ሐዋርያት ሥራ 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 8:1-40

1ሳውልም በእስጢፋኖስ መገደል ተስማምቶ ነበር።

የአማኞች መሰደድና መበተን

በዚያ ቀን በኢየሩሳሌም በነበረችው ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ተነሣ፤ ከሐዋርያትም በስተቀር አማኞች በሙሉ በይሁዳና በሰማርያ አውራጃዎች ሁሉ ተበተኑ፤ 2በመንፈሳዊ ነገር የተጉ ሰዎችም እስጢፋኖስን ቀበሩት፤ ደግሞም እጅግ አለቀሱለት። 3ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ታጥቆ ተነሣ፤ ከቤት ወደ ቤት በመግባትም ወንዶችንና ሴቶችን ጐትቶ እያወጣ ወህኒ ቤት ያስገባቸው ነበር።

ፊልጶስ በሰማርያ

4የተበተኑትም በሄዱበት ሁሉ ቃሉን ሰበኩ፤ 5ፊልጶስም ወደ አንዲት የሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን8፥5 ወይም መሲሕ ሰበከላቸው። 6ብዙ ሕዝብም ፊልጶስ የተናገረውን ሲሰሙና ያደረገውንም ታምራዊ ምልክቶች ሲያዩ፣ አንድ ልብ ሆነው ያዳምጡት ነበር። 7ርኩሳን8፥7 ወይም ክፉ መናፍስትም እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ወጡ፤ ብዙ ሽባዎችና ዐንካሶችም ተፈወሱ፤ 8ከዚህ የተነሣም በከተማዪቱ ታላቅ ደስታ ሆነ።

ጠንቋዩ ሲሞን

9ነገር ግን ከዚህ ቀደም ሲል በከተማዪቱ ውስጥ እየጠነቈለ የሰማርያን ሰዎች ሁሉ ያስገረመ፣ ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም ራሱን እንደ ታላቅ ሰው ይቈጥር ነበር። 10ከታናሽ እስከ ታላቅ ያለው ሰው ሁሉ፣ “ይህ ሰው ‘ታላቁ ኀይል’ በመባል የሚታወቀው መለኮታዊ ኀይል ነው” በማለት ከልብ ያዳምጡት ነበር፤ 11ከብዙ ጊዜ ጀምሮ በጥንቈላ ሥራው ስላስገረማቸውም ትኵረት ሰጥተው ይከተሉት ነበር። 12ነገር ግን ፊልጶስ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም የሰበከላቸውን አምነው በመቀበላቸው ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ፤ 13ራሱ ሲሞን እንኳ ሳይቀር አምኖ ተጠመቀ፤ ፊልጶስንም ተከትሎ ሄደ፤ የሚደረገውን ምልክትና ታላቅ ታምራት አይቶም ተገረመ።

14በኢየሩሳሌም የነበሩት ሐዋርያት የሰማርያ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል መቀበላቸውን በሰሙ ጊዜ፣ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ወደ እነርሱ ላኳቸው። 15እነርሱም ሰማርያ በደረሱ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበሉ ለሰማርያ ሰዎች ጸለዩላቸው፤ 16ምክንያቱም በዚያን ጊዜ በጌታ ኢየሱስ ስም ተጠምቀው ነበር እንጂ ገና መንፈስ ቅዱስ በአንዳቸውም ላይ አልወረደም ነበር። 17ስለዚህ ጴጥሮስና ዮሐንስ እጃቸውን ጫኑባቸው፤ እነርሱም መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።

18ሲሞንም ሐዋርያት እጃቸውን በሚጭኑበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሰጥ አይቶ፣ ገንዘብ አመጣላቸውና እንዲህ አላቸው፤ 19“እጄን የምጭንበት ሰው ሁሉ መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበል ይህን ሥልጣን ለእኔም ስጡኝ።”

20ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ ለመግዛት አስበሃልና፣ አንተም ገንዘብህም አብራችሁ ጥፉ! 21ልብህ በእግዚአብሔር ፊት ቅን ስላልሆነ፣ አንተ በዚህ አገልግሎት ድርሻ ወይም ዕድል ፈንታ የለህም። 22አሁንም ስለዚህ ክፋትህ ንስሓ ግባ፤ ወደ ጌታም ጸልይ፤ ምናልባት ይህን የልብህን ሐሳብ ይቅር ይልህ ይሆናል፤ 23ምክንያቱም በመራራነት ተሞልተህ፣ በዐመፅ ሰንሰለት ተይዘህ አይሃለሁና።”

