ሐዋርያት ሥራ 2 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 2:1-47

በበዓለ አምሳ ቀን መንፈስ ቅዱስ ወረደ

1የበዓለ አምሳ ቀን በደረሰ ጊዜ ሁሉም በአንድነት፣ በአንድ ስፍራ ተሰብስበው ነበር። 2ድንገትም እንደ ብርቱ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ከሰማይ መጥቶ ተቀምጠው የነበሩበትን ቤት እንዳለ ሞላው። 3የእሳት ምላሶች የሚመስሉም ታዩአቸው፤ ተከፋፍለውም በእያንዳንዳቸው ላይ ዐረፉ። 4ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ መንፈስም እንዲናገሩ በሰጣቸው መጠን በሌሎች ቋንቋዎች2፥4 ወይም ልሳኖች እንዲሁም በ11 ይናገሩ ጀመር።

5በዚህ ጊዜ ከሰማይ በታች ካለው ሕዝብ ሁሉ የመጡና እግዚአብሔርን የሚፈሩ አይሁድ በኢየሩሳሌም ነበሩ። 6ይህን ድምፅ ሲሰሙ፣ ብዙ ሕዝብ በአንድነት ተሰበሰቡ፤ እያንዳንዱም ሰው፣ ሰዎቹ በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ በመስማቱ ግራ ተጋባ፤ 7በመገረምና በመደነቅም እንዲህ አሉ፤ “እነዚህ የሚነጋገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? 8ታዲያ፣ እያንዳንዳችን በተወለድንበት፣ በራሳችን ቋንቋ ሲናገሩ የምንሰማቸው እንዴት ቢሆን ነው? 9እኛ የጳርቴና፣ የሜድ፣ የኢላሜጤም ሰዎች፣ በመስጴጦምያ፣ በይሁዳ፣ በቀጰዶቅያ፣ በጳንጦስ፣ በእስያ፣ 10በፍርግያ፣ በጵንፍልያ፣ በግብፅ፣ በቀሬና አጠገብ ባሉት በሊቢያ አውራጃዎች የምንኖር፣ ከሮም የመጣን 11አይሁድና ወደ ይሁዲነት የገባን፣ የቀርጤስና የዐረብ ሰዎች ስንሆን፣ ሰዎቹ የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በየቋንቋችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን!” 12ሁሉም በአድናቆትና ግራ በመጋባት፣ “ይህ ነገር ምን ይሆን?” ተባባሉ።

13አንዳንዶቹ ደግሞ “ያልፈላ ብዙ የወይን ጠጅ2፥13 ወይም ጣፋጭ ወይን ጠጥተዋል” በማለት አፌዙባቸው።

ጴጥሮስ ለሕዝቡ ንግግር አደረገ

14በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ ከዐሥራ አንዱ ጋር ተነሥቶ ቆመ፤ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ለሕዝቡ ተናገረ፤ “እናንት የይሁዳ ሰዎች፤ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁሉ፤ ይህን አንድ ነገር ዕወቁ፤ በጥሞናም አድምጡ። 15ጊዜው ገና ከጧቱ ሦስት ሰዓት ስለሆነ፣ እናንተ እንደምታስቡት እነዚህ ሰዎች አልሰከሩም። 16ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል እንዲህ ተብሎ የተነገረ ነው፤

17“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በመጨረሻው ቀን፣

መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ፤

ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤

ጕልማሶቻችሁ ራእይ ያያሉ፤

ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ።

18በዚያ ጊዜ በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮቼ ላይ፣

መንፈሴን አፈስሳለሁ፤

እነርሱም ትንቢት ይናገራሉ።

19በላይ በሰማያት ድንቅ ነገሮችን፣

አሳያለሁ፤ በታች በምድርም ምልክቶችን እሰጣለሁ፤

ደምና እሳት፣ የጢስም ጭጋግ ይሆናል።

20ታላቅና ክቡር የሆነው የጌታ ቀን ከመምጣቱ በፊት፣

ፀሓይ ወደ ጨለማ፣

ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣሉ።

21የጌታን ስም፣

የሚጠራ ሁሉ ይድናል።’

22“የእስራኤል ሰዎች ሆይ፤ ይህን ቃል ስሙ፤ እናንት ራሳችሁ እንደምታውቁት፣ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ታምራትን፣ ድንቅ ነገሮችንና ምልክቶችን በእርሱ በኩል በማድረግ ለናዝሬቱ ኢየሱስ መስክሮለታል። 23እግዚአብሔር በጥንት ውሳኔውና በቀደመው ዕውቀቱ ይህን ሰው አሳልፎ በእጃችሁ ሰጣችሁ፤ እናንተም በክፉ ሰዎች2፥23 ወይም ሕግ በሌላቸው ሰዎች (አሕዛብን ያመለክታል) እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት። 24እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አስወግዶ አስነሣው፤ ሞት ይዞ ሊያስቀረው አልቻለምና። 25ዳዊትም ስለ እርሱ እንዲህ ይላል፤

