ሐዋርያት ሥራ 11 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 11:1-30

ጴጥሮስ አሕዛብ ቤት ለምን እንደ ገባ አስረዳ

1ሐዋርያትና በይሁዳ የነበሩት ወንድሞች አሕዛብ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ተቀበሉ ሰሙ። 2ስለዚህ ጴጥሮስ ወደ ኢየሩሳሌም በወጣ ጊዜ፣ ከተገረዙት ወገን የነበሩ አማኞች ነቀፉት፤ 3እንዲህም አሉት፤ “ወዳልተገረዙ ሰዎች ገብተህ ከእነርሱ ጋር በላህ።”

4ጴጥሮስ ግን እንዲህ ሲል ነገሩን በቅደም ተከተል ያስረዳቸው ጀመር፤ 5“በኢዮጴ ከተማ ስጸልይ በተመስጦ ውስጥ እያለሁ ራእይ አየሁ፤ ትልቅ ጨርቅ የሚመስል ነገር፣ በአራት ማእዘን ተይዞ ከሰማይ እኔ ወደ ነበርሁበት ቦታ ሲወርድ አየሁ። 6አተኵሬም ይህን ነገር ስመለከት አራት እግር ያላቸው እንስሳት፣ የዱር አራዊት፣ በምድር የሚሳቡ ፍጥረታትና በሰማይ የሚበርሩ አዕዋፍ አየሁ። 7በዚህ ጊዜ፣ ‘ጴጥሮስ ሆይ፤ ተነሣና ዐርደህ ብላ’ የሚለኝን ድምፅ ሰማሁ።

8“እኔም፣ ‘ጌታ ሆይ፤ ይህማ አይሆንም፤ እኔ ርኩስ ወይም ያልተቀደሰ ነገር ፈጽሞ ወደ አፌ ገብቶ አያውቅም’ አልሁ።

9“ያም ድምፅ ዳግመኛ፣ ‘እግዚአብሔር ንጹሕ ያደረገውን አንተ እንደ ርኩስ አትቍጠረው’ ሲል ከሰማይ ተናገረኝ። 10ይህም ሦስት ጊዜ ተደጋገመ፤ ከዚያ ሁሉም እንደ ገና ወደ ሰማይ ተወሰደ።

11“ልክ በዚያው ሰዓት፣ ሦስት ሰዎች ከቂሳርያ ወደ እኔ ተልከው መጥተው እኔ ባለሁበት ቤት ደጅ ላይ ቆሙ፤ 12መንፈስ ቅዱስም ምንም ሳላወላውል ከእነርሱ ጋር እንድሄድ ነገረኝ። እነዚህም ስድስት ወንድሞች ከእኔ ጋር ሄዱ፤ ወደ ሰውየውም ቤት ገባን። 13እርሱም መልአክ በቤቱ ውስጥ ቆሞ እንደ ታየውና እንዲህ እንዳለው ነገረን፤ ‘ወደ ኢዮጴ ሰው ልከህ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንን አስጠራ፤ 14እርሱም አንተና የቤትህ ሰዎች ሁሉ የምትድኑበትን ቃል ይነግርሃል።’

15“እኔም ገና መናገር ስጀምር፣ መንፈስ ቅዱስ በመጀመሪያ በእኛ ላይ እንደ ወረደ ሁሉ በእነርሱም ላይ ወረደ። 16በዚህ ጊዜ፣ ‘ዮሐንስ በውሃ አጠመቀ፤ እናንተ ግን በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ’ ሲል ጌታ የተናገረው ቃል ትዝ አለኝ። 17እንግዲህ እግዚአብሔር በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስናምን ለእኛ የሰጠንን ስጦታ ለእነርሱም ከሰጣቸው፣ ታዲያ፣ እግዚአብሔርን መቋቋም እችል ዘንድ እኔ ማን ነኝ?”

