ሐዋርያት ሥራ 7 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 7:1-60

እስጢፋኖስ በሸንጎው ፊት ያደረገው ንግግር

1ሊቀ ካህናቱም፣ “ይህ የቀረበብህ ክስ እውነት ነውን?” አለው።

2እስጢፋኖስም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ወንድሞችና አባቶች ሆይ፤ አድምጡኝ! አባታችን አብርሃም ወደ ካራን ከመምጣቱ በፊት፣ ገና በመስጴጦምያ ሳለ፣ የክብር አምላክ ተገልጦለት፣ 3‘ከአገርህና ከወገንህ ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ’ አለው።

4“እርሱም ከከለዳውያን ምድር ወጥቶ በካራን ተቀመጠ። ከአባቱም ሞት በኋላ፣ አሁን እናንተ ወደምትኖሩበት ወደዚህ አገር አመጣው። 5በዚህም ስፍራ አንዲት ጫማ ታህል እንኳ ርስት አልሰጠውም፤ ነገር ግን በዚያን ጊዜ ምንም ልጅ ሳይኖረው፣ እርሱና ከእርሱም በኋላ ዘሩ ምድሪቱን እንደሚወርሱ እግዚአብሔር ቃል ገባለት። 6ደግሞም እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ተናገረው፤ ‘ዘርህ በባዕድ አገር መጻተኛ ይሆናል፤ አራት መቶ ዓመትም በባርነት ቀንበር ሥር ይማቅቃል። 7ሆኖም በባርነት የሚገዛቸውን ሕዝብ እኔ ደግሞ እቀጣዋለሁ። ከዚያም አገር ወጥተው በዚህች ስፍራ ያመልኩኛል።’ 8ከዚያም የግዝረትን ኪዳን ሰጠው፤ አብርሃምም ይስሐቅን ወለደ፤ በስምንተኛውም ቀን ገረዘው። ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ዐሥራ ሁለቱን የነገድ አባቶች ወለደ።

9“የነገድ አባቶችም በዮሴፍ ቀንተው በባርነት ወደ ግብፅ ሸጡት፤ እግዚአብሔር ግን ከእርሱ ጋር ስለ ነበር፣ 10ከመከራው ሁሉ አወጣው፤ በግብፅም ንጉሥ በፈርዖን ፊት ሞገስና ጥበብን አጐናጸፈው፤ ፈርዖንም በግብፅና በቤተ መንግሥቱ ሁሉ ላይ ኀላፊ አድርጎ ሾመው።

11“በዚያ ጊዜም በግብፅና በከነዓን አገር ሁሉ ታላቅ መከራን ያስከተለ ራብ መጣ፤ አባቶቻችንም የሚበሉትን ዐጡ። 12ያዕቆብም እህል በግብፅ መኖሩን በሰማ ጊዜ፣ አባቶቻችንን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ግብፅ ላካቸው፤ 13ለሁለተኛ ጊዜ ሲሄዱ ደግሞ ዮሴፍ ማንነቱን ለወንድሞቹ ገለጠ፤ ፈርዖንም ስለ ዮሴፍ ዘመዶች ተረዳ። 14ከዚህ በኋላ፣ ዮሴፍ ልኮ አባቱን ያዕቆብንና ሰባ አምስት ነፍስ የሚሆኑ ቤተ ዘመዶቹን በሙሉ አስመጣ። 15ያዕቆብ ወደ ግብፅ ወረደ፤ እርሱም አባቶቻችንም በዚያ ሞቱ። 16አስከሬናቸውም ወደ ሴኬም ተወስዶ፣ አብርሃም ከዔሞር ልጆች ላይ በጥሬ ብር በገዛው መቃብር ተቀበረ።

17“እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባው ቃል የሚፈጸምበት ጊዜ ሲቃረብም፣ በግብፅ የነበረው የሕዝባችን ቍጥር እየበዛ ሄደ። 18ከዚያ በኋላ ዮሴፍን የማያውቅ ሌላ ንጉሥ በግብፅ ነገሠ። 19እርሱም ሕዝባችንን በተንኰሉ አስጨነቀ፤ ገና የተወለዱ ሕፃናታቸውም ይሞቱ ዘንድ ወደ ውጭ አውጥተው እንዲጥሏቸው አስገደዳቸው።

