ በእናቷ ትወጣለች” እያለ ይመስልብሻል። 45አንቺ ባሏንና ልጆቿን የምትጸየፍ የእናትሽ ልጅ ነሽ፤ ባሎቻቸውንና ልጆቻቸውን የሚጸየፉ የእኅቶችሽ እኅት ነሽ። እናታችሁ ኬጢያዊት፣ አባታችሁም አሞራዊ ነበሩ። 46ታላቂቱ እኅትሽ ከአንቺ በስተ ሰሜን ከሴት ልጆቿ ጋር የምትኖረው ሰማርያ ናት፤ ታናሺቱ እኅትሽም ከአንቺ በስተ ደቡብ ከሴት ልጆቿ ጋር የምትኖረው ሰዶም ናት። 47አንቺም በእነርሱ መንገድ መሄድና አስጸያፊ ተግባራቸውን መከተል ብቻ ሳይሆን፣ ከእነርሱ ይልቅ ፈጥነሽ ምግባረ ብልሹ ሆንሽ። 48እኔ ሕያው እግዚአብሔር! በራሴ እምላለሁ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ አንቺና ሴት ልጆችሽ ያደረጋችሁትን እኅትሽ ሰዶምና ልጆቿ እንኳ አላደረጉትም።

49“ ‘እነሆ የእኅትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበር፤ እርሷና ሴት ልጆቿ እብሪተኞች፣ ጥጋበኞችና ደንታ ቢሶች ነበሩ፤ ድኾችንና ችግረኞችንም አይረዱም ነበር። 50ኵራተኞች ነበሩ፤ በፊቴ አስጸያፊ ተግባር መፈጸማቸውን ባየሁ ጊዜም አስወገድኋቸው። 51ሰማርያ አንቺ ያደረግሽውን ኀጢአት ግማሹን እንኳ አልሠራችም። አንቺ ግን ከእነርሱ የባሰ አስጸያፊ ተግባር በመፈጸምሽ፣ በዚህ ሁሉ እኅቶችሽን ጻድቃን አስመሰልሻቸው። 52እኅቶችሽን እንደ ጻድቃን በማስቈጠርሽ፣ ዕፍረትሽን ተከናነቢ፤ ኀጢአትሽ ከኀጢአታቸው የከፋ ስለሆነ፣ እነርሱ ከአንቺ ይልቅ ጻድቃን ሆኑ። እንግዲህ እኅቶችሽን ጻድቃን ስላስመሰልሻቸው፣ አንቺ ተዋረጂ፤ ዕፍረትሽንም ተከናነቢ።

53“ ‘ነገር ግን የሰዶምንና የሴት ልጆቿን፣ እንዲሁም የሰማርያንና የሴት ልጆቿን ምርኮ እመልሳለሁ፤ የአንቺንም ምርኮ የእነርሱን በምመልስበት ጊዜ እመልሳለሁ። 54ይህም የሚሆነው ለእነርሱ መጽናኛ በመሆንሽ እንድትዋረጂና ባደረግሽው ሁሉ እንድታፍሪ ነው። 55እኅቶችሽ ሰዶምና ሴት ልጆቿ እንዲሁም ሰማርያና ሴት ልጆቿ ቀድሞ ወደ ነበሩበት ሁኔታ ይመለሳሉ፤ አንቺና ሴት ልጆችሽም ቀድሞ ወደ ነበራችሁበት ሁኔታ ትመለሳላችሁ። 56በታበይሽበት ወቅት የእኅትሽን የሰዶምን ስም ለመጥራት እንኳ ፈቃደኛ አልነበርሽም፤ 57ይህም ኀጢአትሽ ከመገለጡ በፊት ነበር። አሁን ግን በዙሪያሽ ሆነው ለሚንቁሽ ለኤዶም16፥57 ከብዙዎቹ የዕብራይስጥና የሱርስት የጥንት ቅጆች ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ ሰብዐ ሊቃናትና ቩልጌት ግን አራም ይላሉ ሴት ልጆችና ለጎረቤቶቿ ሁሉ፣ እንዲሁም ለፍልስጥኤም ሴት ልጆች መሣለቂያ ሆነሻል። 58ለብልግናሽና ለአስጸያፊ ተግባርሽ የሚገባውን ቅጣት ትሸከሚያለሽ፤ ይላል እግዚአብሔር

