ሐዋርያት ሥራ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 4:1-37

ጴጥሮስና ዮሐንስ በአይሁድ ሸንጎ ፊት

1ጴጥሮስና ዮሐንስ ለሕዝቡ እየተናገሩ ሳሉ፣ ካህናትና የቤተ መቅደሱ ጥበቃ ኀላፊ እንዲሁም ሰዱቃውያን ድንገት ወደ እነርሱ መጡ። 2እነርሱም ሐዋርያት ሕዝቡን በማስተማራቸውና በኢየሱስ ስለተገኘው ትንሣኤ ሙታን በመስበካቸው እጅግ ተቈጡ። 3ጴጥሮስና ዮሐንስን ያዟቸው፤ ጊዜውም ምሽት ስለ ነበረ እስኪነጋ ድረስ ወህኒ ቤት አሳደሯቸው። 4ይሁን እንጂ ቃሉን ከሰሙት መካከል ብዙዎቹ አመኑ፤ የወንዶቹም ቍጥር ወደ አምስት ሺሕ ከፍ አለ።

5በማግስቱም አለቆቻቸውና፣ ሽማግሌዎቻቸው እንዲሁም ጸሐፍት በኢየሩሳሌም ተሰበሰቡ። 6ሊቀ ካህናቱ ሐና፣ ቀያፋ፣ ዮሐንስ፣ እስክንድሮስና የሊቀ ካህናቱ ቤተ ዘመዶች ሁሉ በዚያ ተገኝተው ነበር። 7እነርሱም ጴጥሮስንና ዮሐንስን በመካከል አቁመው፣ “ይህን ያደረጋችሁት በምን ኀይል ወይም በማን ስም ነው?” ብለው ጠየቋቸው።

8በዚህ ጊዜ፣ ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ እንዲህ አላቸው፤ “እናንተ የሕዝብ አለቆችና ሽማግሌዎች ሆይ፤ 9ዛሬ ለዚህ ሽባ ሰው ስለ ተደረገው በጎ ሥራ፣ እንዴት እንደ ዳነ የምትጠይቁን ከሆነ፣ 10እናንተ በሰቀላችሁት፣ እግዚአብሔር ግን ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም መዳኑንና ፊታችሁ መቆሙን እናንተም ሆናችሁ የእስራኤል ሕዝብ ሁሉ ይህን ይወቅ። 11እርሱም፣

“ ‘እናንተ ግንበኞች የናቃችሁት፣

የማእዘን ራስ4፥11 ወይም የማእዘን ድንጋይ የሆነው ድንጋይ’

ነው። 12ድነት በሌላ በማንም አይገኝም፤ እንድንበት ዘንድ ለሰዎች የተሰጠ ከዚህ ስም በስተቀር ሌላ ስም ከሰማይ በታች የለምና።”

13ሰዎቹም፣ ጴጥሮስና ዮሐንስ እንዲህ በድፍረት ሲናገሩ ባዩአቸው ጊዜ፣ ያልተማሩ ተራ ሰዎች መሆናቸውን ተረድተው ተደነቁ፤ ከኢየሱስ ጋር እንደ ነበሩም ተገነዘቡ። 14የተፈወሰውን ሰው እዚያው ከእነርሱ ጋር ቆሞ ስላዩት የሚናገሩበትን ሰበብ ዐጡ። 15ስለዚህ ከሸንጎው እንዲያወጧቸው አዘዙ፤ ከዚያም በአንድነት ተሰብስበው ተመካከሩ፤ 16እንዲህም ተባባሉ፤ “እንግዲህ እነዚህን ሰዎች ምን እናድርጋቸው? በኢየሩሳሌም የሚኖር ሁሉ በእነርሱ እጅ የተደረገውን ድንቅ ታምር ዐውቋል፣ ስለዚህ ይህን ማስተባበል አንችልም፤ 17ይሁን እንጂ፣ ይህ ነገር ከእንግዲህ በሕዝቡ መካከል ይበልጥ እንዳይስፋፋ፣ እነዚህም ሰዎች ዳግመኛ በዚህ ስም ለማንም እንዳይናገሩ እናስጠንቅቃቸው።”

18ከጠሯቸውም በኋላ፣ በኢየሱስ ስም ፈጽሞ እንዳይናገሩና እንዳያስተምሩ አዘዟቸው። 19ጴጥሮስና ዮሐንስ ግን መልሰው እንዲህ አሏቸው፤ “ከእግዚአብሔር ይልቅ ለእናንተ መታዘዝ በእግዚአብሔር ፊት ይገባ እንደ ሆነ እስቲ እናንተው ፍረዱ፤ 20እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ወደ ኋላ አንልም።”