20“በዚህ ጊዜ ሙሴ ተወለደ፤ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን ያገኘ ውብ ሕፃን7፥20 ወይም ተራ ልጅ አልነበረም ነበር። በአባቱም ቤት ሦስት ወር በእንክብካቤ አደገ። 21ወደ ውጭ በተጣለም ጊዜ የፈርዖን ልጅ አግኝታ ወሰደችው፤ እንደ ራሷ ልጅ አድርጋም አሳደገችው። 22ሙሴም የግብፆችን ጥበብ ሁሉ ተማረ፤ በንግግሩና በተግባሩም ብርቱ ሆነ።

23“ሙሴ አርባ ዓመት በሆነው ጊዜ፣ ወንድሞቹን የእስራኤልን ልጆች ሊጐበኝ በልቡ ዐሰበ። 24እርሱም፣ አንድ ግብፃዊ ከወገኖቹ አንዱን በደል ሲያደርስበት አይቶ ግብፃዊውንም ገደለ፤ ለተገፋው ወገኑም ተበቀለ። 25ወገኖቹም እግዚአብሔር በእርሱ እጅ ነጻ እንደሚያወጣቸው የሚያስተውሉ መስሎት ነበር፤ እነርሱ ግን አላስተዋሉም። 26በማግስቱም ደግሞ ሁለት እስራኤላውያን ሲጣሉ ደረሰ፤ ሊያስታርቃቸውም ፈልጎ፣ ‘ሰዎች፤ እናንተ እኮ ወንድማማቾች ናችሁ፤ እንዴት እርስ በርሳችሁ ትጐዳዳላችሁ?’ አላቸው።

27“በባልንጀራው ላይ በደል ሲያደርስ የነበረው ሰው ግን፣ ሙሴን ገፈተረውና እንዲህ አለ፤ ‘አንተን ገዥና ፈራጅ አድርጎ በእኛ ላይ የሾመህ ማን ነው? 28ወይስ ትናንት ግብፃዊውን እንደ ገደልኸው እኔንም ልትገድለኝ ትፈልጋልህን?’ 29ሙሴም ይህን እንደ ሰማ ሸሽቶ በምድያም አገር መጻተኛ ሆኖ ተቀመጠ፤ በዚያም ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደ።

30“ከአርባ ዓመት በኋላ፣ በሲና ተራራ አካባቢ ባለው ምድረ በዳ፣ በሚነድድ ቍጥቋጦ ነበልባል ውስጥ መልአክ ተገለጠለት። 31ሙሴም ባየው ነገር ተደነቀ፤ ነገሩን ለማጣራት ወደዚያ ሲቀርብ የጌታ ድምፅ፤ 32‘እኔ የአባቶችህ አምላክ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ’ ሲል ሰማ። ሙሴም በፍርሀት ተዋጠ፤ ለመመልከትም አልደፈረም።

33“ጌታም እንዲህ አለው፤ ‘የእግርህን ጫማ አውልቅ፤ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች ምድር ናትና። 34በግብፅ ያለውን የሕዝቤን መከራ በርግጥ አይቻለሁ፤ የጭንቅ ጩኸታቸውን ሰምቻለሁ፤ ላድናቸውም ወርጃለሁ። አሁንም ና፤ ወደ ግብፅ መልሼ እልክሃለሁ።’

35“እንግዲህ እነዚያ፣ ‘ገዥና ፈራጅ አድርጎ የሾመህ ማን ነው?’ ብለው የናቁትን ይህን ሙሴ እግዚአብሔር በቍጥቋጦው ውስጥ በታየው መልአክ አማካይነት ገዥና ታዳጊ አድርጎ ወደ እነርሱ ላከው። 36እርሱም መርቶ ከግብፅ አወጣቸው፤ በግብፅ፣ በቀይ ባሕርና በምድረ በዳ አርባ ዓመት ድንቅ ነገሮችንና ታምራዊ ምልክቶችን አደረገ።