59“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ቃል ኪዳኔን በማፍረስ መሐላዬን ንቀሻልና ተገቢውን ቅጣት ከእኔ ዘንድ ትቀበያለሽ። 60ነገር ግን በልጅነትሽ ጊዜ ከአንቺ ጋር የገባሁትን ቃል ኪዳን ዐስባለሁ፤ ለዘላለምም የሚኖር ቃል ኪዳን ከአንቺ ጋር እመሠርታለሁ። 61ከአንቺ ታላላቅ የሆኑትንና ታናናሽ የሆኑትን እኅቶችሽን ስትቀበዪ፣ አካሄድሽን ታስቢአለሽ፤ ታፍሪአለሽም። ሴት ልጆች እንዲሆኑሽም እነርሱን ለአንቺ እሰጣለሁ፤ ከአንቺ ጋር በገባሁት ቃል ኪዳን መሠረት ግን አይደለም። 62ስለዚህ ከአንቺ ጋር ቃል ኪዳኔን ዐድሳለሁ፤ በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቂአለሽ። 63ያደረግሽውን ሁሉ ይቅር ባልሁሽ ጊዜ፣ በደልሽ ትዝ ሲልሽ ታፍሪያለሽ፤ ከውርደትሽም የተነሣ አፍሽን ከቶ አትከፍቺም፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’ ”

Thai New Contemporary Bible

เอเสเคียล 16:1-63

คำอุปมาเรื่องความไม่ซื่อสัตย์ของกรุงเยรูซาเล็ม

1พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าว่า 2“บุตรมนุษย์เอ๋ย จงประจันหน้ากับเยรูซาเล็มเพราะเรื่องการกระทำอันน่าชิงชังของนาง 3และจงกล่าวว่า ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสแก่เยรูซาเล็มดังนี้ว่า บรรพบุรุษและชาติกำเนิดของเจ้าอยู่ในดินแดนคานาอัน บิดาของเจ้าเป็นชาวอาโมไรต์และมารดาเป็นชาวฮิตไทต์ 4วันที่เจ้าเกิดมา ไม่มีใครตัดสายสะดือให้ ไม่มีใครอาบน้ำให้สะอาด ไม่มีใครเอาเกลือถูตัวหรือเอาผ้าอ้อมพันให้ 5ไม่มีใครเหลียวแลสงสารเจ้า หรือเมตตาพอที่จะทำสิ่งเหล่านี้ให้เจ้า เจ้ากลับถูกทิ้งไว้กลางทุ่ง เพราะวันที่เจ้าเกิดมา เจ้าก็เป็นที่รังเกียจเดียดฉันท์

6“ ‘แล้วเราผ่านไปเห็นเจ้าดิ้นไปมาเนื้อตัวโชกเลือด เราก็พูดกับเจ้าซึ่งนอนจมกองเลือดอยู่ว่า “จงมีชีวิตอยู่!” 7เราจะทำให้เจ้าเจริญเติบโตเหมือนต้นไม้กลางทุ่ง เจ้าเติบใหญ่จนกลายเป็นสาว16:7 หรือเพชรน้ำเอกทรวงอกเต่งตึงขึ้นและผมก็ยาว แต่เจ้าก็ยังล่อนจ้อนและเปลือยอยู่

8“ ‘ต่อมาเมื่อเราผ่านไปและมองดูเจ้า ก็เห็นว่าเจ้าโตพอที่จะมีความรักแล้ว เราจึงคลี่มุมชายเสื้อของเราคลุมกายเจ้า และปกปิดความเปลือยเปล่าของเจ้าไว้ เราให้คำปฏิญาณและได้ทำพันธสัญญากับเจ้า และเจ้าก็เป็นกรรมสิทธิ์ของเรา พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น

