ሕዝቅኤል 1 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 1:1-28

ሕያዋኑ ፍጡራንና የእግዚአብሔር ክብር

1በሠላሳኛው ዓመት፣1፥1 ወይም ዓመቴ በአራተኛው ወር፣ በአምስተኛው ቀን፣ በኮቦር ወንዝ አጠገብ በምርኮኞች መካከል ሳለሁ፣ ሰማያት ተከፈቱ፤ እኔም የእግዚአብሔርን ራእይ አየሁ።

2ንጉሡ ዮአኪን በተማረከ በአምስተኛው ዓመት፣ በአምስተኛው ቀን፣ 3በባቢሎናውያን1፥3 ወይም በከለዳውያን ምድር በኮቦር ወንዝ አጠገብ፣ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ቡዝ ልጅ፣1፥3 ወይም ወደ ካህኑ ቡዝ ልጅ ወደ ሕዝቅኤል ወደ ካህኑ ወደ ሕዝቅኤል መጣ፤ በዚያ የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ነበረች።

4እኔም አየሁ፤ ስመለከትም፣ እነሆ ዐውሎ ነፋስ ከሰሜን በኩል መጣ፤ ይኸውም በታላቅ ብርሃን የተከበበ፣ መብረቅን የሚረጭ ታላቅ ደመና ነበረ፤ የእሳቱም መኻል የጋለ ብረት ይመስል ነበር። 5በእሳቱም ውስጥ የአራት ሕያዋን ፍጡራን አምሳያ ነበረ፤ መልካቸውም የሰው ቅርጽ ይመስል ነበር። 6እያንዳንዳቸውም አራት አራት ፊትና አራት አራት ክንፍ ነበራቸው። 7እግራቸው ቀጥ ያለ ነበር፤ ኰቴያቸውም እንደ ጥጃ ኰቴ ያለ ሲሆን፣ እንደ ተወለወለ ናስም ያብለጨልጭ ነበር። 8በአራቱ ጐኖቻቸው ባሉት ክንፎቻቸው ሥር የሰው እጅ ነበራቸው። አራቱም ፊቶችና ክንፎች ነበሯቸው፤ 9ክንፎቻቸውም እርስ በርስ ይነካኩ ነበር። እያንዳንዱም ቀጥ ብሎ ይሄድ ነበር፤ ወደ ኋላቸውም ዞር ብለው አይመለከቱም ነበር።

10ፊታቸውም እንዲህ ነበር፤ አራቱም እያንዳንዳቸው የሰው ፊት ነበራቸው፤ በቀኝ በኩል የአንበሳ ፊት፣ በግራ በኩልም የበሬ ፊት ነበራቸው፤ እያንዳንዳቸውም ደግሞ የንስር ፊት ነበራቸው። 11እንግዲህ ፊታቸው ይህን ይመስል ነበር፤ ክንፋቸውም ወደ ላይ ተዘርግቶ ነበር፤ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ክንፍ ነበራቸው፤ የእያንዳንዱም ክንፍ የሌላውን ክንፍ ይነካ ነበር፤ ሁለቱ ክንፎቻቸው ሰውነታቸውን ይሸፍኑ ነበር። 12እያንዳንዱ ቀጥ ብሎ ወደ ፊት ይሄድ ነበር፤ ወደ ኋላም ሳይዞር መንፈስ ወደሚሄድበት ሁሉ ይሄድ ነበር። 13የሕያዋን ፍጡራኑ መልክም እንደሚነድ የከሰል ፍምና የተቀጣጠለ ችቦ ይመስል ነበር፤ በፍጡራኑ መካከል እሳት ወዲያ ወዲህ ይንቀሳቀስ ነበር፤ ብርሃኑም ደማቅ ነበር፤ ከእሳቱም ውስጥ መብረቅ ይወጣ ነበር። 14ፍጡራኑም እንደ መብረቅ ብልጭታ ፍጥነት ወዲያ ወዲህ ይወረወሩ ነበር።

