ሐጌ 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሐጌ 2:1-23

ቃል የተገባው የአዲሱ ቤት ክብር

1በሰባተኛው ወር፣ በሃያ አንደኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል በነቢዩ በሐጌ በኩል እንዲህ ሲል መጣ፤ 2“ለይሁዳ ገዥ ለሰላትያል ልጅ ለዘሩባቤል፣ ለሊቀ ካህናቱ ለኢዮሴዴቅ ልጅ ለኢያሱ፣ ከምርኮ ለተረፈውም ሕዝብ እንዲህ ብለህ ተናገር፤ እንዲህም ብለህ ጠይቃቸው፤ 3‘ይህን ቤት በቀድሞ ክብሩ ሳለ ያየ ከመካከላችሁ ማን አለ? አሁንስ ምን መስሎ ይታያችኋል? ይህ በፊታችሁ ምንም እንዳይደለ የሚቈጠር አይደለምን?’ 4እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘አሁን ግን ዘሩባቤል ሆይ፤ በርታ፤ የሊቀ ካህናቱ የኢዮሴዴቅ ልጅ ኢያሱ ሆይ፤ በርታ፤ እናንተም የምድሪቱ ሕዝብ ሁሉ በርቱ’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና ሥሩ’ ይላል ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር5‘ከግብፅ በወጣችሁ ጊዜ የገባሁላችሁ ቃል ይህ ነው፤ መንፈሴም በመካከላችሁ ይሆናልና አትፍሩ።’

6“ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘በቅርብ ጊዜ እንደ ገና ሰማያትንና ምድርን፣ ባሕሩንና የብሱን አንድ ጊዜ አናውጣለሁ። 7ሕዝቦችን ሁሉ አናውጣለሁ፤ የሕዝቦችም ሀብት ሁሉ ወደዚህ ይመጣል፤ ይህንም ቤት በክብር እሞላዋለሁ’ ይላል ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር8‘ብሩ የእኔ ነው፤ ወርቁም የእኔ ነው’ ይላል ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር ጸባኦት፤ 9‘የዚህ የአሁኑ ቤት ክብር ከቀድሞው ቤት ክብር ይበልጣል’ ይላል ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር ጸባኦት፤ ‘በዚህም ቦታ ሰላምን እሰጣለሁ’ ይላል ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር ጸባኦት።”

ተግሣጽና በረከት

10ዳርዮስ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት፣ በዘጠነኛው ወር፣ በሃያ አራተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል በነቢዩ በሐጌ በኩል እንዲህ ሲል መጣ፤ 11እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘ሕጉ ምን እንደሚል ካህናቱን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፤ 12አንድ ሰው የተቀደሰውን ሥጋ በልብሱ ዕጥፋት ቢይዝ፣ ያም ዕጥፋት እንጀራ ወይም ወጥ፣ የወይን ጠጅ ወይም ዘይት ወይም ሌላ ምግብ ቢነካ የተቀደሰ ይሆናልን?’ ”

ካህናቱም፣ “የተቀደሰ አይሆንም” ብለው መለሱ።

13ሐጌም፣ “ሬሳ በመንካቱ የረከሰ ሰው፣ ከእነዚህ አንዱን ቢነካ፣ የተነካው ነገር ይረክሳልን?” ሲል ጠየቀ።

ካህናቱም፣ “አዎን፣ ይረክሳል” ሲሉ መለሱ።

14ከዚያም ሐጌ እንዲህ አለ፤ “ ‘ይህ ሕዝብና ይህ ወገንም በፊቴ እንደዚሁ ነው’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘የእጃቸው ሥራና የሚያቀርቡት ሁሉ የረከሰ ነው’።