9“ ‘เราได้อาบน้ำให้เจ้า ชำระล้างเลือดจากตัวเจ้าและเอาน้ำมันชโลมให้เจ้า 10เราเอาชุดปักและรองเท้าหนังสวมให้เจ้า ให้เจ้าแต่งกายด้วยผ้าลินินเนื้อดี คลุมกายเจ้าด้วยอาภรณ์ราคาแพง 11เราตกแต่งเจ้าด้วยเพชรนิลจินดา สวมกำไลมือและสร้อยคอให้ 12ใส่ห่วงจมูก ตุ้มหู และสวมมงกุฎงามให้ 13เจ้าจึงงดงามด้วยทองคำและเงิน เสื้อผ้าอาภรณ์ของเจ้าทำด้วยผ้าลินินเนื้อดี ผ้าราคาแพง และผ้าปัก อาหารของเจ้าคือแป้งละเอียด น้ำผึ้ง และน้ำมันมะกอก เจ้ากลายเป็นคนสวยงามมากและรุ่งโรจน์ขึ้นเป็นราชินี 14และชื่อเสียงของเจ้าก็เลื่องลือไปในหมู่ประชาชาติเนื่องด้วยความสวยงามของเจ้า เพราะความโอ่อ่าตระการที่เรามอบให้นั้นทำให้เจ้างามเพียบพร้อม พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น

15“ ‘แต่เจ้าวางใจในความงามของตัวเอง และใช้ชื่อเสียงของเจ้าทำตัวเป็นหญิงโสเภณี เจ้าโปรยเสน่ห์ให้ทุกคนที่ผ่านไปมาและทอดกายให้เขา16:15 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูฉบับหนึ่งว่าผ่านไปมา เรื่องแบบนี้ไม่น่าจะเกิดขึ้น 16เจ้าเอาอาภรณ์บางส่วนของเจ้าไปทำให้สถานบูชาบนที่สูงมีสีสันฉูดฉาด ที่ซึ่งเจ้าใช้ขายเนื้อขายตัว สิ่งเหล่านี้ไม่น่าเกิดขึ้นและไม่น่าเป็นไปได้ 17เจ้ายังเอาเพชรนิลจินดาชั้นเลิศซึ่งเรามอบให้ และเครื่องประดับเงินและทองคำของเราไปสร้างรูปเคารพเพศชายสำหรับตน และทำการแพศยากับรูปเคารพเหล่านั้น 18และเจ้านำผ้าปักของเจ้าไปสวมให้รูปเคารพ เอาน้ำมันกับเครื่องหอมของเราไปบูชาต่อหน้ามัน 19ทั้งอาหารที่เราให้เจ้าคือแป้งละเอียด น้ำมันมะกอก และน้ำผึ้ง เจ้าก็เอาไปถวายเป็นเครื่องหอมบูชาต่อหน้าพระเหล่านั้น นี่คือสิ่งที่เกิดขึ้นแล้ว พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น

20“ ‘และเจ้าถึงกับจับลูกชายลูกสาวที่เจ้าคลอดออกมาเพื่อเราไปเซ่นสังเวยเป็นอาหารแก่รูปเคารพต่างๆ การแพศยานอกใจของเจ้ายังไม่พออีกหรือ? 21เจ้าถึงต้องเข่นฆ่าลูกๆ ของเรา และเผาพวกเขา16:21 หรือให้พวกเขาลุยไฟเพื่อบูชายัญแก่รูปเคารพ 22ตลอดการกระทำอันน่าชิงชังและการแพศยานอกใจของเจ้า เจ้าไม่ได้ระลึกถึงวัยเยาว์ของเจ้า เมื่อเจ้าเปลือยเปล่าตัวล่อนจ้อนและดิ้นไปดิ้นมาอยู่ในกองเลือดเลย