37“የእስራኤልንም ሕዝብ፣ ‘እግዚአብሔር እንደ እኔ ያለ ነቢይ ከመካከላችሁ ያስነሣላችኋል’ ያላቸው ይኸው ሙሴ ነበር። 38እርሱም በሲና ተራራ ከተናገረው መልአክና ከአባቶቻችን ጋር በምድረ በዳ በሕዝቡ ጉባኤ መካከል ነበር፤ የሕይወትንም ቃል ወደ እኛ ለማስተላለፍ ተቀበለ።

39“አባቶቻችን ግን ተቃወሙት እንጂ ሊታዘዙት ስላልፈለጉ በልባቸው ወደ ግብፅ ተመለሱ። 40አሮንንም፣ ‘ፊት ፊታችን የሚሄዱ አማልክት አብጅልን፤ ከግብፅ ምድር መርቶ ያወጣን ያ ሙሴ ምን እንደ ደረሰበት አናውቅምና’ አሉት። 41በዚያን ጊዜ የጥጃ ምስል ሠርተው፣ ለጣዖቱ መሥዋዕት አቀረቡ፤ በእጃቸውም ሥራ ተደሰቱ፤ ፈነጠዙም። 42እግዚአብሔር ግን ከእነርሱ ዘወር አለ፤ ያመልኳቸውም ዘንድ ለሰማይ ከዋክብት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ይህም በነቢያት መጽሐፍ እንዲህ ተብሎ በተጻፈው መሠረት ተፈጸመ፤

“ ‘እናንት የእስራኤል ቤት ሆይ፤ አርባ ዓመት በምድረ በዳ በነበራችሁ ጊዜ፣

መሥዋዕትንና መባን ለእኔ አቀረባችሁልኝን?

43ይልቁንም ልታመልኳቸው የሠራችኋቸውን፣

የሞሎክን ድንኳንና የጣዖታችሁን፣

የሬምፉምን ኮከብ ከፍ ከፍ አድርጋችሁ ያዛችሁ።

ስለዚህ እኔም እንድትጋዙ አደርጋለሁ፤ ከባቢሎንም ወዲያ እሰድዳችኋለሁ።’

44“እግዚአብሔር ለሙሴ ባሳየው ንድፍና ባዘዘው መሠረት የተሠራችው የምስክር ድንኳን፣ ከአባቶቻችን ጋር በምድረ በዳ ነበረች። 45አባቶቻችንም ድንኳኗን ከተቀበሉ በኋላ፣ እግዚአብሔር በኢያሱ መሪነት ያሳደዳቸውን የአሕዛብን አገር በወረሱ ጊዜ ይዘዋት ገቡ፤ እስከ ዳዊትም ዘመን ድረስ በምድሪቱ ተቀመጠች፤ 46ዳዊትም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ በማግኘቱ ለያዕቆብ7፥46 አንዳንድ የጥንት ቅጆች የያዕቆብ ቤት ይላሉ። አምላክ ማደሪያ ያዘጋጅ ዘንድ ለመነ፤ 47ነገር ግን የማደሪያውን ቤት የሠራለት ሰሎሞን ነበር።

48“ይሁን እንጂ፣ ልዑል የሰው እጅ በሠራው ቤት ውስጥ አይኖርም፤ ይህም ነቢዩ እንዲህ ባለው መሠረት ነው፤

49“ ‘ሰማይ ዙፋኔ ነው፤

ምድርም የእግሬ ማሳረፊያ ናት፤

ታዲያ ምን ዐይነት ቤት ትሠሩልኛላችሁ?

ይላል ጌታ፤

ወይንስ ማረፊያ የሚሆነኝ የትኛው ቦታ ነው?

50ይህን ሁሉ የሠራው እጄ አይደለምን?’