24ሲሞንም መልሶ፣ “ከተናገራችሁት ምንም ነገር እንዳይደርስብኝ ጌታን ለምኑልኝ” አላቸው።

25ጴጥሮስና ዮሐንስም የጌታን ቃል ከመሰከሩና ገልጠው ከተናገሩ በኋላ፣ በብዙ የሰማርያ መንደሮች ወንጌልን እየሰበኩ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።

ፊልጶስና ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ

26የጌታም መልአክ ፊልጶስን፣ “ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚያወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ” አለው፤ 27እርሱም ተነሥቶ ሄደ። እነሆ፤ የኢትዮጵያ ንግሥት የህንደኬ ባለሟልና የሀብት ንብረቷ ሁሉ አዛዥ የሆነ አንድ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ አገኘ። ይህም ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር። 28ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብብ ነበር። 29መንፈስም ፊልጶስን፣ “ሂድ፤ ወደዚህ ሠረገላ ቅረብ” አለው።

30ፊልጶስም ፈጥኖ ወደ ሠረገላው ሄደ፤ ጃንደረባውም የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብብ ሰምቶ፣ “ለመሆኑ፣ የምታነብበውን ታስተውለዋለህን?” አለው።

31ጃንደረባውም፣ “የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውላለሁ” አለው፤ እርሱም ወደ ሠረገላው ወጥቶ አብሮት እንዲቀመጥ ፊልጶስን ለመነው።

32ጃንደረባው ያነብብ የነበረው የመጽሐፍ ክፍል ይህ ነበር፤

“እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፤

የበግ ጠቦት በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል፣

እንዲሁ አፉን አልከፈተም።

33ራሱን በማዋረዱም ፍትሕን ተነፈገ፤

ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና፣

ስለ ትውልዱ ማን ሊናገር ይችላል?”

34ጃንደረባውም መልሶ ፊልጶስን፣ “ነቢዩ ይህን የሚናገረው ስለ ማን ነው? ስለ ራሱ ነው ወይስ ስለ ሌላ ሰው? እባክህ ንገረኝ” አለው። 35ፊልጶስም አፉን ከፈተ፤ ከዚሁም መጽሐፍ ክፍል ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌል ሰበከለት።

36በመጓዝ ላይ ሳሉም ውሃ ካለበት ስፍራ ደረሱ፤ ጃንደረባውም፣ “እነሆ፤ ውሃ እዚህ አለ፤ ታዲያ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምን ነገር አለ?” አለው።

37ፊልጶስም፣ “በፍጹም ልብህ ካመንህ መጠመቅ ትችላለህ” አለው።

ጃንደረባውም፣ “ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ” ሲል መለሰለት፤8፥37 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ይህ ጥቅስ የላቸውም። 38ሠረገላውም እንዲቆም አዘዘ። ከዚያም ሁለቱ አብረው ወደ ውሃው ወረዱ፤ ፊልጶስም ጃንደረባውን አጠመቀው። 39ከውሃውም በወጡ ጊዜ፣ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጥቆ ወሰደው፤ ጃንደረባውም ከዚህ በኋላ አላየውም፤ ሆኖም ደስ እያለው ጕዞውን ቀጠለ። 40ከዚያ በኋላ ግን ፊልጶስ በአዛጦን ታየ፤ ቂሳርያም እስኪደርስ ድረስ በሚያልፍባቸው ከተሞች ሁሉ ወንጌልን ይሰብክ ነበር።

Thai New Contemporary Bible

กิจการของอัครทูต 8:1-40

1และเซาโลอยู่ที่นั่นก็เห็นชอบกับการตายของสเทเฟน

คริสตจักรถูกข่มเหงและกระจัดกระจายไป

ครั้งนั้นเกิดการข่มเหงคริสตจักรครั้งใหญ่ที่กรุงเยรูซาเล็ม สาวกทั้งปวงยกเว้นพวกอัครทูตได้กระจัดกระจายไปทั่วแคว้นยูเดียและสะมาเรีย 2บรรดาผู้อยู่ในทางพระเจ้าจัดการฝังศพสเทเฟนและอาลัยถึงเขาอย่างยิ่ง 3ฝ่ายเซาโลเริ่มทำลายล้างคริสตจักร เขาเข้าไปบ้านนั้นบ้านนี้ฉุดลากชายหญิงไปขังไว้ในคุก