23“ ‘วิบัติ วิบัติแก่เจ้า พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น นอกเหนือจากความชั่วร้ายทั้งหมดของเจ้าแล้ว 24เจ้ายังได้สร้างเนินสูงให้ตัวเองและสร้างสถานบูชาที่สูงตระหง่านไว้ที่ลานชุมชนทุกแห่ง 25เจ้าสร้างสถานบูชาอันสูงตระหง่านไว้ที่หัวถนนทุกสาย และทำให้ความงามของตนลดค่าลง โดยพลีกายให้ทุกคนที่ผ่านไปมาด้วยความสำส่อนมากยิ่งขึ้น 26เจ้าแพศยาคบชู้กับชาวอียิปต์เพื่อนบ้านผู้มากด้วยราคะ และยั่วยุโทสะของเราด้วยความสำส่อนที่ทวีขึ้นของเจ้า 27ฉะนั้นเราจึงเหยียดมือของเราออกต่อสู้กับเจ้า และลดพรมแดนของเจ้า เรายกเจ้าให้ความโลภโมโทสันของศัตรูของเจ้าคือบรรดาชาวฟีลิสเตีย16:27 ภาษาฮีบรูว่าเหล่าธิดาของชาวฟีลิสเตีย ผู้ตกตะลึงในความประพฤติอันลามกต่ำทรามของเจ้า 28เจ้ายังแพศยาคบชู้กับชาวอัสซีเรียอีกด้วย เพราะเจ้าไม่อิ่มในกาม และแม้หลังจากนั้นเจ้าก็ยังไม่หนำใจ 29แล้วเจ้าก็ทวีความสำส่อนมากยิ่งขึ้น โดยเล่นชู้กับบาบิโลน16:29 หรือเคลเดียดินแดนแห่งพ่อค้าวาณิช แต่ถึงขนาดนี้แล้วเจ้าก็ยังไม่จุใจ

30“ ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศว่า ทำไมเจ้าช่างอ่อนไหวใจง่ายจนทำสิ่งต่างๆ ถึงเพียงนี้ ทำตัวเป็นหญิงแพศยาหน้าด้าน! 31เมื่อเจ้าสร้างเนินต่างๆ ไว้ที่หัวถนน และสถานบูชาที่สูงตระหง่านในลานชุมชนทุกแห่ง เจ้าก็ยังต่างจากหญิงโสเภณีก็ตรงที่เจ้าไม่แยแสค่าจ้าง

32“ ‘เจ้าคือภรรยาแพศยา! เจ้าชื่นชอบคนแปลกหน้ายิ่งกว่าสามีของตนเอง 33หญิงโสเภณีทุกคนได้รับค่าจ้าง แต่เจ้าให้ของกำนัลแก่ชู้รักทั้งปวง ให้สินบนจ้างเขามาหาเจ้าจากทุกหนทุกแห่ง เพื่อสนองราคะตัณหาของเจ้า 34ฉะนั้นในการแพศยาของเจ้า เจ้าจึงแตกต่างจากโสเภณีอื่นๆ คือไม่มีใครตามจีบเอาใจเจ้า เจ้าแตกต่างมากเพราะว่าเจ้ายอมจ่ายค่าจ้าง แต่ไม่ได้อะไรตอบแทน

