ሕዝቅኤል 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 11:1-25

በእስራኤል መሪዎች ላይ የተላለፈ ፍርድ

1መንፈስም ወደ ላይ አነሣኝ፤ ከዚያም በምሥራቅ በኩል ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤት በር አመጣኝ። በበሩም መግቢያ ላይ ሃያ አምስት ሰዎች ነበሩ፤ በእነርሱም መካከል የሕዝቡን መሪዎች የዓዙርን ልጅ ያእዛንያንና የበናያስን ልጅ ፈላጥያንን አየሁ። 2እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “የሰው ልጅ ሆይ፤ እነዚህ ሰዎች ክፋትን የሚያቅዱና በዚህችም ከተማ ላይ ተንኰልን የሚመክሩ ናቸው። 3እነርሱም፣ ‘ቤቶች የሚሠሩበት ጊዜ ቅርብ አይደለምን?11፥3 ወይም ቤቶችን ለመሥራት ጊዜው አሁን አይደለም ይህች ከተማ ድስት ናት፤ እኛም ሥጋ ነን’ ብለዋል። 4ስለዚህ ትንቢት ተናገርባቸው፤ የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር።”

5የእግዚአብሔርም መንፈስ በላዬ ወረደ፤ እንዲህም አለኝ፤ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የእስራኤል ቤት ሆይ፤ እናንተ እንዲህ ብላችኋል፤ እኔ ግን የልባችሁን ሐሳብ ዐውቃለሁ። 6በዚህች ከተማ ብዙ ሰው ገድላችኋል፤ መንገዶቿንም ሬሳ በሬሳ አድርጋችኋል።’

7“ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በዚያ የጣላችኋቸው ሬሳዎች እነርሱ ሥጋ ናቸው፤ ይህችም ከተማ ድስት ናት፤ እናንተን ግን ከውስጧ አወጣችኋለሁ። 8ሰይፍን ፈርታችኋል፤ እኔም ሰይፍ እልክባችኋለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር9ከከተማዪቱ አውጥቼ ለባዕዳን አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፤ ፍርድንም አመጣባችኋለሁ። 10በሰይፍ ትወድቃላችሁ፤ በእስራኤል ድንበር ላይ እፈርድባችኋለሁ፤ በዚያ ጊዜም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። 11ይህች ከተማ ድስት አትሆንላችሁም፤ እናንተም በውስጧ ሥጋ አትሆኑም፤ በእስራኤልም ድንበር ላይ እፈርድባችኋለሁ፤ 12በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ፤ እናንተ በዙሪያችሁ ያሉትን አሕዛብ ሥርዐት ተከተላችሁ እንጂ ትእዛዜን አልፈጸማችሁም ሕጌንም አልጠበቃችሁምና።”

13ትንቢት እየተናገርሁ ሳለ፣ የበናያስ ልጅ ፈላጥያ ሞተ፤ እኔም በግንባሬ ተደፍቼ፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፣ ወዮ! የእስራኤልን ቅሬታ ፈጽመህ ታጠፋለህን?” በማለት በታላቅ ድምፅ ጮኽሁ።

14የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 15“የሰው ልጅ ሆይ፤ ወንድሞችህ፣ የራስህ ዘመዶችና11፥15 ወይም በምርኮ ከአንተ ጋር የነበሩና (ሰብዐ ሊቃናትና ሱርስትን ይመ) የእስራኤል ቤት ሁሉ፤ ‘ከእግዚአብሔር ርቀዋል፤ ይህች ምድር ርስት ሆና ለእኛ ተሰጥታናለች’ ብለው የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች የተናገሩባቸው ናቸው።11፥15 ወይም የኢየሩሳሌም ሰዎች የተናገሩባቸው፣ ከእግዚአብሔር ራቁ

የእስራኤል የመመለስ ተስፋ

16“ስለዚህ እንዲህ በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በአሕዛብ መካከል ብሰድዳቸውም፤ በአገሮች መካከል ብበታትናቸውም፣ በሄዱባቸው አገሮች ሁሉ ለጥቂት ጊዜ መቅደስ ሆኜአቸዋለሁ’ ”።

17“ስለዚህ እንዲህ በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ከአሕዛብ መካከል እሰበስባችኋለሁ፤ ከተበተናችሁባቸው አገሮች እመልሳችኋለሁ፤ የእስራኤልንም ምድር እንደ ገና እሰጣችኋለሁ።’