“ ‘ጌታን ሁልጊዜ በፊቴ አየዋለሁ፤

እርሱ በቀኜ ነውና፣

ከቶ አልታወክም።

26ስለዚህ ልቤ ደስ አለው፤ አንደበቴም ሐሤት አደረገ፤

ሥጋዬም በተስፋ ይኖራል።

27ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና፤

ቅዱስህም መበስበስን እንዲያይ አታደርግም።

28የሕይወትን መንገድ እንዳውቅ አደረግኸኝ፤

በፊትህም በሐሤት ትሞላኛለህ።’

29“ወንድሞች ሆይ፤ ከቀደምት አባቶች ዳዊት ሞቶ እንደ ተቀበረ፣ መቃብሩም እስከ ዛሬ ድረስ በመካከላችን እንደሚገኝ በድፍረት መናገር እችላለሁ። 30ነቢይ በመሆኑም፣ እግዚአብሔር ከዘሮቹ አንዱን በዙፋኑ ላይ እንደሚያስቀምጥ በመሐላ ቃል የገባለት መሆኑን ዐወቀ። 31ይህን አስቀድሞ በማየቱ እርሱ በሲኦል እንደማይቀርና ሥጋውም እንደማይበሰብስ ስለ ክርስቶስ2፥31 ወይም መሲሕ፤ በግሪኩ ክርስቶስ፣ በዕብራይስጡ መሲሕ የሁለቱም ቃላት ትርጕም የተቀባው ማለት ነው፤ እንዲሁም በ36 ትንሣኤ ተናገረ። 32ይህን ኢየሱስ፣ እግዚአብሔር ከሞት አስነሣው፤ እኛም ሁላችን ለዚህ ነገር ምስክሮች ነን። 33ስለዚህ በእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ ካለ በኋላ፣ የመንፈስ ቅዱስን ተስፋ ከአብ ተቀብሎ አሁን የምታዩትንና የምትሰሙትን አፈሰሰው። 34ዳዊት ወደ ሰማያት አልወጣም፤ እርሱ ራሱ ግን እንዲህ ብሏል፤

“ ‘ጌታ ጌታዬን፣

35“ጠላቶችህን ለእግርህ መረገጫ፣

እስከማደርግልህ ድረስ፣

በቀኜ ተቀመጥ” አለው።’

36“እንግዲህ፣ እግዚአብሔር ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን፣ ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ ይረዳ!”

37ሕዝቡም ይህን በሰሙ ጊዜ ልባቸው እጅግ ተነካ፤ ጴጥሮስንና ሌሎቹንም ሐዋርያት፣ “ወንድሞች ሆይ፤ ታዲያ ምን እናድርግ?” አሏቸው።

38ጴጥሮስም እንዲህ አላቸው፤ “ንስሓ ግቡ፤ ኀጢአታችሁም እንዲሰረይላችሁ፣ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ። 39የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ እንዲሁም ጌታ አምላካችን ወደ ራሱ ለሚጠራቸው፣ በሩቅ ላሉትም ሁሉ ነውና።”

40በሌላ ብዙ ቃል እየመሰከረላቸው፣ “ከዚህ ጠማማ ትውልድ ራሳችሁን አድኑ” በማለት አስጠነቀቃቸው። 41ቃሉን የተቀበሉትም ተጠመቁ፤ በዚያ ቀን ሦስት ሺሕ ያህል ሰዎች በቍጥራቸው ላይ ተጨመሩ።

የአማኞች የኅብረት ኑሮ

42እነርሱም በሐዋርያት ትምህርትና በኅብረት፣ እንጀራውንም በመቍረስና በጸሎት ይተጉ ነበር። 43በሐዋርያት እጅ ብዙ ድንቅና ታምራት ይደረግ ስለ ነበር፣ ሰው ሁሉ ፍርሀት ዐደረበት። 44ያመኑት ሁሉ በአንድነት ነበሩ፤ ያላቸውንም ሁሉ የጋራ አደረጉ። 45ሀብታቸውንና ንብረታቸውንም እየሸጡ ለእያንዳንዱ ሰው የሚያስፈልገውን ያህል ይሰጡት ነበር። 46በየዕለቱ በቤተ መቅደስ በአንድነት እየተገናኙ፣ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ በደስታና በቀና ልብ ይመገቡ ነበር፤ 47እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ፣ በሕዝቡ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው፤ ጌታም የሚድኑትን በቍጥራቸው ላይ ዕለት በዕለት ይጨምር ነበር።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