18ይህን በሰሙ ጊዜም የሚሉትን አጥተው እንዲህ እያሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ፤ “ይህማ ከሆነ አሕዛብም ወደ ሕይወት ይመጡ ዘንድ፣ እግዚአብሔር ንስሓን ሰጥቷቸዋል ማለት ነዋ።”

በአንጾኪያ የነበረችው ቤተ ክርስቲያን

19በእስጢፋኖስ ላይ በተነሣው ስደት ምክንያት የተበተኑት አማኞች ቃሉን ለአይሁድ ብቻ እየተናገሩ እስከ ፊንቄ፣ እስከ ቆጵሮስና እስከ አንጾኪያ ድረስ ዘለቁ። 20ከቆጵሮስና ከቀሬና የመጡት አንዳንዶች ሰዎች ግን ወደ አንጾኪያ ሄደው ለግሪኮችም ጭምር በመንገር የጌታን የኢየሱስን ወንጌል ሰበኩላቸው። 21የጌታም እጅ ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ ቍጥራቸውም እጅግ ብዙ የሆኑ ሰዎች አምነው ወደ ጌታ ተመለሱ።

22ወሬውም በኢየሩሳሌም ከነበረችው ቤተ ክርስቲያን ጆሮ ደረሰ፤ ቤተ ክርስቲያኒቱም በርናባስን ወደ አንጾኪያ ላከችው። 23እርሱም እዚያ ደርሶ እግዚአብሔር በጸጋው የሠራውን ባየ ጊዜ ደስ አለው፤ ሁሉም በፍጹም ልብ በጌታ በመታመን እንዲጸኑ መከራቸው። 24እርሱም መንፈስ ቅዱስንና እምነትን የተሞላ ደግ ሰው ነበር፤ ቍጥሩ ብዙ የሆነ ሕዝብም ወደ ጌታ ተጨመረ።

25ከዚህ በኋላ በርናባስ፣ ሳውልን ለመፈለግ ወደ ጠርሴስ ሄደ፤ 26ባገኘውም ጊዜ ወደ አንጾኪያ አመጣው። ሁለቱም እዚያ ካለችው ቤተ ክርስቲያን ጋር በመሆን አንድ ዓመት ሙሉ እጅግ ብዙ ሕዝብ አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርትም ለመጀመሪያ ጊዜ በአንጾኪያ “ክርስቲያን” ተብለው ተጠሩ።

27በዚህ ጊዜ አንዳንድ ነቢያት ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ። 28ከእነርሱም አንዱ አጋቦስ የተባለው ተነሥቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ እንደሚሆን መንፈስ ቅዱስ አስመልክቶት ተናገረ፤ ይህም በቀላውዴዎስ ቄሳር ዘመን ተፈጸመ። 29ደቀ መዛሙርትም እያንዳንዳቸው ዐቅማቸው በፈቀደ መጠን አዋጥተው በይሁዳ የሚኖሩትን ወንድሞች ለመርዳት ወሰኑ፤ 30ርዳታውንም በበርናባስና በሳውል እጅ ለሽማግሌዎቹ በመላክ፣ ይህንኑ አደረጉ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

מעשי השליחים 11:1-30

1עד מהרה נודע לשליחים ולשאר האחים ביהודה שגם הגויים נושעים על־ידי האמונה במשיח. 2כשחזר פטרוס לירושלים החלו היהודים המשיחיים למתוח עליו ביקורת.

3”אתה ביקרת בביתם של גויים, ואפילו אכלת איתם!“ טענו.