ฟีลิปในสะมาเรีย

4บรรดาผู้กระจัดกระจายไปนั้นก็เที่ยวประกาศพระวจนะในทุกแห่งหนที่พวกเขาไป 5ส่วนฟีลิปลงไปยังเมืองหนึ่งในแคว้นสะมาเรียและประกาศเรื่องพระคริสต์8:5 หรือพระเมสสิยาห์ที่นั่น 6เมื่อฝูงชนได้ฟังฟีลิปและได้เห็นหมายสำคัญที่เขาทำก็ล้วนตั้งใจฟังสิ่งที่เขากล่าว 7วิญญาณชั่ว8:7 ภาษากรีกว่าโสโครกกรีดร้องแล้วออกมาจากหลายคน และคนเป็นอัมพาตและคนพิการหลายคนก็หาย 8ดังนั้นจึงมีความชื่นชมยินดีใหญ่หลวงในเมืองนั้น

ซีโมนนักอาคม

9ในเมืองนั้นมีชายคนหนึ่งชื่อซีโมน เขาได้เล่นคาถาอาคมมาระยะหนึ่งแล้วและได้ทำให้ชาวสะมาเรียทั้งปวงอัศจรรย์ใจ เขายกตัวว่าเป็นผู้ยิ่งใหญ่ 10และประชาชนทุกคนทั้งผู้ใหญ่ผู้น้อยต่างสนใจฟังเขาและพากันยกย่องว่า “ชายผู้นี้คือฤทธิ์อำนาจของพระเจ้าที่รู้จักกันในนามว่าองค์ผู้ทรงมหิทธิฤทธิ์” 11คนเหล่านี้ติดตามเขาเพราะอัศจรรย์ใจในวิทยาคมของเขามานาน 12แต่เมื่อฟีลิปประกาศข่าวประเสริฐเรื่องอาณาจักรของพระเจ้าและพระนามของพระเยซูคริสต์ พวกเขาก็เชื่อฟีลิปและรับบัพติศมาทั้งชายและหญิง 13ซีโมนเองก็เชื่อและรับบัพติศมา เขาติดตามฟีลิปไปทุกแห่งและรู้สึกประหลาดใจในหมายสำคัญและการอัศจรรย์อันยิ่งใหญ่ต่างๆ ที่ได้เห็น

14เมื่ออัครทูตในกรุงเยรูซาเล็มได้ข่าวว่าชาวสะมาเรียรับพระวจนะของพระเจ้าแล้วก็ส่งเปโตรกับยอห์นมาหาพวกเขา 15เมื่อทั้งสองมาถึงก็อธิษฐานเผื่อพวกเขาให้ได้รับพระวิญญาณบริสุทธิ์ 16เพราะยังไม่มีใครในพวกเขาได้รับพระวิญญาณบริสุทธิ์ เพียงแต่ได้รับบัพติศมาเข้าใน8:16 หรือบัพติศมาใน พระนามขององค์พระเยซูเจ้า 17จากนั้นเปโตรกับยอห์นวางมือบนพวกเขาและพวกเขาก็ได้รับพระวิญญาณบริสุทธิ์

18เมื่อซีโมนเห็นคนได้รับพระวิญญาณบริสุทธิ์โดยอัครทูตวางมือให้จึงนำเงินมาเสนอให้พวกเขา 19และกล่าวว่า “ขอมอบความสามารถนี้ให้แก่ข้าพเจ้าด้วยเพื่อว่าทุกคนที่ข้าพเจ้าวางมือให้จะได้รับพระวิญญาณบริสุทธิ์”

20เปโตรตอบว่า “ให้เงินของท่านพินาศไปพร้อมกับตัวท่านเพราะท่านคิดจะใช้เงินซื้อของประทานจากพระเจ้า! 21ท่านไม่มีส่วนร่วมในพันธกิจนี้เพราะใจของท่านไม่ได้ซื่อตรงต่อพระเจ้า 22จงกลับใจใหม่จากการชั่วร้ายนี้และอธิษฐานต่อองค์พระผู้เป็นเจ้า พระองค์อาจจะอภัยให้ท่านที่คิดเช่นนี้อยู่ในใจ 23เพราะเราเห็นว่าท่านเต็มไปด้วยความขมขื่นและตกเป็นเชลยของบาป”

24แล้วซีโมนจึงตอบว่า “โปรดอธิษฐานต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าเผื่อข้าพเจ้าด้วยเพื่อสิ่งที่ท่านกล่าวจะไม่เกิดขึ้นกับข้าพเจ้า”

