ሐዋርያት ሥራ 14 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 14:1-28

ጳውሎስና በርናባስ በኢቆንዮን

1በኢቆንዮንም ጳውሎስና በርናባስ አብረው ወደ አይሁድ ምኵራብ ገቡ፤ በዚያም በሚገባ ስላስተማሩ፣ ከአይሁድም ከግሪክም እጅግ ብዙ ሰዎች አመኑ። 2ያላመኑት አይሁድ ግን፣ አሕዛብን አነሣሥተው ወንድሞችን እንዲጠሉ አደረጓቸው። 3ጳውሎስና በርናባስም ስለ ጌታ በድፍረት እየተናገሩ ብዙ ጊዜ እዚያው ቈዩ፤ ጌታም የሚናገሩትን የጸጋውን ቃል በታምራዊ ምልክትና በድንቅ ሥራ እየደገፈ ያረጋግጥላቸው ነበር። 4የከተማውም ሕዝብ ተከፋፈለ፤ ገሚሱ ከአይሁድ ጋር፣ ገሚሱም ከሐዋርያት ጋር ሆነ። 5በዚህ ጊዜ አሕዛብና አይሁድ ከመሪዎቻቸው ጋር ተባብረው ሊያንገላቷቸውና በድንጋይ ሊያስወግሯቸው ሞከሩ። 6እነርሱ ግን ይህን እንዳወቁ ልስጥራንና ደርቤን ወደተባሉት ወደ ሊቃኦንያ ከተሞችና በዙሪያቸው ወዳለው አገር ሸሹ፤ 7በዚያም ወንጌልን መስበክ ቀጠሉ።

ጳውሎስና በርናባስ በልስጥራና በደርቤን

8በልስጥራንም፣ እግሩ ዐንካሳ የሆነና ከተወለደ ጀምሮ ፈጽሞ በእግሩ ሄዶ የማያውቅ ሽባ ሰው ተቀምጦ ነበር። 9ይህም ሰው ጳውሎስ ሲናገር ያደምጥ ነበር። ጳውሎስም ወደ እርሱ ትኵር ብሎ ተመለከተና ለመዳን እምነት እንዳለው ባየ ጊዜ 10በታላቅ ድምፅ፣ “ቀጥ ብለህ በእግርህ ቁም!” አለው፤ በዚህ ጊዜ ዘልሎ ተነሣና መራመድ ጀመረ።

11ሕዝቡም ጳውሎስ ያደረገውን ባዩ ጊዜ፣ በሊቃኦንያ ቋንቋ፣ “አማልክት በሰው ተመስለው ወደ እኛ ወርደዋል!” ብለው ጮኹ፤ 12በርናባስን “ድያ” አሉት፤ ጳውሎስም ዋና ተናጋሪ ስለ ነበር “ሄርሜን” አሉት። 13ከከተማው ወጣ ብሎ የነበረው የድያ ቤተ መቅደስ ካህንም፣ ኰርማዎችንና የአበባ ጕንጕኖችን ወደ ከተማው መግቢያ አምጥቶ፣ ከሕዝቡ ጋር ሆኖ ሊሠዋላቸው ፈለገ።

14ሐዋርያቱ በርናባስና ጳውሎስ ይህን በሰሙ ጊዜ ልብሳቸውን ቀድደው ወደ ሕዝቡ መካከል ሮጡ፤ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው እንዲህ አሉ፤ 15“እናንት ሰዎች፤ ለምን ይህን ታደርጋላችሁ? እኛም እኮ እንደ እናንተው ሰዎች ነን። እናንተም ደግሞ ከዚህ ከንቱ ነገር ርቃችሁ ሰማይንና ምድርን፣ ባሕርንም በውስጣቸውም የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ፈጠረ ወደ ሕያው እግዚአብሔር እንድትመለሱ ወንጌልን እንሰብክላችኋለን። 16እርሱ ባለፉት ትውልዶች፣ ሕዝቦች ሁሉ በገዛ መንገዳቸው እንዲሄዱ ተዋቸው፤ 17ይሁን እንጂ ዝናብን ከሰማይ እንዲሁም ፍሬያማ ወቅቶችን በመስጠቱ፣ ደግሞም ልባችሁን በመብልና በደስታ በማርካቱ መልካምን በማድረግ ራሱን ያለ ምስክር አልተወም።” 18ይህን ሁሉ ተናግረው እንኳ፣ ሕዝቡ እንዳይሠዋላቸው ያስተዉት በብዙ ችግር ነበር።

19አይሁድ ግን ከአንጾኪያና ከኢቆንዮን መጥተው፣ ሕዝቡን አግባቡ፤ ጳውሎስንም በድንጋይ ከወገሩት በኋላ፣ የሞተ መስሏቸው ጐትተው ከከተማው ወደ ውጭ አወጡት። 20ሆኖም ደቀ መዛሙርት ከብበውት እንዳሉ ተነሣ፤ ወደ ከተማም ገባ። በማግስቱም ከበርናባስ ጋር ወደ ደርቤን ሄዱ።