35“ ‘ฉะนั้นหญิงแพศยาเอ๋ย จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า! 36พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เนื่องจากเจ้าโปรยหว่านราคะตัณหา16:36 หรือความมั่งคั่ง และเผยความเปลือยเปล่าของตนโดยการสำส่อนกับชู้รักทั้งหลาย และเนื่องจากรูปเคารพอันน่าชิงชังของเจ้า รวมถึงการเซ่นสังเวยเลือดลูกๆ ของเจ้าแก่พระเหล่านั้น 37ฉะนั้นเราจะรวบรวมชู้รักทุกคนที่เจ้าชื่นชอบ ทั้งผู้ที่เจ้ารักและผู้ที่เจ้าเกลียด เราจะรวบรวมเขาจากทุกด้านมาเล่นงานเจ้า เราจะริบทุกสิ่งจากเจ้าไปต่อหน้าพวกเขา และพวกเขาทุกคนจะเห็นความเปลือยเปล่าของเจ้า 38เราจะตัดสินลงโทษเจ้าในฐานะผู้หญิงที่ล่วงประเวณีและฆ่าคน เราจะทำให้เจ้าโชกเลือดด้วยความกริ้วและความหึงหวงของเรา 39แล้วเราจะมอบเจ้าแก่บรรดาชู้รักของเจ้า พวกเขาจะทลายเนินสูง และทำลายสถานบูชาที่สูงตระหง่านของเจ้า พวกเขาจะทำให้เจ้าล่อนจ้อน และริบเอาเพชรนิลจินดาสวยๆ งามๆ ไป และเปลื้องอาภรณ์ของเจ้าออก ทิ้งเจ้าไว้ให้เปลือยเปล่า 40พวกเขาจะยกขบวนมาสู้กับเจ้า ซึ่งจะขว้างก้อนหินใส่เจ้าและจะฟาดฟันเจ้าออกเป็นชิ้นๆ ด้วยดาบของพวกเขา 41พวกเขาจะเผาบ้านเรือนของเจ้า และลงโทษเจ้าต่อหน้าต่อตาผู้หญิงมากมาย เราจะยุติการแพศยาของเจ้าและเจ้าจะไม่จ่ายค่าจ้างให้บรรดาชู้รักของเจ้าอีกต่อไป 42เมื่อนั้นโทสะที่เรามีต่อเจ้าจะยุติลง และความหึงหวงของเราจะหันเหไปจากเจ้า เราจะสงบอารมณ์และจะไม่โกรธอีก

43“ ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศว่า เพราะเจ้าไม่ได้ระลึกถึงวัยเยาว์ของเจ้า แต่ยั่วโมโหเราด้วยสิ่งทั้งหมดนี้ แน่นอนเราจะตอบแทนเจ้าให้สาสมกับสิ่งที่เจ้าทำลงไป เจ้าไม่ได้เพิ่มความลามกต่ำทรามเข้ากับการกระทำอันน่าชิงชังทั้งหลายของเจ้าหรอกหรือ?

44“ ‘ทุกคนที่ยกภาษิตมากล่าว จะกล่าวถึงเจ้าด้วยภาษิตที่ว่า “แม่เป็นอย่างไร ลูกสาวก็เป็นอย่างนั้น” 45เจ้าเป็นลูกแท้ๆ ของแม่เจ้า ผู้เกลียดชังสามีกับลูกๆ ของตน และเจ้าเป็นน้องแท้ๆ ของพี่สาวเจ้า ผู้เกลียดชังสามีกับลูกๆ ของตน แม่ของเจ้าเป็นชาวฮิตไทต์และพ่อของเจ้าเป็นชาวอาโมไรต์ 46พี่สาวของเจ้าคือสะมาเรียผู้อาศัยอยู่ทางเหนือกับลูกสาวทั้งหลายของนาง น้องสาวของเจ้าคือโสโดมซึ่งอาศัยอยู่ทางใต้กับลูกสาวทั้งหลายของนาง 47เจ้าไม่เพียงแต่ดำเนินในวิถีทางอันชั่วร้ายของพวกเขา และเลียนแบบการกระทำอันน่าชิงชังของพวกเขาเท่านั้น แต่ไม่นานวิถีทั้งปวงของเจ้าก็ต่ำทรามยิ่งกว่าพวกเขาเสียอีก 48พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เรามีชีวิตอยู่แน่ฉันใด โสโดมน้องสาวของเจ้ากับลูกๆ ของนางยังไม่เคยทำสิ่งที่เจ้ากับลูกสาวทั้งหลายของเจ้าทำลงไปฉันนั้น