21እንደ ገና ከዛቱባቸው በኋላም ለቀቋቸው፤ ምክንያቱም ሕዝቡ ሁሉ ስለ ሆነው ነገር እግዚአብሔርን ያመሰግኑ ስለ ነበር ሊቀጧቸው አልቻሉም፤ 22በዚህ ታምር የተፈወሰውም ሰው ዕድሜው ከአርባ ዓመት በላይ ነበርና።

የአማኞች ጸሎት

23ጴጥሮስና ዮሐንስም ከተፈቱ በኋላ ወደ ወገኖቻቸው ተመልሰው፣ የካህናት አለቆችና ሽማግሌዎች ያሏቸውን ሁሉ ነገሯቸው። 24እነርሱም ይህን በሰሙ ጊዜ ድምፃቸውን በአንድነት ወደ እግዚአብሔር ከፍ አድርገው እንዲህ አሉ፤ “ልዑል ጌታ ሆይ፤ አንተ ሰማይንና ምድርን፣ ባሕርንም፣ በውስጣቸውም የሚኖሩትን ሁሉ ፈጥረሃል፤ 25በመንፈስ ቅዱስም አማካይነት በአገልጋይህ በአባታችን በዳዊት አፍ እንዲህ ብለህ ተናግረሃል፤

“ ‘አሕዛብ ለምን በቍጣ ተነሣሡ?

ሕዝቡስ ለምን በከንቱ አሤሩ?

26የምድር ነገሥታት ተሰለፉ፤

ገዦችም በአንድነት ተሰበሰቡ፤

በጌታ ላይ፣

በተቀባውም4፥26 ወይም ክርስቶስ ወይም መሲሕ ማለት ነው። ላይ ተከማቹ።’

27በርግጥም ሄሮድስና ጳንጥዮስ ጲላጦስ ከአሕዛብና ከእስራኤል ሕዝብ ጋር በዚህች ከተማ አንተ በቀባኸው በቅዱሱ ብላቴናህ በኢየሱስ ላይ ለማሤር ተሰበሰቡ፤ 28ይህም የሆነው የአንተ ክንድና ፈቃድ ጥንት የወሰኑት እንዲፈጸም ነው። 29አሁንም ጌታ ሆይ፤ ዛቻቸውን ተመልከት፤ ባሪያዎችህም ቃልህን በፍጹም ድፍረት መናገር እንዲችሉ አድርጋቸው። 30ለመፈወስ እጅህን ዘርጋ፤ በቅዱሱ ብላቴናህም በኢየሱስ ስም ድንቅና ታምራት አድርግ።”

31ከጸለዩም በኋላ የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፤ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ የእግዚአብሔርንም ቃል በድፍረት ተናገሩ።

የአማኞች ማኅበራዊ አኗኗር

32ያመኑትም ሁሉ በአንድ ልብና በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ነበር፤ ያላቸውም ሁሉ የጋራ ነበር እንጂ የራሱ የሆነውን ሀብት እንኳ እንደ ግሉ የሚቈጥር ማንም አልነበረም። 33ሐዋርያትም ስለ ጌታ ኢየሱስ ትንሣኤ በታላቅ ኀይል መመስከራቸውን ቀጠሉ፤ በሁላቸውም ላይ ታላቅ ጸጋ ነበር። 34ከመካከላቸውም አንድ ችግረኛ አልነበረም፤ ምክንያቱም መሬትም ሆነ ቤት የነበራቸውን ሁሉ እየሸጡ ዋጋውን አምጥተው፣ 35በሐዋርያት እግር ሥር በማስቀመጥ ለእያንዳንዱ በሚያስፈልገው መጠን ያካፍሉት ነበር።

36በቆጵሮስ የሚኖር ዮሴፍ የሚባል አንድ ሌዋዊ ነበረ፤ ሐዋርያትም “በርናባስ” ብለው ጠሩት፤ ትርጕሙም “የመጽናናት ልጅ” ማለት ነው፤ 37እርሱም መሬቱን ሸጦ፣ ገንዘቡን አምጥቶ በሐዋርያት እግር ሥር አስቀመጠ።