18“ወደዚያ በተመለሱ ጊዜ የረከሱ ምስሎቿንና ጸያፍ ተግባሯን ያስወግዳሉ። 19የማያወላውል ልብ እሰጣቸዋለሁ፤ አዲስ መንፈስ በውስጣቸው አኖራለሁ፤ ድንጋዩን ልብ ከውስጣቸው አወጣለሁ፤ ሥጋ ልብም እሰጣቸዋለሁ። 20ስለዚህ ትእዛዜን ይፈጽማሉ፤ ሕጌን ይጠብቃሉ። እነርሱ ሕዝቤ ይሆናሉ፤ እኔም አምላካቸው እሆናለሁ። 21ነገር ግን ልባቸው ወደ ረከሱ ምስሎቻቸውና ወደ ጸያፍ ተግባራቸው ያዘነበለውን እንደ ሥራቸው እከፍላቸዋለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።”

22ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ዘረጉ፤ መንኰራኵሮቹም በአጠገባቸው ነበሩ፤ የእስራኤልም አምላክ ክብር በላያቸው ላይ ነበር። 23የእግዚአብሔርም ክብር ከከተማዪቱ ውስጥ ተነሥቶ ወጣ፤ ከከተማዪቱም በስተ ምሥራቅ ካለው ተራራ በላይ ቆም አለ። 24መንፈስም ወደ ላይ አነሣኝ፤ በእግዚአብሔርም መንፈስ በተሰጠው ራእይም በባቢሎን11፥24 ወይም ከለዳውያን ምድር ወደ ነበሩት ምርኮኞች አመጣኝ።

ከዚያም ያየሁት ራእይ ከእኔ ወጥቶ ሄደ፤ 25እኔም እግዚአብሔር ያሳየኝን ነገር ሁሉ ለምርኮኞቹ ተናገርሁ።

Thai New Contemporary Bible

เอเสเคียล 11:1-25

การพิพากษาบรรดาผู้นำอิสราเอล

1แล้วพระวิญญาณทรงยกข้าพเจ้าขึ้น นำมายังประตูทิศตะวันออกของพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้า มีชาย 25 คนอยู่ตรงทางเข้าประตูนั้น และในหมู่พวกเขาข้าพเจ้าเห็นยาอาซันยาห์บุตรอัสซูร์และเปลาทียาห์บุตรเบไนยาห์ ทั้งคู่เป็นผู้นำประชากร 2พระองค์ตรัสกับข้าพเจ้าว่า “บุตรมนุษย์เอ๋ย คนเหล่านี้คือคนที่คิดแผนชั่วและให้คำปรึกษาอันร้ายกาจในกรุงนี้ 3พวกเขากล่าวว่า ‘ใกล้จะถึงเวลาที่เราจะสร้างบ้านขึ้นแล้วไม่ใช่หรือ?11:3 หรือนี่ไม่ใช่เวลาที่จะสร้างบ้าน กรุงนี้เป็นเหมือนหม้อและเราเป็นเหมือนเนื้อที่ปลอดภัยอยู่ในนั้น’ 4ฉะนั้นจงเผยพระวจนะกล่าวโทษเขาเถิด บุตรมนุษย์เอ๋ย จงเผยพระวจนะ”

5แล้วพระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้าเสด็จมาเหนือข้าพเจ้า พระองค์ตรัสสั่งให้ข้าพเจ้ากล่าวว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า พงศ์พันธุ์อิสราเอลเอ๋ย เจ้าพูดเช่นนั้น แต่เรารู้ว่าเจ้าคิดอะไรอยู่ 6เจ้าได้ฆ่าคนมากมายในกรุงนี้ มีคนตายเกลื่อนถนนไปหมด

7“ดังนั้นพระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า ซากศพที่เจ้าทิ้งเกลื่อนคือเนื้อ และกรุงนี้คือหม้อ แต่เราจะขับไล่เจ้าออกไปจากที่นี่ 8เจ้ากลัวดาบ เราก็จะนำดาบมายังเจ้า พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศไว้ดังนี้ 9เราจะขับไล่เจ้าออกจากกรุงนี้และมอบเจ้าให้แก่คนต่างชาติ เราจะลง โทษเจ้า 10เจ้าจะล้มตายด้วยดาบและเราจะพิพากษาเจ้าที่ชายแดนอิสราเอล เมื่อนั้นเจ้าจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์ 11กรุงนี้จะไม่ใช่หม้อสำหรับเจ้า และเจ้าก็ไม่ใช่เนื้อในหม้อนี้ เราจะพิพากษาเจ้าที่ชายแดนอิสราเอล 12และเจ้าจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์ เพราะเจ้าไม่ได้ปฏิบัติตามกฎหมายของเราและไม่ได้รักษาบทบัญญัติของเรา แต่กลับประพฤติตามแบบอย่างของชนชาติทั้งหลายที่อยู่รายรอบเจ้า”