49“ ‘บัดนี้โสโดมน้องสาวของเจ้ามีบาปคือ นางกับลูกๆ ที่หยิ่งยโสได้รับการบำรุงบำเรอเกินขนาดและไม่มีเรื่องทุกข์ร้อนอันใด พวกเขาไม่ช่วยเหลือคนยากจนขัดสน 50เขาจองหองและทำสิ่งที่น่าชิงชังต่อหน้าเรา ฉะนั้นเราจึงกำจัดพวกเขาไปตามที่เจ้าได้เห็นแล้ว 51สะมาเรียทำบาปไม่ได้ครึ่งหนึ่งของเจ้า เจ้าทำสิ่งที่น่าชิงชังยิ่งกว่าที่พวกเขาทำ การกระทำทั้งสิ้นของเจ้าพลอยทำให้พี่สาวน้องสาวของเจ้าดูชอบธรรมขึ้น 52เจ้าจงทนรับความอับอายขายหน้าไป เพราะเจ้าทำให้พี่สาวน้องสาวของเจ้าดูดีกว่า เนื่องจากบาปของเจ้าชั่วช้าเลวทรามยิ่งกว่าของพวกเขา พวกเขาจึงดูเป็นฝ่ายชอบธรรม ฉะนั้นจงละอายแก่ใจและทนรับความอัปยศอดสูของเจ้าไปเถิด เพราะเจ้าทำให้พี่สาวน้องสาวของเจ้าดูชอบธรรม

53“ ‘แต่เราจะคืนความรุ่งโรจน์ให้แก่โสโดมกับบรรดาลูกสาวของนาง คืนให้แก่สะมาเรียกับบรรดาลูกสาวของนาง และคืนความรุ่งโรจน์ให้แก่เจ้าด้วย 54เพื่อเจ้าจะทนรับความอับอายขายหน้าและละอายใจในสิ่งทั้งปวงที่พวกเจ้าทำลงไป ซึ่งเป็นการปลอบประโลมพวกเขา 55แล้วพี่สาวน้องสาวของเจ้าคือ โสโดมกับลูกๆ และสะมาเรียกับลูกๆ จะคืนสู่สภาพเดิม และเจ้ากับลูกๆ ก็จะคืนสู่สภาพเดิมด้วย 56เจ้าไม่ยอมแม้แต่จะเอ่ยถึงโสโดมน้องสาวของเจ้าในวันแห่งความหยิ่งผยองของเจ้า 57ก่อนหน้าความชั่วร้ายของเจ้าจะถูกเปิดโปง ถึงอย่างนั้นตอนนี้เจ้าก็ถูกดูหมิ่นเหยียดหยามโดยธิดาทั้งหลายแห่งเอโดม16:57 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูบางฉบับ และฉบับ LXX. และ Vulg. ว่าอารัมและเพื่อนบ้านทั้งปวงของนาง รวมทั้งธิดาทั้งหลายของชาวฟีลิสเตีย คือคนทั้งปวงรอบตัวเจ้าก็ดูหมิ่นเหยียดหยามเจ้า 58เจ้าจะต้องทนรับผลจากความลามกต่ำทราม และการกระทำอันน่าชิงชังของเจ้า องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

59“ ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เราจะจัดการกับเจ้าอย่างสาสม เพราะเจ้าลบหลู่ดูหมิ่นคำปฏิญาณของเราโดยละเมิดพันธสัญญา 60ถึงกระนั้นเราก็จะระลึกถึงพันธสัญญาที่เราให้ไว้กับเจ้าเมื่อครั้งเจ้ายังเยาว์วัย และเราจะสถาปนาพันธสัญญานิรันดร์กับเจ้า 61แล้วเจ้าจะระลึกถึงวิถีทางของเจ้าและละอายใจ เมื่อเรายกพี่สาวน้องสาวของเจ้าให้เป็นลูกสาวของเจ้า แต่ไม่ใช่ตามพันธสัญญาที่เราให้ไว้กับเจ้า 62ดังนั้นเราจะสถาปนาพันธสัญญาของเราไว้กับเจ้า แล้วเจ้าจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์ 63เมื่อนั้นเราจะลบล้างมลทินบาปให้เจ้าสำหรับทุกสิ่งที่เจ้าทำลงไป เจ้าจะจำได้และละอายใจ ไม่กล้าปริปากอีกเลยเนื่องจากความละอายของเจ้า’ พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศดังนั้น”