51“እናንት ልባችሁና ጆሯችሁ ያልተገረዘ፣ ዐንገተ ደንዳኖች ልክ እንደ አባቶቻችሁ መንፈስ ቅዱስን ሁልጊዜ ትቃወማላችሁ። 52ከነቢያት መካከል አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን አለ? የጻድቁን መምጣት አስቀድመው የተናገሩትን እንኳ ገድለዋል፤ እናንተም አሁን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት፤ ገደላችሁትም፤ 53በመላእክት አማካይነት የተሰጣችሁንም ሕግ ተቀበላችሁ እንጂ አልጠበቃችሁትም።”

የእስጢፋኖስ መወገር

54በሸንጎው ስብሰባ ላይ የነበሩትም ይህን በሰሙ ጊዜ እጅግ ተቈጡ፤ ጥርሳቸውንም አፏጩበት። 55እስጢፋኖስ ግን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት፣ የእግዚአብሔርን ክብር እንዲሁም ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፣ 56“እነሆ፤ ሰማያት ተከፍተው፣ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ” አለ።

57በዚህ ጊዜ በታላቅ ድምፅ እየጮኹ ጆሯቸውን ደፍነው እርሱ ወደ አለበት በአንድነት ሮጡ፤ 58ይዘውም ከከተማው ውጭ ጣሉት፤ በድንጋይም ይወግሩት ጀመር። ይህ በሚሆንበት ጊዜ በዚያ የነበሩ ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በተባለ ጕልማሳ እግር አጠገብ አስቀመጡ።

59እስጢፋኖስም እየወገሩት ሳለ፣ “ጌታ ኢየሱስ ሆይ፤ ነፍሴን ተቀበላት፤” ብሎ ጸለየ፤ 60ከዚያም ተንበርክኮ በታላቅ ድምፅ፣ “ጌታ ሆይ፤ ይህን ኀጢአት አትቍጠርባቸው!” ብሎ ጮኸ፤ ይህን ካለ በኋላም አንቀላፋ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

מעשי השליחים 7:1-60

1”האם נכונות ההאשמות האלה?“ שאל הכהן הגדול את סטפנוס.

2”הקשיבו אלי, אנשים, אחים וזקנים נכבדים!“ השיב סטפנוס. ”אלוהי הכבוד נגלה אל אברהם אבינו בארם נהריים, לפני שיצא לחרן, 3ואמר לו לעזוב את ארץ מולדתו, להיפרד מבני משפחתו וללכת אל הארץ שה׳ ינחה אותו אליה. 4אברהם עזב את אור כשדים וגר בחרן עד מות אביו. לאחר מכן הביא אותו ה׳ לכאן, לארץ הזאת אשר אתם גרים בה עכשיו. 5אלוהים לא נתן לאברהם רכוש משלו – אפילו לא חלקת־אדמה קטנה; הוא רק הבטיח לו שבמרוצת הזמן תשתייך כל הארץ לאברהם ולצאצאיו, אך כי באותה עת לא היה לו עדיין ילד. 6כמו־כן אמר לו אלוהים שצאצאיו אלה יעזבו את ארצם ויגורו בארץ זרה, ושם יהיו עבדים במשך ארבע מאות שנה. 7אולם אלוהים הבטיח לאברהם שיעניש את הארץ אשר תשעבד אותם, ושלאחר מכן יצאו ויעבדו אותו כאן.

8”באותה עת נתן ה׳ לאברהם את מצוות המילה, כהוכחה לברית שכרת עם אברהם, וכאשר נולד בנו יצחק מל אותו אברהם ביום השמיני לחייו. כעבור זמן יצחק מל את יעקב, ויעקב את שנים־עשר האבות.

9”אותם אנשים שהיו לאבות האומה הישראלית קנאו ביוסף אחיהם, ומכרו אותו כעבד לישמעאלים שהיו בדרכם למצרים. אולם אלוהים היה עם יוסף 10והציל אותו מכל צרותיו. אלוהים העניק ליוסף חן רב וחכמה בלתי־רגילה, אשר מצאו־חן בעיני פרעה מלך מצרים, ומשום כך מינה אותו פרעה למושל על כל ארץ מצרים ולאחראי על כל ענייני הארמון.

