ሉቃስ 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 8:1-56

የዘሪው ምሳሌ

8፥4-15 ተጓ ምብ – ማቴ 13፥2-23ማር 4፥1-20

1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት የምሥራች ቃል እየሰበከ በየከተማውና በየመንደሩ ዐለፈ። ዐሥራ ሁለቱም ከእርሱ ጋር ነበሩ፤ 2እንዲሁም ከርኩሳን መናፍስትና ከደዌ የተፈወሱ አንዳንድ ሴቶች አብረውት ነበሩ፤ እነርሱም ሰባት አጋንንት የወጡላት መግደላዊት የተባለችው ማርያም፣ 3የሄሮድስ ቤት ኀላፊ የነበረው የኩዛ ሚስት ዮሐና፣ ሶስና፣ ደግሞም ሌሎች ብዙዎች ነበሩ፤ እነዚህም በግል ንብረታቸው የሚያገለግሉት ነበሩ።

4ብዙ ሕዝብ በአንድነት ተሰብስቦ ሳለ፣ ደግሞም ሰዎች ከተለያዩ ከተሞች ወደ እርሱ በሚጐርፉበት ጊዜ፣ ይህን ምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው፤ 5“አንድ ዐራሽ ዘሩን ሊዘራ ወጣ፤ ሲዘራም፣ አንዳንዱ ዘር መንገድ ዳር ወደቀ፣ በእግርም ተረጋገጠ፤ የሰማይ ወፎችም በሉት። 6አንዳንዱም ዘር በድንጋያማ ቦታ ላይ ወደቀ፤ እንደ በቀለም ርጥበት አልነበረውምና ደረቀ። 7ሌላው ዘር ደግሞ እሾኽ መካከል ወደቀ፤ እሾኹም አብሮት አደገና ዐንቆ አስቀረው። 8ሌላውም ዘር በመልካም መሬት ላይ ወደቀ፤ በበቀለም ጊዜ መቶ ዕጥፍ አፈራ።”

ይህን ብሎ ሲያበቃም ድምፁን ከፍ አድርጎ፣ “ሰሚ ጆሮ ያለው ይስማ” አለ።

9ደቀ መዛሙርቱም የዚህን ምሳሌ ትርጕም ጠየቁት። 10እርሱም እንዲህ አለ፤ “የእግዚአብሔርን መንግሥት ምስጢር ማወቅ ለእናንተ ተሰጥቷል፤ ለሌሎች ግን በምሳሌ እናገራለሁ፤ ይኸውም፣

“ ‘እያዩ ልብ እንዳይሉ፣

እየሰሙም እንዳያስተውሉ ነው።’

11“እንግዲህ የምሳሌው ትርጕም ይህ ነው፤ ዘር የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ነው። 12በመንገድ ዳር የወደቀው ቃሉን የሚሰሙ፣ ነገር ግን አምነው እንዳይድኑ ዲያብሎስ መጥቶ ቃሉን ከልባቸው የሚወስድባቸው ናቸው። 13በድንጋያማ ቦታ ላይ የወደቀውም ቃሉን ሲሰሙ በደስታ የሚቀበሉ ናቸው፤ እነዚህ ለጊዜው ያምናሉ እንጂ ሥር ስለሌላቸው በፈተና ጊዜ ፈጥነው የሚክዱ ናቸው። 14በእሾኽ መካከል የወደቀውም ቃሉን የሚሰሙት ናቸው፤ እነዚህም ውለው ዐድረው በምድራዊ ሕይወት ጭንቀት፣ በባለጠግነትና ተድላ ደስታ ታንቀው በሚገባ አያፈሩም። 15በመልካም መሬት ላይ የወደቀውም ቃሉን ቅንና በጎ በሆነ ልብ ሰምተው የሚጠብቁ፣ ታግሠውም በመጽናት ፍሬ የሚያፈሩ ናቸው።

በመቅረዝ ላይ ያለ መብራት

16“መብራትን አብርቶ ጋን ውስጥ ወይም በዐልጋ ሥር የሚያስቀምጥ ማንም የለም፤ ይልቁንም ወደ ቤት የሚገቡ ብርሃኑን እንዲያዩ በመቅረዝ ላይ ያስቀምጠዋል። 17የማይገለጥ የተሰወረ፣ የማይታወቅ ወደ ብርሃን የማይወጣ፣ የተደበቀ ነገር የለምና። 18እንግዲህ እንዴት እንደምትሰሙ ተጠንቀቁ፤ ላለው ይጨመርለታልና፤ ከሌለው ሁሉ ግን ያው ያለው የሚመስለው እንኳ ይወሰድበታል።”