使徒行傳 2:1-47

聖靈降臨

1五旬節那天,門徒聚集在一起。 2忽然,天上發出一陣響聲,好像狂風呼嘯而過,充滿了他們所在的房子, 3又有火焰般的舌頭顯現出來,分別落在各人的頭上。 4大家都被聖靈充滿,得到聖靈所賜的才能,說起別的語言來。

5當時耶路撒冷住著從各國回來的虔誠的猶太人。 6眾人聽見這陣響聲便趕過來,聽見門徒在說他們各自的語言,都十分納悶, 7驚詫地說:「看啊!這些說話的不都是加利利人嗎? 8怎麼會說我們各自的語言呢? 9我們這裡有帕提亞人、瑪代人、以攔人,以及住在美索不達米亞猶太加帕多迦本都亞細亞10弗呂迦旁非利亞埃及和靠近古利奈利比亞的人,還有從羅馬來的猶太人和改信猶太教的人、 11克里特人和阿拉伯人。我們都聽見他們在用我們各自的語言訴說上帝的偉大!」 12他們都大感驚奇和困惑,彼此議論說:「這到底是怎麼回事?」

13有些人就譏笑說:「他們不過是被新酒灌醉了!」

彼得講道

14彼得和其他十一位使徒都站起來,他大聲對眾人說:「各位猶太同胞和住在耶路撒冷的人啊,請留心聽!我告訴你們這是怎麼回事。 15你們以為這些人是醉了,其實不是,因為現在才早上九點鐘。 16你們眼前看見的正是先知約珥所說的,

17『上帝說,在末後的日子,

我要將我的靈澆灌所有的人,

你們的兒女要說預言,

青年要見異象,

老人要做異夢。

18那時,我要將我的靈澆灌我的奴僕和婢女,

他們都要說預言。

19在天上,我要顯異兆;

在地上,我要行神蹟,有血、有火、有濃煙。

20太陽要變得昏暗,

月亮要變得血紅。

這都要發生在主偉大榮耀的日子來臨以前。

21那時,凡求告主名的,都必得救。』

22「各位以色列人啊,請留心聽。上帝藉著拿撒勒人耶穌在你們中間行了異能、奇事和神蹟,以證明拿撒勒人耶穌是祂派來的。這是你們都知道的。 23上帝照著自己的計劃和預知把耶穌交在你們手裡,你們藉著邪惡之人的手把祂釘死在十字架上了。 24但上帝為祂解除了死亡的痛苦,使祂從死裡復活,因為祂不可能被死亡拘禁。 25論到耶穌,大衛曾說,

『我看見主常在我面前,

祂在我右邊,我必不動搖。

26因此我的心歡喜,我的口頌讚,

我的身體也要活在盼望中。

27因為你不會把我的靈魂撇在陰間,

也不會讓你的聖者身體朽壞。

28你已把生命之路指示我,

叫我在你面前充滿喜樂。』

29「弟兄們,我肯定地對你們說,先祖大衛死了,埋葬了,他的墳墓至今還在這裡。 30大衛是先知,知道上帝曾起誓要從他的後裔中選立一人繼承他的王位。 31他預先知道這事,講到基督的復活,說,『祂的靈魂不會被撇在陰間,祂的身體也不會朽壞』。 32上帝已經使這位耶穌復活了!我們都是這件事的見證人。 33現在祂升到上帝的右邊,從天父領受了所應許的聖靈,並將聖靈澆灌下來,你們今天也耳聞目睹了。 34大衛並沒有升到天上,但他曾說,

『主對我主說,

你坐在我的右邊,

35等我使你的仇敵成為你的腳凳。』

36「所以,全體以色列人啊!你們應當確實地知道,上帝已經立這位被你們釘在十字架上的耶穌為主,為基督了。」

37他們聽了彼得的話,覺得扎心,就對彼得和其他使徒說:「弟兄們,我們該怎麼辦呢?」 38彼得說:「你們每一個人都要悔改,奉耶穌基督的名受洗,使你們的罪得到赦免,你們就必領受上帝所賜的聖靈。 39因為這應許是給你們和你們的兒女,以及遠方的人,就是所有被主——我們的上帝呼召的人。」

40然後,彼得還講了許多話警戒、勸勉他們,說:「你們要保守自己脫離這邪惡的世代。」

41結果,那天約有三千人相信了他傳的道,接受了洗禮。 42他們都一心遵守使徒的教導,一起團契、掰餅、禱告。

43大家都滿心敬畏上帝。使徒又行了很多神蹟奇事。 44信徒聚在一起,共用所有的東西。 45他們把田產家業變賣了,按照各人的需要把錢分給大家。 46他們天天同心合意地聚集在聖殿裡敬拜上帝,又在各人家中擘餅聚會,以歡喜、慷慨的心分享食物, 47讚美上帝,受到眾人的喜愛。主使得救的人數與日俱增。