11”כעבור זמן־מה שרר רעב כבד אשר גרם סבל רב במצרים ובכנען, ולאבותינו לא היה מה לאכול. 12כאשר שמע יעקב שיש עדיין אוכל במצרים, שלח לשם את בניו בפעם הראשונה כדי לקנות מה שיוכלו להשיג. 13בביקורם השני במצרים גילה להם יוסף את זהותו ואף הציג אותם לפני פרעה. 14יוסף שלח להביא מארץ כנען את יעקב אביו ואת כל בני־משפחתו, כולם יחד מנו שבעים וחמש איש, והזמין אותם לגור איתו במצרים. 15וכך ירד יעקב למצרים. לאחר שמתו יעקב ובניו, 16נלקחו גופותיהם לשכם ונקברו בקבר שקנה אברהם מיד בני־חמור.

17”כשקרב המועד שקבע אלוהים לשחרור בני־ישראל מעבדותם, כפי שהבטיח לאברהם אבינו, התרבה עם ישראל במצרים במהירות גדולה. 18ואז עלה לשלטון מלך אשר לא כיבד את זכרו של יוסף. 19מלך זה נהג בעמנו ברשעות ובאכזריות, וציווה על אבותינו להפקיר את ילדיהם למוות. 20באותה תקופה נולד משה, שהיה טוב בעיני אלוהים, והוריו הסתירוהו בביתם במשך שלושה חודשים. 21כשלא יכלו הוריו להסתיר אותו יותר נאלצו להוציאו מן הבית, מצאה אותו בת פרעה ואימצה אותו לה לבן. 22משה לומד בכל חכמת מצרים, גדל והיה לנואם מחונן ולאיש־מעשים דגול.

23”יום אחד עלה בדעתו של משה לבקר את אחיו בני־ישראל, והוא בן ארבעים. 24בעת ביקורו ראה איש מצרי מתאכזר אל ישראלי. משה ניגש אל המצרי והרג אותו. 25הוא קיווה שאחיו יבינו שאלוהים שלח אותו לעזור להם, אך הם לא הבינו זאת.

26”למחרת שוב ביקר משה את בני־עמו, והפעם ראה שני ישראלים רבים ביניהם. הוא ניסה להפריד ביניהם ואמר: ’הרי אחים אתם; מדוע אתם מתקוטטים?‘

27”אולם האיש שהחל בקטטה דרש ממשה להסתלק ולא להתערב. ’מי מינה אותך למושל ושופט עלינו?‘ שאל. 28’האם אתה עומד להרוג אותי כשם שהרגת אתמול את המצרי?‘ “

29לשמע דברים אלה ברח משה למדיין, ושם נולדו שני בניו.

30”כעבור ארבעים שנה נגלה אליו מלאך ה׳ במדבר הר־סיני מתוך הסנה הבוער. 31המראה הבלתי־רגיל הפליא את משה; הוא רץ אל הסנה כדי להביט בו מקרוב, ואז שמע את קול ה׳: 32’אנוכי אלוהי אבותיך – אלוהי אברהם, יצחק ויעקב!‘ משה רעד מפחד ולא העז להרים את עיניו.

33”לפני כן אמר אלוהים למשה: ’של נעליך מעל רגליך, כי המקום אשר אתה עומד עליו אדמת־קודש הוא‘. 34ואלוהים המשיך: ’ראה ראיתי את עוני עמי אשר במצרים, ואת צעקתם שמעתי… וארד להצילו… ועתה לכה ואשלחך אל פרעה והוצא את עמי בני־ישראל ממצרים‘.7‏.34 ז 34 שמות ג 5‏-10

35”המדובר באותו משה אשר בני־ישראל דחוהו זמן־מה קודם לכן כאשר מחו: ’מי מינה אותך למושל ושופט עלינו?‘ אותו משה נשלח אליהם עתה להיות להם למנהיג ולמושיע! 36בעזרת ניסים גדולים וכבירים הוציא משה את עמו מארץ מצרים, העבירם דרך ים סוף, ולאחר מכן נדד איתם במדבר ארבעים שנה. 37זהו אותו משה אשר אמר לבני־ישראל:7‏.37 ז 37 דברים יח 15 ’נביא מקרבכם – מאחיכם – כמוני, יקים לכם אלוהים, אליו תשמעון‘. 38כשהתקהלו בני־ישראל במדבר, משה היה האיש שתיווך בינם לבין המלאך שנתן להם את תורת ה׳ – את דבר האלוהים החי – בהר סיני.