የኢየሱስ እናትና ወንድሞች

8፥19-21 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥46-50ማር 3፥31-35

19ከዚህ በኋላ የኢየሱስ እናትና ወንድሞቹ እርሱ ወዳለበት መጡ፤ እነርሱም ከሕዝቡ ብዛት የተነሣ ወደ እርሱ ሊቀርቡ አልቻሉም። 20በዚህ ጊዜ፣ “እናትህና ወንድሞችህ ሊያዩህ ፈልገው በውጭ ቆመዋል” የሚል ወሬ ደረሰው።

21እርሱም መልሶ፣ “እናቴና ወንድሞቼስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚያደርጉት ናቸው” አላቸው።

ኢየሱስ ማዕበሉን ጸጥ አደረገ

8፥22-25 ተጓ ምብ – ማቴ 8፥23-27ማር 4፥36-41

8፥22-25 ተጓ ምብ – ማር 6፥47-52ዮሐ 6፥16-21

22ከዕለታቱ በአንድ ቀን፣ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጀልባ ላይ ወጣ፤ ኢየሱስም፤ “ወደ ባሕሩ ማዶ እንሻገር” አላቸው፤ ከዚያም ጕዞ ቀጠሉ። 23እየተጓዙ ሳሉም ኢየሱስ እንቅልፍ ወስዶት ተኛ፤ በዚህ ጊዜ በባሕሩ ላይ ማዕበል ተነሣ፤ ውሃውም ጀልባዋን ዘልቆ ስለ ገባ፣ አደጋ አፋፍ ላይ ደረሱ።

24ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው፣ “ጌታ ሆይ፤ ጌታ ሆይ፤ ማለቃችን እኮ ነው!” እያሉ ቀሰቀሱት።

እርሱም ነቅቶ ነፋሱንና የውሃውን መናወጥ ገሠጸ፤ በዚህ ጊዜ ነፋሱም ነውጡም ተወ፤ ጸጥታም ሆነ። 25እርሱም ደቀ መዛሙርቱን፣ “እምነታችሁ የት አለ?” አላቸው።

እነርሱም በፍርሀትና በመደነቅ፣ “ይህ ነፋስንና ውሃን የሚያዝ፣ እነርሱም የሚታዘዙለት እርሱ ማን ነው?” ተባባሉ።

አጋንንት ያደረበት ሰው መፈወሱ

8፥26-37 ተጓ ምብ – ማቴ 8፥28-34

8፥26-39 ተጓ ምብ – ማር 5፥1-20

26ከዚህ በኋላ ከገሊላ ባሻገር ወዳለው ወደ ጌርጌሴኖን8፥26 አንዳንድ ቅጆች ጋድሬኔስ፣ ሌሎች ቅጆች ደግሞ ጌርጌ ሴኔስ ይላሉ፤ 37 ይመ አገር በጀልባ ተሻገሩ። 27ኢየሱስ ከጀልባዋ ወደ ምድር በወረደ ጊዜ፣ አጋንንት ያደረበት አንድ ሰው ከከተማ ወጥቶ አገኘው፤ ይህ ሰው ለብዙ ጊዜ ልብስ ሳይለብስ፣ በቤትም ሳይኖር የመቃብርን ስፍራ ቤቱ ያደረገ ነበር። 28ኢየሱስንም ባየው ጊዜ እየጮኸ ፊቱ ተደፋ፤ በታላቅ ድምፅም፣ “የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፤ ከእኔ ጋር ምን ጕዳይ አለህ? እንዳታሠቃየኝ እለምንሃለሁ” አለ። 29ርኩሱ8፥29 ወይም ክፉ መንፈስ ይህን ያለው ከሰውየው እንዲወጣ ኢየሱስ አዝዞት ስለ ነበር ነው። ርኩሱ መንፈስ በየጊዜው ስለሚነሣበት ሰውየው በሰንሰለትና በእግር ብረት እየታሰረ ቢጠበቅም፣ የታሰረበትን ሰንሰለት እየበጣጠሰ ያደረበት ጋኔን ወደ በረሓ ይነዳው ነበር።