ጳውሎስና በርናባስ በሶርያ ወዳለችው አንጾኪያ ተመለሱ

21ጳውሎስና በርናባስ በደርቤን የምሥራቹን ቃል ሰብከው፣ ብዙ ደቀ መዛሙርትም ካፈሩ በኋላ፣ ወደ ልስጥራን፣ ወደ ኢቆንዮንና ወደ አንጾኪያ ተመለሱ። 22የደቀ መዛሙርቱንም ልብ በማበረታታትና በእምነታቸው ጸንተው እንዲኖሩ በመምከር፣ “ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት በብዙ መከራ ማለፍ አለብን” አሏቸው። 23ከዚያም በየአብያተ ክርስቲያናቱ ሽማግሌዎችን ከሾሙላቸው በኋላ፣ በጾምና በጸሎት ላመኑበት ጌታ ዐደራ ሰጧቸው። 24በጲስድያም ዐልፈው ወደ ጵንፍልያ መጡ፤ 25በጴርጌንም ቃሉን ከሰበኩ በኋላ፣ ወደ አጣልያ ወረዱ።

26ከአጣልያም፣ እስካሁን ላከናወኑት ሥራ፣ ለእግዚአብሔር ጸጋ በዐደራ ወደ ተሰጡባት ከተማ ወደ አንጾኪያ በመርከብ ተመለሱ። 27እዚያም በደረሱ ጊዜ፣ ቤተ ክርስቲያንን በአንድነት ሰብስበው፣ እግዚአብሔር በእነርሱ አማካይነት ያደረገውን ሁሉ፣ ደግሞም ለአሕዛብ እንዴት የእምነትን በር እንደ ከፈተላቸው ተናገሩ። 28በዚያም ከደቀ መዛሙርት ጋር ብዙ ጊዜ ተቀመጡ።

Knijga O Kristu

Djela Apostolska 14:1-28

Pavao i Barnaba u Ikoniju

1U Ikoniju14:1 Ikonij, Listra i Derba (14:6) bili su gradovi na području današnje Turske. Pavao i Barnaba također uđu u židovsku sinagogu te su propovijedali s takvom silom da je povjerovalo veliko mnoštvo Židova i pogana.14:1 U grčkome: Židova i Grka. 2Ali Židovi koji nisu htjeli poslušati podjare pogane protiv Pavla i Barnabe klevećući ih. 3Apostoli su ipak ondje dugo ostali i hrabro propovijedali o Božjoj milosti. A Bog je potvrđivao njihove riječi dajući da im da čine čudesa i znamenja. 4Žitelji grada podijelili su se. Neki su bili za Židove, drugi za apostole.

5Na koncu pogani i Židovi sa svojim poglavarima navale na njih da ih kamenuju. 6Kad su to doznali, pobjegnu u likaonske gradove Listru i Derbu 7te su ondje navješćivali Radosnu vijest.

Pavao i Barnaba u Listri i Derbi

8U Listri Pavao i Barnaba naiđu na čovjeka hroma od rođenja. Nikada nije hodao. 9Slušao je Pavlovo propovijedanje i Pavao je vidio da vjeruje u iscjeljenje 10pa mu glasno reče: “Ustani!” Čovjek skoči i prohoda.

11Kad je mnoštvo vidjelo što je Pavao učinio, poviče na svojemu likaonskom narječju: “Bogovi u ljudskom obličju sišli su k nama!” 12Zaključili su da je Barnaba grčki bog Zeus, a Pavao Hermes jer je vodio glavnu riječ. 13Iz Zeusova hrama u predgrađu dođe svećenik s bikovima i cvjetnim vijencima te su ih on inarod htjeli žrtvovati apostolima pred gradskim vratima.

14Kad su za to čuli Barnaba i Pavao, razderu svoju odjeću i potrče među narod vičući: 15“Ljudi, što to radite? Mi smo samo smrtnici, jednako kao i vi! Došli smo vam navijestiti Radosnu vijest, da se od tih ispraznosti obratite živomu Bogu koji je stvorio nebo, zemlju, more i sve što je u njima! 16Prije je puštao da svaki narod ide svojim putem, 17ali nikada vas nije ostavljao bez svjedočanstva o sebi. Uvijek je slao dobročinstva s neba: kišu, dobru žetvu, hranu i radost u srca.” 18Ali svejedno su jedva spriječili mnoštvo da im prinese žrtvu.

19Neki Židovi iz Antiohije i Ikonija dođu i podjare svjetinu da kamenuje Pavla. Zatim ga odvuku izvan grada misleći da je mrtav. 20Ali kad su ga okružili vjernici,14:20 U grčkome: učenici. Isto i u 15:23, 36 i 40. Pavao ustane i vrati se u grad. Sutradan ode s Barnabom u Derbu.

Pavao i Barnaba vraćaju se u sirijsku Antiohiju

21Kad su u Derbi navijestili Radosnu vijest i stekli brojne učenike, vrate se u Listru, Ikonij i Antiohiju. 22Ondje su snažili vjernike i ohrabrivali ih da ustraju u vjeri podsjećajući ih da u Božje kraljevstvo treba ući kroz mnoge nevolje. 23Po crkvama su postavljali starješine te su ih, pošto su za njih postili i molili, predavali na brigu Gospodinu u kojega su povjerovali. 24Zatim kroz Pizidiju opet dođu u Pamfiliju. 25U Pergi su opet propovijedali Riječ, a zatim odu u Ataliju.

26Odande na koncu odjedre u sirijsku Antiohiju odakle su i započeli putovanje, povjereni Božjoj milosti za djelo koje su dovršili. 27Kad stignu u Antiohiju, sazovu Crkvu i ispripovijedaju što je Bog sve kroz njih učinio na putu: kako je i poganima otvorio vrata vjere. 28I dugo su ondje ostali s vjernicima.