39”אולם אבותינו דחו את משה ורצו לשוב למצרים. 40’עשה לנו אלוהים אשר ילכו לפננו‘, ביקשו מאהרון, ’כי איננו יודעים מה קרה למשה אשר הוציא אותנו מארץ מצרים‘. 41וכך עשו להם בני ישראל עגל־זהב, הקריבו לו קורבנות, ושמחו באליל שיצרו במו ידיהם.

42”משום כך פנה להם ה׳ עורף והניח להם לסגוד לשמש, לירח ולכוכבים כמו לאלים! בספר עמוס שואל ה׳ את עם ישראל: ’הזבחים ומנחה הגשתם לי במדבר ארבעים שנה, בית ישראל? 43לא! התעניינותכם האמיתית הייתה באלילים שלכם: בסוכתו של מולך, בכוכבו של ריפן, ובכל הצלמים שעשיתם לכם. משום כך אגרש אתכם מכאן לארץ רחוקה – עד מעבר לבבל אגלה אתכם!‘.7‏.43 ז 43 ראה עמוס ה 25‏-27

44”במשך נדודיהם במדבר נשאו אותם אבותינו את משכן העדות, ובתוכו שמרו את לוחות־הברית. משכן זה נבנה בדיוק לפי הדגם שהראה אלוהים למשה. 45שנים רבות לאחר מכן, כשפקד יהושע על הקרבות נגד הגויים שישבו בכנען, הביאו האבות את המשכן הזה אל ארצם החדשה, ושם הוא נשאר עד ימי דוד המלך.

46”דוד, שמצא־חן בעיני אלוהים, ביקש את הזכות לבנות מקדש קבע לאלוהי יעקב. 47אולם רק בנו של דוד, שלמה, זכה לבנות את המקדש הזה. 48‏-49ובכל זאת, אלוהים אינו שוכן במקדש מעשה ידי־אדם. ’השמים כסאי‘, אמר ה׳ בפי ישעיהו הנביא, ’והארץ – הדום רגלי. אי־זה בית אשר תבנו לי? ואי־זה מקום מנוחתי? 50(הלא) את כל אלה ידי עשתה!‘.7‏.50 ז 50 ישעיהו סו 1‏-2 51הו עם קשה עורף ועובד אלילים! עד מתי תמשיכו להתנגד לרוח הקודש? אתם נוהגים בדיוק כמו אבותיכם – גם הם התנגדו לרוח הקודש. 52האם יכולים אתם לנקוב בשמו של נביא אחד שאבותיכם לא רדפו אותו? הם אפילו הרגו את אלה שניבאו את בואו של המשיח הצדיק – זה שבגדתם בו ורצחתם אותו! 53אכן, בכוונה תחילה הפרתם את תורת ה׳, אשר נמסרה לכם באמצעות המלאכים.“

54כששמעו חברי הסנהדרין את האשמותיו של סטפנוס, נמלאו זעם וחרקו בשיניהם. 55אך סטפנוס, שהיה מלא רוח הקודש, נעץ מבטו בשמים, וראה את כבוד האלוהים ואת ישוע עומד לימין האלוהים. 56”הנני רואה את השמים נפתחים, ואת ישוע המשיח עומד לימין האלוהים!“ אמר להם סטפנוס.

57לשמע דברים אלה אטמו את אוזניהם, צרחו בכל כוחם והתנפלו עליו. 58הם גררו אותו אל מחוץ לעיר ורגמו אותו באבנים. מבצעי גזר־הדין פשטו את מעיליהם, והניחו אותם למשמרת לרגלי בחור אחד בשם שאול.

59בשעה שפגעו בו האבנים זו אחר זו התפלל סטפנוס: ”אדוני, ישוע, קבל נא את רוחי!“ 60ואז נפל על ברכיו וזעק: ”אדוני, סלח להם על החטא הזה!“ ובאותו רגע נפח את נשמתו.