30ኢየሱስም፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው።

እርሱም ብዙ አጋንንት ገብተውበት ስለ ነበር፣ “ሌጌዎን” አለው። 31አጋንንቱም እንጦርጦስ ግቡ ብሎ እንዳያዝዛቸው አጥብቀው ለመኑት።

32በዚያም አካባቢ በተራራ ወገብ ላይ የብዙ ዐሣማ መንጋ ተሰማርቶ ነበር፤ አጋንንቱም ወደ ዐሣማው መንጋ ግቡ ብሎ እንዲፈቅድላቸው ለመኑት፤ እርሱም ፈቀደላቸው። 33አጋንንቱም ከሰውየው ወጥተው ወደ ዐሣማዎቹ ገቡ፤ የዐሣማውም መንጋ በገደሉ አፋፍ ቍልቍል በመንደርደር ባሕሩ ውስጥ ገብቶ ሰጠመ።

34እረኞቹም የሆነውን ነገር ባዩ ጊዜ፣ ሸሽተው በመሄድ በከተማውና በገጠሩ አወሩ። 35ሕዝቡም የተደረገውን ነገር ለማየት ከያሉበት ወጥተው ወደ ኢየሱስ መጡ። አጋንንት የወጡለትም ሰው ልብስ ለብሶ፣ ወደ ልቦናው ተመልሶ፣ በኢየሱስም እግር ሥር ተቀምጦ ባዩት ጊዜ ፈሩ። 36በአጋንንት የተያዘው ሰው ሲድን ያዩትም፣ እንዴት እንደ ዳነ ለሕዝቡ አወሩላቸው። 37የጌርጌሴኖን አካባቢ ሰዎችም ሁሉ ታላቅ ፍርሀት ስላደረባቸው፣ ከዚያ እንዲሄድላቸው ኢየሱስን ለመኑት፤ እርሱም ወደ ጀልባው ገብቶ ተመልሶ ሄደ።

38አጋንንት የወጡለትም ሰው አብሮት ለመሆን ኢየሱስን ለመነው፤ እርሱ ግን እንዲህ ሲል አሰናበተው፤ 39“ወደ ቤትህ ተመልሰህ፣ እግዚአብሔር ያደረገልህን ታላቅ ነገር ተናገር።” ሰውየውም ኢየሱስ ያደረገለትን ታላቅ ነገር በከተማው ሁሉ በይፋ እየተናገረ ሄደ።

የሞተችው ልጅና የታመመችው ሴት

8፥40-56 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥18-26ማር 5፥22-43

40ሕዝቡ ሁሉ መምጣቱን ይጠባበቁ ስለ ነበር፣ ኢየሱስ በተመለሰ ጊዜ በደስታ ተቀበሉት። 41በዚህ ጊዜ ኢያኢሮስ የተባለ የምኵራብ አለቃ መጥቶ፣ በኢየሱስ እግር ላይ በመውደቅ ወደ ቤቱ እንዲሄድለት ለመነው፤ 42ይህን ልመና ያቀረበው ዕድሜዋ ዐሥራ ሁለት ዓመት የሆነ አንዲት ልጅ ስለ ነበረችው ነው፤ እርሷ በሞት አፋፍ ላይ ነበረች።

ወደዚያው እያመራ ሳለ፣ ሕዝቡ በመጋፋት እጅግ ያጨናንቀው ነበር። 43ዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈስሳት የኖረች አንዲት ሴት ነበረች፤ ያላትን ሁሉ ለባለ መድኀኒቶች ጨርሳ8፥43 አያሌ ቅጆች ያላትን ሁሉ ለባለ መድኀኒቶች ጨርሳ የሚለው የላቸውም። ሊፈውሳትም የቻለ ማንም አልነበረም። 44እርሷም ከበስተ ኋላው ተጠግታ የልብሱን ጫፍ ነካች፤ ይፈስስ የነበረው ደሟም ወዲያው ቆመ።

45ኢየሱስም፣ “የነካኝ ማነው?” አለ።

ሁሉም መንካታቸውን በካዱ ጊዜ ጴጥሮስ፣ “ጌታ ሆይ፤ ሕዝቡ ሁሉ ከብቦህ በግፊያ እያስጨነቀህ ነው” አለው።

46ኢየሱስ ግን፣ “አንድ ሰው ነክቶኛል፤ ኀይል ከእኔ እንደ ወጣ ዐውቃለሁና” አለ።

47ሴትዮዋም ሳትታወቅ መሄድ እንዳልቻለች በተረዳች ጊዜ፣ እየተንቀጠቀጠች መጥታ በፊቱ ተደፋች፤ ለምን እንደ ነካችውና እንዴት ወዲያው እንደ ተፈወሰች በሕዝቡ ሁሉ ፊት ተናገረች። 48እርሱም፣ “ልጄ ሆይ እምነትሽ ፈውሶሻል በሰላም ሂጂ” አላት።