15ሕያዋን ፍጡራኑን ስመለከታቸው፣ አራት ፊቶች ባሉት በእያንዳንዱ ፍጡር አጠገብ አንዳንድ መንኰራኵር በምድር ላይ አየሁ። 16የመንኰራኵሮቹ መልክና አሠራር እንዲህ ነበር፤ እንደ ቢረሌ ያንጸባርቁ ነበር፤ የአራቱም ቅርጽ ተመሳሳይ ሆኖ፤ እያንዳንዱ መንኰራኵር በመንኰራኵር ውስጥ ተሰክቶ የተሠራ ይመስል ነበር። 17በሚሄዱበት ጊዜም፣ ፍጡራኑ ወደሚዞሩበት ወደ አራቱ አቅጣጫ ሁሉ መንቀሳቀስ ይችሉ ነበር፤ ፍጡራኑ በሚሄዱበትም ጊዜ መንኰራኵሮቹ ወዲያና ወዲህ1፥17 ወይም ወደ ሌላ አይሉም ነበር። 18የመንኰራኵሮቹ ክብ ጠርዝ ረዥምና አስፈሪ ነበር፤ የአራቱም መንኰራኵሮች ክብ ጠርዝ ዙሪያውን በዐይኖች የተሞላ ነበር።

19ሕያዋኑ ፍጡራን ሲንቀሳቀሱ፣ በአጠገባቸው ያሉ መንኰራኵሮችም ይንቀሳቀሱ ነበር፤ ሕያዋኑ ፍጡራን ከምድር ከፍ ከፍ ሲሉ፣ መንኰራኵሮቹም አብረዋቸው ከፍ ከፍ ይሉ ነበር። 20መንፈስ ወደሚሄድበት ሁሉ ይሄዳሉ፤ የሕያዋኑ ፍጡራን መንፈስ በውስጣቸው ስላለ መንኰራኵሮቹ አብረዋቸው ይነሣሉ፤ 21ፍጡራኑ ሲንቀሳቀሱ ይንቀሳቀሳሉ፤ ፍጡራኑ ቀጥ ብለው ሲቆሙ እነርሱም ይቆማሉ፤ ፍጡራኑ ከምድር ከፍ ከፍ ሲሉ፣ የሕያዋኑ ፍጡራን መንፈስ በውስጣቸው ስላለ መንኰራኵሮቹ አብረዋቸው ይነሣሉ።

22ከሕያዋኑ ፍጡራን ራስ በላይ የሚያስፈራና፤ እንደ በረዶ የሚያንጸባርቅ ጠፈር የሚመስል ነገር ነበር። 23ከጠፈሩም በታች የአንዱ ክንፍ ወደ ሌላው ተዘርግቶ ነበር፤ እያንዳንዱም ሰውነቱን የሚሸፍንበት ሁለት ክንፍ ነበረው። 24ፍጡራኑ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ የክንፎቻቸውን ድምፅ ሰማሁ፤ ድምፁም እንደሚጐርፍ ውሃ ጩኸት፣ ሁሉን እንደሚችል1፥24 በዕብራይስጡ ሻዳይ ይላል አምላክ ድምፅና እንደ ሰራዊት ውካታ ነበር። መንቀሳቀሳቸውን ሲያቆሙም ክንፎቻቸውን ዝቅ ያደርጉ ነበር።

25መንቀሳቀሳቸውን አቁመው ክንፎቻቸውን ዝቅ እንዳደረጉ፣ ከራሳቸው በላይ ካለው ጠፈር ድምፅ ተሰማ። 26ከራሳቸው በላይ ካለው ጠፈር ከፍ ብሎ የሰንፔር1፥26 ወይም ላፒስ ላዙሊ ዙፋን የሚመስል ነገር ነበር፤ በዙፋኑም ላይ የሰው መልክ የሚመስል ነበር። 27ወገቡ ከሚመስለው ጀምሮ ወደ ላይ በእሳት መካከል እንዳለ የጋለ ብረት፣ ከወገቡም በታች እሳት ይመስል እንደ ነበር አየሁ፤ ደማቅ ብርሃንም በዙሪያው ነበር። 28በዝናብ ቀን በደመና ውስጥ እንደሚታየው ቀስተ ደመና በዙሪያው ያለው ጸዳል እንዲሁ ነበር።

ይህም የእግዚአብሔር ክብር መልክ አምሳያ ነበረ። ባየሁትም ጊዜ በግንባሬ ተደፋሁ፤ የአንድ ተናጋሪን ድምፅ ሰማሁ።

Persian Contemporary Bible

حزقيال 1:1‏-28

رؤيای حزقيال نبی

1‏-3در روز پنجم ماه چهارم سال سی‌ام، كه پنج سال از تبعيد يهوياكين پادشاه می‌گذشت، ناگهان آسمان به روی حزقيال، پسر بوزی، گشوده شد و خدا رؤياهايی به او نشان داد. حزقيال كاهنی بود كه با يهوديان تبعيدی، كنار رود خابور در بابل زندگی می‌كرد. حزقيال چنين تعريف می‌كند:

4در يكی از اين رؤياها، طوفانی ديدم كه از شمال به طرف من می‌آمد. پيشاپيش آن، ابر بزرگی از آتش در حركت بود، هاله‌ای از نور دور آن بود و در درون آن، چيزی مانند فلزی براق، می‌درخشيد. 5سپس، از ميان ابر، چهار موجود عجيب ظاهر شدند كه شبيه انسان بودند. 6ولی هر يک، چهار صورت و دو جفت بال داشتند! 7پاهايشان نيز مثل پای انسان بود، ولی پنجهٔ پايشان به سم گوساله شباهت داشت و مانند فلزی براق، می‌درخشيد. 8زير هر يک از بالهايشان، دستهايی می‌ديدم مثل دست انسان. 9انتهای بالهای آن چهار موجود زنده به همديگر وصل بود. آنها مستقيم حركت می‌كردند بدون آنكه برگردند.

10هر يک از آنها چهار صورت داشت: در جلو، صورت انسان؛ در طرف راست، صورت شير؛ در طرف چپ، صورت گاو و در پشت، صورت عقاب. 11هر كدام دو جفت بال داشتند، كه يک جفت باز بود و به نوک بالهای موجودات پهلويی می‌رسيد و جفت ديگر، بدنشان را می‌پوشاند. 12هر جا روحشان می‌رفت، آنها هم مستقيم می‌رفتند بدون آنكه رويشان را برگردانند.

13در ميان اين موجودات زنده، چيزهايی شبيه به زغال افروخته با مشعل روشن، در حال حركت بودند. از ميان آنها، برق می‌جهيد. 14آن موجودات زنده نيز به سرعت برق به عقب و جلو حركت می‌كردند.

15در همان حال كه به اين چهار موجود زنده خيره شده بودم، زير آنها و بر روی زمين، چهار چرخ ديدم زير هر موجود يک چرخ. 16چرخها مانند زبرجد می‌درخشيدند و همه مثل هم بودند. داخل هر چرخ، چرخ ديگری نيز قرار داشت. 17برای همين می‌توانستند بی‌آنكه مجبور باشند دور بزنند، به هر سو كه بخواهند، بروند. 18آن چهار چرخ دارای لبه‌ها و پره‌هايی بودند و دور لبه‌ها پر از چشم بود.

19‏-21وقتی آن موجودات زنده حركت می‌كردند، چرخها هم با آنها حركت می‌كردند. هنگامی كه آنها از زمين برمی‌خاستند، چرخها نيز برمی‌خاستند، و وقتی می‌ايستادند، چرخها هم می‌ايستادند، چون روح آن چهار موجود در چرخها نيز قرار داشت. پس موجودات زنده و چرخها تحت هدايت روحشان بودند.

22بالای سر موجودات زنده، چيزی شبيه به يک صفحهٔ بزرگ گسترده شده بود كه مانند بلور می‌درخشيد و انسان را به هراس می‌انداخت. 23زير اين صفحه، دو بال هر موجود زنده طوری باز بود كه به بالهای موجود ديگر می‌رسيد، و دو بال ديگر، بدنشان را می‌پوشانيد. 24وقتی پرواز می‌كردند، صدای بالهايشان مانند غرش امواج ساحل يا همچون صدای خدا و يا همانند فرياد يک لشكر بزرگ بود. وقتی می‌ايستادند، بالهايشان را پايين می‌آوردند. 25هر بار كه می‌ايستادند، از صفحهٔ بلورين بالای سر آنها صدايی به گوش می‌رسيد.

26بر فراز صفحهٔ بالای سرشان، چيزی شبيه به يک تخت سلطنتی زيبا قرار داشت كه گويی از ياقوت كبود ساخته شده بود و بر روی آن تخت، وجودی نشسته بود كه به يک انسان شباهت داشت. 27‏-28از كمر به بالا همچون فلزی غوطه‌ور در آتش می‌درخشيد، و از كمر به پايين، مانند شعله‌های آتش، تابان بود. دورتادورش را نيز نوری درخشان فرا گرفته بود كه همهٔ رنگهای رنگين‌كمان در آن ديده می‌شد.

حضور پرجلال خداوند بدين‌گونه بر من ظاهر شد. هنگامی كه آن منظره را ديدم، به خاک افتادم. آنگاه صدای كسی را شنيدم كه با من سخن می‌گفت.