25หลังจากเปโตรกับยอห์นเป็นพยานและประกาศพระวจนะขององค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วทั้งสองก็กลับไปยังกรุงเยรูซาเล็ม ระหว่างนั้นก็ได้ประกาศข่าวประเสริฐในหมู่บ้านของชาวสะมาเรียหลายแห่ง

ฟีลิปกับขันทีชาวเอธิโอเปีย

26ทูตองค์หนึ่งขององค์พระผู้เป็นเจ้าสั่งฟีลิปว่า “จงลงใต้ ไปยังถนนที่เรียกว่าทางกันดารซึ่งเชื่อมระหว่างกรุงเยรูซาเล็มกับเมืองกาซา” 27ดังนั้นฟีลิปก็ออกเดินทางไป ในระหว่างทางเขาพบขันทีชาวเอธิโอเปีย8:27 คือจากตอนบนของลุ่มแม่น้ำไนล์ เป็นขุนนางคนสำคัญดูแลคลังทรัพย์ของพระนางคานดาสีราชินีแห่งเอธิโอเปีย ขันทีผู้นี้ได้มานมัสการที่เยรูซาเล็ม 28ระหว่างเดินทางกลับบ้านเขานั่งอ่านหนังสือผู้เผยพระวจนะอิสยาห์อยู่ในรถม้า 29พระวิญญาณตรัสบอกฟีลิปว่า “จงเข้าไปใกล้ๆ รถม้านั้นเถิด”

30แล้วฟีลิปจึงวิ่งเข้าไปใกล้รถนั้น เขาได้ยินเสียงคนอ่านหนังสือผู้เผยพระวจนะอิสยาห์ก็ถามว่า “ท่านเข้าใจสิ่งที่ท่านอ่านหรือ?”

31ขันทีนั้นตอบว่า “ถ้าไม่มีใครอธิบาย ข้าพเจ้าจะเข้าใจได้อย่างไร?” ดังนั้นเขาจึงเชิญฟีลิปขึ้นมานั่งด้วยกัน

32พระคัมภีร์ที่ขันทีกำลังอ่านอยู่นั้นคือ

“เขาถูกนำตัวไปเหมือนแกะที่ถูกนำไปฆ่า

และเหมือนลูกแกะที่เงียบอยู่ต่อหน้าผู้ตัดขน

เขาก็ไม่ได้ปริปากเช่นกัน

33เมื่อเขาถูกย่ำยีนั้นเขาไม่ได้รับความยุติธรรมเลย

ใครเล่าจะพูดถึงเชื้อสายของเขาได้?

เพราะชีวิตของเขาถูกพรากไปจากโลก”8:32,33 อสย.53:7,8

34ขันทีถามฟีลิปว่า “โปรดบอกเราเถิด ผู้เผยพระวจนะกำลังพูดถึงใคร ตัวผู้เผยพระวจนะเองหรือใครอื่น?” 35แล้วฟีลิปจึงเริ่มจากข้อพระคัมภีร์ตอนนั้นและเล่าถึงข่าวประเสริฐเรื่องพระเยซูให้เขาฟัง

36ขณะเดินทางไปตามถนน พวกเขามาพบแอ่งน้ำ ขันทีจึงเอ่ยว่า “ดูเถิด ที่นี่มีน้ำ มีอะไรขัดข้องไม่ให้ข้าพเจ้ารับบัพติศมาเล่า?”8:36 สำเนาต้นฉบับในสมัยหลังบางสำเนาว่าเล่า?” 37ฟีลิปกล่าวว่า “ถ้าท่านเชื่อด้วยสุดใจของท่าน ก็รับบัพติศมาได้” ขันทีตอบว่า “ข้าพเจ้าเชื่อว่าพระเยซูคริสต์ทรงเป็นพระบุตรของพระเจ้า” 38และเขาสั่งให้หยุดรถ จากนั้นฟีลิปกับขันทีก็ลงไปในน้ำและฟีลิปให้ขันทีรับบัพติศมา 39เมื่อขึ้นจากน้ำพระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้าทรงรับฟีลิปไปทันที ขันทีไม่เห็นเขาอีกเลยแต่เดินทางต่อไปด้วยความชื่นชมยินดี 40อย่างไรก็ดีฟีลิปได้มาปรากฏตัวที่เมืองอาโซทัสและเดินทางไปทั่วเพื่อประกาศข่าวประเสริฐในทุกเมืองจนมาถึงเมืองซีซารียา