4ואז סיפר להם פטרוס את הסיפור כולו – מראשיתו ועד סופו:

5”יום אחד בשעה שהתפללתי ביפו ראיתי חזיון: סדין גדול, קשור בארבע קצותיו, הורד מן השמים. 6בתוך הסדין היו כל מיני חיות, זוחלים ועופות טרפים. 7לאחר מכן שמעתי קול מן השמים שקרא: ’קום, פטרוס, שחט ואכול!‘ “

8” ’חס וחלילה, אדוני!‘ עניתי. ’מעולם לא אכלתי אוכל בלתי כשר או טמא!‘

9”אולם אותו קול מן השמים חזר ואמר: ’אם אלוהים אומר שמשהו מסוים טהור, סימן שהוא טהור. אתה אל תקרא לו טמא!‘

10”חזיון זה חזר ונשנה שלוש פעמים, ולאחר מכן הועלה הסדין לשמים. 11באותה שעה הגיעו אל הבית שבו התארחתי שלושה אנשים שנשלחו מקיסריה, 12ורוח הקודש אמר לי ללכת איתם ללא היסוס, למרות היותם גויים! ששת האחים האלה הצטרפו אלי, וכעבור יום הגענו לקיסריה – לביתו של האדם ששלח את השלושה. 13הוא סיפר לנו שמלאך ה׳ נגלה אליו וציווה עליו לשלוח אנשים ליפו, כדי למצוא את שמעון פטרוס. 14’הוא יאמר לך ולבני ביתך כיצד תוכל להיוושע!‘ אמר לו המלאך.

15”כשהתחלתי לבשר להם צלח רוח הקודש על הנאספים, בדיוק כפי שצלח עלינו בתחילה. 16ואז נזכרתי בדברי האדון: ’יוחנן הטביל אתכם במים, אולם עוד זמן־מה תיטבלו ברוח הקודש‘. 17ואם אלוהים נתן לגויים האלה אותה המתנה שנתן לנו, כשהאמנו באדון ישוע המשיח, מי אני שאתווכח אתו?“

18דבריו של פטרוס השביעו את רצונם של היהודים המשיחיים, והם החלו להלל ולשבח את האלוהים. ”כן,“ אמרו, ”גם לגויים העניק אלוהים את הזכות לחזור בתשובה ולקבל חיי נצח!“

19המאמינים אשר נמלטו מירושלים, בעת הרדיפה שהחלה לאחר מותו של סטפנוס, הגיעו בינתיים עד צור וצידון, קפריסין ואנטיוכיה. בכל מקום הם הכריזו על הבשורה, אבל רק ליהודים. 20אך מאמינים אחדים, שנסעו מקפריסין וקוריניה לאנטיוכיה, סיפרו גם לכמה יוונים על האדון ישוע. 21האדון ברך את מאמציהם, וגויים רבים האמינו באדון ישוע.

22כששמעו על כך חברי הקהילה בירושלים, שלחו את בר־נבא לאנטיוכיה כדי לעזור למאמינים החדשים. 23כשהגיע בר־נבא לאנטיוכיה וראה את מעשיו הנפלאים של ה׳, הוא נמלא שמחה רבה ועודד את המאמינים לדבוק באדון בכל מחיר. 24בר־נבא היה אדם טוב לב, מלא רוח הקודש ובעל אמונה חזקה. באותה עת נוספו אנשים רבים לקהל המאמינים.

25לאחר מכן נסע בר־נבא לטרסוס כדי לחפש את שאול, 26וכשמצא אותו, חזר עמו לאנטיוכיה. השניים נשארו באנטיוכיה שנה שלמה ולימדו את המאמינים החדשים והרבים (שם, באנטיוכיה, החלו לכנות את תלמידי ישוע המשיח בשם ”משיחיים“).

27באותה תקופה באו לאנטיוכיה נביאים אחדים מירושלים. 28אחד מהם, אגבוס שמו, קם באחת האספות וניבא, בהשראת רוח הקודש, שרעב כבד יבוא על כל האימפריה הרומאית (נבואתו התגשמה בתקופת שלטונו של קלודיוס). 29משום כך החליטו המאמינים באנטיוכיה לשלוח עזרה כספית לאחיהם ביהודה, כל אחד כפי יכולתו. 30לאחר שאספו את התרומות מסרו אותן לבר־נבא ולשאול, כדי שיביאו אותן לזקני הקהילה בירושלים.