49ኢየሱስ ገና እየተናገረ ሳለ፣ አንድ ሰው ከምኵራብ አለቃው ከኢያኢሮስ ቤት መጥቶ፣ “ልጅህ ሞታለች፤ ከዚህ በኋላ መምህሩን አታድክመው” አለው።

50ኢየሱስም ይህን ሰምቶ ኢያኢሮስን፣ “አትፍራ፣ እመን ብቻ እንጂ፤ ልጅህ ትድናለች” አለው።

51ወደ ኢያኢሮስ ቤት ሲገባም ከጴጥሮስ፣ ከዮሐንስና ከያዕቆብ እንዲሁም ከልጅቱ አባትና እናት በቀር ማንም አብሮት እንዲገባ አልፈቀደም። 52በዚህ ጊዜ ሰዎቹ ሁሉ እያለቀሱላት ዋይ ዋይ ይሉ ነበር። እርሱ ግን፣ “አታልቅሱ፤ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም” አላቸው።

53ሰዎቹም መሞቷን ስላወቁ ሣቁበት። 54እርሱ ግን እጇን ይዞ፣ “ልጄ ሆይ፤ ተነሺ” አላት። 55የልጅቷም መንፈስ ተመለሰ፤ ወዲያውም ተነሥታ ቆመች፤ ኢየሱስም የሚበላ ነገር እንዲሰጧት አዘዛቸው። 56ወላጆቿም ተደነቁ፤ እርሱ ግን የሆነውን ነገር ለማንም እንዳያወሩ አዘዛቸው።

Thai New Contemporary Bible

ลูกา 8:1-56

คำอุปมาเรื่องผู้หว่าน

(มธ.13:2-23; มก.4:1-20)

1หลังจากนั้นพระเยซูเสด็จไปตามเมืองและหมู่บ้านต่างๆ ทรงประกาศข่าวประเสริฐเรื่องอาณาจักรของพระเจ้า สาวกทั้งสิบสองคนอยู่กับพระองค์ 2พร้อมกับพวกผู้หญิงซึ่งทรงรักษาให้หายจากวิญญาณชั่วและโรคต่างๆ ผู้หญิงเหล่านี้ได้แก่ มารีย์ (ที่เรียกว่าชาวมักดาลา) ที่ทรงขับผีออกจากนางเจ็ดตน 3โยอันนาภรรยาของคูซาคนต้นเรือนของเฮโรด สูสันนา และคนอื่นๆ อีกมากมาย ผู้หญิงเหล่านี้ช่วยสนับสนุนพวกเขาด้วยทรัพย์สินของตน

4ขณะผู้คนจำนวนมากมาชุมนุมกันอยู่และประชาชนจากเมืองนั้นเมืองนี้กำลังพากันมาเข้าเฝ้าพระเยซู พระองค์ตรัสคำอุปมานี้ว่า 5“ชาวนาคนหนึ่งออกไปหว่านเมล็ดพืช ขณะที่หว่าน บางเมล็ดก็ตกตามทาง ถูกเหยียบย่ำและนกในอากาศก็มาจิกกินไปหมด 6บางเมล็ดตกบนกรวดหิน เมื่องอกขึ้นมาก็เหี่ยวเฉาเพราะขาดความชุ่มชื้น 7บางเมล็ดก็ตกกลางพงหนาม ถูกหนามงอกขึ้นมาปกคลุม 8แต่ยังมีบางเมล็ดที่ตกบนดินดี งอกขึ้นมาแล้วเกิดผลมากกว่าที่หว่านไว้ร้อยเท่า”

เมื่อพระองค์กล่าวถึงตรงนี้ก็ทรงพูดเสียงดังว่า “ใครมีหูที่จะฟังก็จงฟังเถิด”

9เหล่าสาวกมาทูลถามพระองค์ถึงความหมายของคำอุปมานี้ 10พระองค์ตรัสว่า “ความลับของอาณาจักรของพระเจ้า ทรงโปรดให้พวกท่านรู้ แต่กับคนอื่นนั้นเรากล่าวเป็นคำอุปมาเพื่อว่า