15“ ‘እንግዲህ ከዛሬ ጀምራችሁ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ከመነባበሩ በፊት የነበረውን ሁኔታ አስተውሉ።2፥15 ወይም ላለፉት ቀናት እንደ ማለት ነው። 16አንድ ሰው ሃያ መስፈሪያ ወደሚሆን የእህል ክምር በመጣ ጊዜ ዐሥር ብቻ አገኘ፤ አምሳ ማድጋ የወይን ጠጅ ለመቅዳት ወደ መጭመቂያው በሄደ ጊዜ ሃያ ብቻ አገኘ። 17የእጃችሁን ሥራ ሁሉ በዋግ፣ በአረማሞና በበረዶ መታሁት፤ እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም’ ይላል እግዚአብሔር18‘ከዚህ ቀን ጀምሮ፣ ይኸውም ከዘጠነኛው ወር ሃያ አራተኛ ቀን ጀምሮ፣ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሠረት እስከ ተጣለበት ቀን ድረስ ያለውን ዘመን አስተውሉ፤ ልብ ብላችሁም አስቡ፤ 19በጐተራ የቀረ ዘር አሁንም ይገኛልን? የወይኑና የበለሱ ዛፍ፣ የሮማኑና የወይራው ዛፍ እስካሁን አላፈሩም።

“ ‘ከዚህ ቀን ጀምሮ እባርካችኋለሁ።’ ”

እግዚአብሔር ለዘሩባቤል የሰጠው ተስፋ

20በወሩ ሃያ አራተኛ ቀን የእግዚአብሔር ቃል ዳግመኛ እንዲህ ሲል ወደ ሐጌ መጣ፤ 21“ለይሁዳ ገዥ ለዘሩባቤል ሰማያትንና ምድርን እንደማናውጥ ንገረው፤ 22የመንግሥታትን ዙፋን እገለብጣለሁ፤ የባዕዳንን መንግሥታት ኀይል አጠፋለሁ፤ ሠረገሎችንና ሠረገለኞችን እገለብጣለሁ፤ ፈረሶችና ጋላቢዎቻቸውም በገዛ ወንድሞቻቸው ሰይፍ ይወድቃሉ።

23“ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘በዚያን ቀን ባሪያዬ የሰላትያል ልጅ ዘሩባቤል ሆይ፤ እኔ እወስድሃለሁ’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘እንደ ማተሚያ ቀለበቴ አደርግሃለሁ፤ እኔ መርጬሃለሁና’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።”

Thai New Contemporary Bible

ฮักกัย 2:1-23

สง่าราศีของพระนิเวศใหม่ที่ทรงสัญญาไว้

ปีที่สองแห่งรัชกาลกษัตริย์ดาริอัส 1ในวันที่ยี่สิบเอ็ดเดือนที่เจ็ด องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสผ่านผู้เผยพระวจนะฮักกัยว่า 2“จงกล่าวแก่เศรุบบาเบลผู้ว่าการของยูดาห์บุตรเชอัลทิเอล มหาปุโรหิตโยชูวาบุตรเยโฮซาดัก และประชาชนที่เหลืออยู่ จงถามพวกเขาว่า 3‘ใครบ้างในพวกเจ้าที่เหลืออยู่ที่เคยเห็นความโอ่อ่าตระการแต่เดิมของนิเวศนี้? บัดนี้เจ้าเห็นเป็นอย่างไร? รู้สึกว่าเทียบกันไม่ได้เลยใช่ไหม? 4แต่บัดนี้จงเข้มแข็งเถิด เศรุบบาเบลเอ๋ย’ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า ‘จงเข้มแข็งเถิด มหาปุโรหิตโยชูวาบุตรเยโฮซาดักเอ๋ย จงเข้มแข็งเถิด ประชาชนทั้งปวงในดินแดนนี้’ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น ‘และจงทำงานไปเถิด เพราะเราอยู่กับเจ้า’ พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศดังนั้น 5‘ตามที่เราได้ทำพันธสัญญาไว้กับเจ้าเมื่อเจ้าออกมาจากอียิปต์ และจิตวิญญาณของเรายังคงอยู่ท่ามกลางพวกเจ้า อย่ากลัวเลย’

6“พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า ‘อีกสักหน่อยหนึ่ง เราจะเขย่าฟ้าสวรรค์และแผ่นดินโลก ทะเล และผืนแผ่นดินอีกครั้ง 7เราจะเขย่ามวลประชาชาติและสิ่งที่ประชาชาติทั้งหลายพึงปรารถนาจะหลั่งไหลมา และเราจะทำให้นิเวศนี้เปี่ยมด้วยสง่าราศี’ พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสดังนั้น 8พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศว่า ‘เงินและทองเป็นของเรา 9สง่าราศีของนิเวศปัจจุบันจะรุ่งโรจน์กว่าสง่าราศีของนิเวศเดิม’ พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสดังนั้น ‘และเราจะให้สันติสุขแก่สถานที่นี้’ พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศดังนั้น”