Thai New Contemporary Bible

กิจการของอัครทูต 4:1-37

เปโตรกับยอห์นต่อหน้าสภาแซนเฮดริน

1ขณะเปโตรกับยอห์นกล่าวแก่ประชาชนอยู่ พวกปุโรหิต หัวหน้ายามพระวิหาร และพวกสะดูสีก็มาหา 2พวกเขางุ่นง่านใจมากเพราะอัครทูตสั่งสอนและประกาศแก่คนทั้งหลายถึงการเป็นขึ้นจากตายโดยอ้างถึงการคืนพระชนม์ของพระเยซู 3เขาได้จับเปโตรและยอห์นไว้และเนื่องจากเย็นแล้วจึงขังทั้งสองคนไว้ในคุกจนกระทั่งวันรุ่งขึ้น 4แต่หลายคนที่ได้ยินคำสอนก็เชื่อ จำนวนของผู้เชื่อเพิ่มขึ้นเป็นห้าพันคนโดยประมาณ

5วันรุ่งขึ้นพวกผู้นำ ผู้อาวุโส และเหล่าธรรมาจารย์มาประชุมกันในกรุงเยรูซาเล็ม 6ทั้งมหาปุโรหิตอันนาส คายาฟาส ยอห์น อเล็กซานเดอร์และคนอื่นๆ ในครอบครัวของมหาปุโรหิตก็อยู่ที่นั่น 7พวกเขาให้นำตัวเปโตรกับยอห์นมาอยู่ต่อหน้าและถามว่า “พวกเจ้าทำเช่นนี้โดยฤทธิ์อำนาจหรือในนามของผู้ใด?”

8แล้วเปโตรซึ่งเปี่ยมด้วยพระวิญญาณบริสุทธิ์ก็กล่าวแก่พวกเขาว่า “เรียนท่านผู้นำและเหล่าผู้อาวุโสของประชาชน! 9หากเราถูกเรียกตัวมาให้การในวันนี้เพราะเรื่องที่แสดงความเมตตาแก่คนง่อยและถูกสอบสวนว่าเขาหายพิการได้อย่าง ไร 10ทั้งท่านและปวงประชากรอิสราเอลก็จงทราบเถิดว่าสิ่งนี้เป็นโดยพระนามของพระเยซูคริสต์ชาวนาซาเร็ธซึ่งท่านได้ตรึงตายที่ไม้กางเขนแต่พระเจ้าทรงให้พระองค์เป็นขึ้นจากตายโดยพระนามของพระองค์นั้นเอง ชายผู้ที่ยืนอยู่ต่อหน้าท่านนี้จึงได้รับการรักษาให้หาย 11พระองค์ทรงเป็น

“ ‘ศิลาที่ท่านทั้งหลายผู้ก่อได้ทอดทิ้ง

ซึ่งได้กลับกลายเป็นศิลามุมเอก4:11 หรือศิลาหัวมุมแล้ว’4:11 สดด.118:22

12ในผู้อื่นไม่มีความรอดเลยเพราะไม่ได้ประทานนามอื่นที่จะช่วยให้เราทั้งหลายรอดแก่มนุษย์ทั่วใต้ฟ้า”

13เมื่อพวกเขาเห็นความกล้าหาญของเปโตรกับยอห์นและตระหนักว่าคนทั้งสองเป็นชาวบ้านธรรมดาไร้การศึกษาก็ประหลาดใจและนึกขึ้นได้ว่าคนเหล่านี้เคยอยู่กับพระเยซู 14แต่เพราะเขาได้เห็นชายที่หายโรคยืนอยู่กับคนเหล่านี้เขาก็พูดอะไรไม่ได้ 15ดังนั้นจึงสั่งให้คนทั้งสองออกไปจากสภาแซนเฮดรินจากนั้นจึงหารือกันว่า 16“เราจะทำอย่างไรกับพวกนี้ดี? ทุกคนที่อยู่ในกรุงเยรูซาเล็มรู้ว่าพวกเขาได้ทำการอัศจรรย์อันโดดเด่นประการหนึ่งและเราไม่อาจปฏิเสธได้ 17แต่เพื่อยุติเรื่องนี้ไม่ให้เลื่องลือไปอีกในหมู่ประชาชนเราต้องสั่งห้ามพวกนี้ไม่ให้เอ่ยนามนั้นกับใครอีก”

18จากนั้นพวกเขาจึงเรียกตัวคนทั้งสองมาอีกและสั่งห้ามไม่ให้พูดหรือสอนในพระนามพระเยซูอีกเลย 19แต่เปโตรกับยอห์นกล่าวตอบว่า “พวกท่านตัดสินเอาเองเถิดว่าเป็นการถูกต้องแล้วหรือในสายพระเนตรของพระเจ้าที่จะเชื่อฟังพวกท่านยิ่งกว่าเชื่อฟังพระเจ้า? 20เพราะพวกเราต้องพูดในสิ่งที่ได้เห็นและได้ยินมา”