13ขณะที่ข้าพเจ้าเผยพระวจนะอยู่ เปลาทียาห์บุตรเบไนยาห์ก็สิ้นชีวิตไป ข้าพเจ้าจึงซบหน้าลงและร้องเสียงดังว่า “โอ ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต! พระองค์จะทรงทำลายล้างชนอิสราเอลที่เหลืออยู่นี้เสียสิ้นเลยหรือ?”

14พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าว่า 15“บุตรมนุษย์เอ๋ย ผู้คนในเยรูซาเล็มได้กล่าวถึงญาติพี่น้องร่วมสายเลือดเดียวกันกับเจ้า11:15 หรือผู้ตกเป็นเชลยเช่นเดียวกับเจ้าและพงศ์พันธุ์อิสราเอลทั้งหมดว่า ‘พวกเขา11:15 หรือจงอยู่ห่างไกลจากองค์พระผู้เป็นเจ้า ดินแดนนี้จึงตกเป็นกรรมสิทธิ์ของพวกเรา’

พระสัญญาว่าอิสราเอลจะกลับคืนมา

16“ฉะนั้นจงกล่าวว่า ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า ถึงแม้เราขับไล่พวกเขาไปไกลๆ ไปอยู่ในหมู่ประชาชาติต่างๆ และทำให้พวกเขากระจัดกระจายไปสู่นานาประเทศ แต่อีกไม่นานเราก็จะเป็นสถานนมัสการสำหรับพวกเขาในประเทศที่เขาไปนั้น’

17“ฉะนั้นจงกล่าวว่า ‘พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสดังนี้ว่า เราจะรวบรวมพวกเจ้าจากประชาชาติต่างๆ และนำเจ้ากลับมาจากนานาประเทศที่เราทำให้เจ้ากระจัดกระจายไปนั้น ทั้งเราจะคืนดินแดนอิสราเอลให้เจ้าอีกครั้ง’

18“พวกเขาจะกลับมาและกำจัดเทวรูปอันชั่วช้าสามานย์และรูปเคารพอันน่าชิงชังให้หมดไป 19เราจะให้พวกเขามีใจเดียว และมีจิตวิญญาณใหม่ เราจะถอนใจหินของพวกเขาออกและให้ใจเนื้อแก่พวกเขา 20แล้วพวกเขาจะปฏิบัติตามกฎหมายของเรา และจะใส่ใจรักษาบทบัญญัติของเรา พวกเขาจะเป็นประชากรของเรา และเราจะเป็นพระเจ้าของพวกเขา 21แต่ส่วนผู้ที่มอบใจให้เทวรูปอันชั่วช้าสามานย์และรูปเคารพอันน่าชิงชัง เราจะตอบแทนให้สาสมกับที่พวกเขาทำลงไป พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตประกาศไว้ดังนี้”

22จากนั้นเครูบซึ่งมีวงล้ออยู่ข้างๆ ก็กางปีกออก และพระเกียรติสิริของพระเจ้าแห่งอิสราเอลอยู่เหนือเหล่าเครูบ 23พระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้า เคลื่อนขึ้นจากในกรุงนั้น และหยุดนิ่งอยู่เหนือภูเขาด้านตะวันออกของกรุง 24ในนิมิตซึ่งพระวิญญาณของพระเจ้าประทาน พระวิญญาณทรงยกข้าพเจ้าขึ้น และพาข้าพเจ้ากลับมายังเหล่าเชลยในบาบิโลน11:24 หรือเคลเดีย

แล้วนิมิตที่ข้าพเจ้าเห็นก็ขึ้นไปจากข้าพเจ้า 25ข้าพเจ้าจึงแจ้งทุกสิ่งที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงสำแดงแก่ข้าพเจ้าให้บรรดาเชลยฟัง