พระพรแก่ผู้ที่มีมลทิน

10ในวันที่ยี่สิบสี่เดือนที่เก้าปีที่สองแห่งรัชกาลดาริอัส พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงผู้เผยพระวจนะฮักกัยว่า 11“พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า ‘จงถามปุโรหิตดูเถิดว่าบทบัญญัติระบุไว้อย่างไร 12หากผู้หนึ่งผู้ใดห่อเนื้อบริสุทธิ์ไว้กับเสื้อคลุม แล้วห่อเนื้อนั้นไปถูกขนมปังหรือแกง เหล้าองุ่น น้ำมันหรืออาหารอื่นๆ สิ่งนั้นจะพลอยบริสุทธิ์ไปด้วยหรือไม่?’ ”

บรรดาปุโรหิตตอบว่า “ไม่”

13แล้วฮักกัยกล่าวว่า “หากผู้ใดเป็นมลทินเพราะไปแตะร่างผู้ตาย แล้วไปแตะสิ่งหนึ่งสิ่งใด สิ่งนั้นจะเป็นมลทินหรือไม่?”

บรรดาปุโรหิตตอบว่า “สิ่งนั้นจะเป็นมลทิน”

14ฮักกัยจึงกล่าวว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า ‘ประชากรและประชาชาตินี้ก็เป็นเช่นนั้นในสายตาของเรา ไม่ว่าเขาจะทำสิ่งใดหรือถวายอะไร ล้วนแต่เป็นมลทินทั้งสิ้น

15“ ‘บัดนี้จงตรึกตรองเรื่องนี้ให้ดี นับตั้งแต่วันนี้ไป2:15 หรือเท่าที่ผ่านมา จงพิจารณาว่าสิ่งต่างๆ เป็นอย่างไรก่อนหน้าที่จะวางศิลาฐานรากของพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 16เมื่อผู้หนึ่งผู้ใดมายังกองข้าวโดยหวังว่าจะได้ข้าวยี่สิบถัง กลับมีเพียงสิบถัง เมื่อผู้ใดมายังบ่อเก็บเหล้าองุ่นโดยหวังว่าจะตักได้ห้าสิบถัง ก็มีเพียงยี่สิบถัง 17เราทำลายสิ่งทั้งปวงที่เจ้าลงแรงทำขึ้นโดยตัวทำลาย เชื้อรา และลูกเห็บ ถึงกระนั้นเจ้าก็ไม่ยอมกลับมาหาเรา’ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น 18‘นับแต่วันนี้เป็นต้นไป ตั้งแต่วันที่ยี่สิบสี่เดือนที่เก้านี้ จงตรึกตรองถึงวันที่วางฐานรากของพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า จงใคร่ครวญว่า 19มีเมล็ดพืชใดๆ เหลืออยู่ในยุ้งฉางบ้าง? จวบจนบัดนี้เถาองุ่น มะเดื่อ ทับทิม และต้นมะกอกไม่ได้ผลิผลเลย

“ ‘นับตั้งแต่วันนี้ไปเราจะอวยพรเจ้า’ ”

เศรุบบาเบลเป็นแหวนตราขององค์พระผู้เป็นเจ้า

20พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงฮักกัยเป็นครั้งที่สองในวันที่ยี่สิบสี่ของเดือนนั้นว่า 21“จงบอกเศรุบบาเบลผู้ว่าการของยูดาห์ว่า เราจะเขย่าฟ้าสวรรค์และแผ่นดินโลก 22เราจะคว่ำราชบัลลังก์และขยี้อำนาจของบรรดาอาณาจักรต่างชาติ เราจะคว่ำรถม้าศึกและพลขับ ม้าศึกและคนขี่ม้าของพวกเขาจะล้มลง ต่างล้มลงด้วยดาบของพี่น้องของเขา

23“พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศว่า ‘ในวันนั้นเราจะรับเจ้า เศรุบบาเบลบุตรเชอัลทิเอลผู้รับใช้ของเรา’ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น ‘และเราจะทำให้เจ้าเป็นดั่งแหวนตราของเราเพราะเราได้เลือกสรรเจ้า’ พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศดังนั้น”