21หลังจากขู่สำทับแล้วพวกเขาก็ปล่อยคนทั้งสองไป พวกเขาตัดสินใจไม่ได้ว่าจะลงโทษคนพวกนี้ได้อย่างไรเพราะประชาชนทั้งปวงพากันสรรเสริญพระเจ้าสำหรับสิ่งที่เกิดขึ้น 22เนื่องจากชายคนที่ได้รับการรักษาให้หายอย่างอัศจรรย์นั้นอายุกว่าสี่สิบปีแล้ว

คำอธิษฐานของผู้เชื่อ

23เมื่อได้รับการปล่อยตัวแล้วเปโตรกับยอห์นก็กลับมาหาพวกพ้องของตน แล้วเล่าทุกอย่างตามที่พวกหัวหน้าปุโรหิตกับผู้อาวุโสได้กล่าวกับพวกเขา 24เมื่อพวกเขาได้ฟังแล้วก็พร้อมใจกันเปล่งเสียงอธิษฐานทูลพระเจ้าว่า “ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้าองค์เจ้าชีวิต พระองค์ทรงสร้างฟ้าสวรรค์ แผ่นดินโลก ท้องทะเลและสรรพสิ่งในนั้น 25พระองค์ตรัสโดยพระวิญญาณบริสุทธิ์ผ่านปากผู้รับใช้ของพระองค์ คือดาวิดบรรพบุรุษของเราว่า

“ ‘เหตุใดประชาชาติทั้งหลายจึงลุกฮือ

ชนชาติต่างๆ จะวางแผนให้ป่วยการไปทำไม?

26เหล่ากษัตริย์ของโลกตั้งตนขัดขืน

บรรดาผู้ปกครองรวมตัวกันเพื่อวางแผนต่อต้านองค์พระผู้เป็นเจ้า

และต่อต้านผู้หนึ่งซึ่งพระองค์ทรงเจิมตั้งไว้4:26 คือพระคริสต์ หรือพระเมสสิยาห์4:26 สดด.2:1,2

27อันที่จริงเฮโรดกับปอนทิอัสปีลาตร่วมกับคนต่างชาติและประชาชนชนชาวอิสราเอลในกรุงนี้คบคิดกันต่อต้านองค์พระเยซูผู้รับใช้บริสุทธิ์ของพระองค์ผู้ซึ่งพระองค์ได้ทรงเจิมตั้งไว้นั้น 28สิ่งที่พวกเขาได้ทำไปนั้นเป็นสิ่งที่ฤทธานุภาพและพระดำริของพระองค์ได้กำหนดไว้ก่อนแล้วว่าจะเกิดขึ้น 29บัดนี้ พระองค์เจ้าข้า ขอทรงพิจารณาคำข่มขู่ของเขา และขอให้ผู้รับใช้ของพระองค์สามารถกล่าวพระวจนะของพระองค์ด้วยใจกล้าหาญอย่างมาก 30ขอทรงเหยียดพระหัตถ์ออกรักษาโรคและกระทำหมายสำคัญและปาฏิหาริย์ต่างๆ โดยพระนามของพระเยซูผู้รับใช้บริสุทธิ์ของพระองค์เถิด”

31หลังจากพวกเขาอธิษฐานจบสถานที่ซึ่งพวกเขาประชุมกันอยู่นั้นก็สะเทือนสะท้านและพวกเขาล้วนเปี่ยมด้วยพระวิญญาณบริสุทธิ์และกล่าวพระวจนะของพระเจ้าด้วยใจกล้า

ผู้เชื่อแบ่งปันสิ่งที่ตนมี

32ผู้เชื่อทั้งปวงมีความคิดจิตใจเป็นหนึ่งเดียวกันไม่มีใครอ้างว่าทรัพย์สินที่มีอยู่เป็นของตนเองแต่พวกเขาแบ่งปันทุกสิ่งที่ตนมี 33โดยฤทธิ์อำนาจอันยิ่งใหญ่ เหล่าอัครทูตเป็นพยานอย่างต่อเนื่องถึงการคืนพระชนม์ขององค์พระเยซูเจ้าและพระคุณมากล้นมีแก่พวกเขาทุกคน 34ในหมู่พวกเขาไม่มีใครขัดสนเพราะบางครั้งบางคราวผู้ที่มีบ้านหรือที่ดินก็นำไปขายและนำเงินที่ได้ 35มาวางแทบเท้าของอัครทูตจากนั้นจึงแจกจ่ายให้ทุกคนตามความจำเป็น

36โยเซฟคนเลวีจากเกาะไซปรัสซึ่งอัครทูตเรียกว่าบารนาบัส (แปลว่าลูกแห่งการให้กำลังใจ) 37ได้ขายที่ดินของเขาและนำเงินมาวางแทบเท้าของอัครทูต