“ ‘แม้ได้ดูพวกเขาก็ไม่เห็น

แม้ได้ฟังพวกเขาก็ไม่เข้าใจ’8:10 อสย.6:9

11“ความหมายของคำอุปมาก็คือ เมล็ดที่หว่านคือพระวจนะของพระเจ้า 12ที่หล่นตามทางคือผู้ที่ได้ยิน แล้วมารก็มาชิงพระวจนะไปจากใจของเขาเพื่อไม่ให้เขาเชื่อและได้รับความรอด 13ที่ตกลงบนหินคือผู้ที่ได้ยิน แล้วรับพระวจนะด้วยความยินดีแต่ไม่หยั่งรากลึก เขาเชื่อเพียงชั่วระยะหนึ่ง แต่เมื่อถูกทดลองก็เลิกราไป 14เมล็ดพืชที่ตกกลางพงหนามคือผู้ที่ได้ยิน แต่ขณะที่เขาดำเนินชีวิตไปตามทางของเขาก็ถูกความพะวักพะวน ทรัพย์สมบัติ และความสนุกบันเทิงในชีวิตกีดขวาง เขาจึงไม่เติบโตเป็นผู้ใหญ่ 15แต่เมล็ดที่ตกบนดินดีนั้นคือผู้ที่จิตใจดีงามสูงส่ง ผู้ได้ยินพระวจนะแล้วรับไว้และเกิดผลด้วยความอดทนบากบั่น

ตะเกียงบนเชิงตะเกียง

16“ไม่มีใครจุดตะเกียงแล้วซ่อนไว้ในถังหรือวางไว้ใต้เตียง แต่ย่อมตั้งไว้บนเชิงตะเกียงเพื่อคนที่เข้ามาเห็นแสงสว่าง 17เพราะไม่มีสักสิ่งที่ซ่อนไว้แล้วจะไม่ถูกเปิดเผย ไม่มีสักสิ่งที่ปิดบังไว้จะไม่มีใครรู้หรือไม่ถูกเปิดโปง 18เหตุฉะนั้นจงเอาใจใส่สิ่งที่เจ้าได้ยินได้ฟังให้ดี ผู้ใดที่มีอยู่แล้วจะได้รับเพิ่มขึ้น ส่วนผู้ที่ไม่มี แม้สิ่งที่เขาคิดว่าเขามีก็จะถูกเอาไปจากเขา”

มารดากับน้องชายของพระเยซู

(มธ.12:46-50; มก.3:31-35)

19ขณะนั้นมารดากับน้องๆ ของพระเยซูมาหาพระองค์ แต่ไม่สามารถเข้าใกล้พระองค์ได้เพราะคนแน่นมาก 20มีบางคนมาทูลพระองค์ว่า “มารดากับน้องชายของท่านยืนอยู่ข้างนอกต้องการจะพบท่าน”

21พระองค์ทรงตอบว่า “มารดาและน้องชายของเราคือบรรดาผู้ที่ได้ยินพระวจนะของพระเจ้าและนำไปปฏิบัติ”

พระเยซูทรงห้ามพายุ

(มธ.8:23-27; มก.4:36-41)

22วันหนึ่งพระเยซูตรัสกับเหล่าสาวกว่า “ให้เราข้ามทะเลสาบไปอีกฟากหนึ่งเถิด” พวกเขาจึงพากันลงเรือไป 23ขณะที่เขาแล่นเรือไปพระเยซูบรรทมหลับ เกิดพายุใหญ่กลางทะเลสาบ น้ำซัดเข้าเรือ และพวกเขาตกอยู่ในอันตรายใหญ่หลวง

24เหล่าสาวกเข้ามาปลุกพระองค์และทูลว่า “พระอาจารย์ พระอาจารย์ เรากำลังจะจมแล้ว!”

พระองค์ทรงลุกขึ้นห้ามลมและคลื่น พายุก็สงบลงและทุกอย่างก็สงบเงียบ 25พระองค์ทรงถามเหล่าสาวกว่า “ความเชื่อของพวกท่านอยู่ที่ไหน?”

พวกเขากลัวและประหลาดใจ ต่างถามกันว่า “นี่คือใครหนอ? แม้แต่ลมและคลื่นก็ยังเชื่อฟังคำสั่งของพระองค์”

การรักษาคนถูกผีสิง

(มธ.8:28-34; มก.5:1-20)

26พวกเขาแล่นเรือมาถึงแดนเกราซา8:26 หรือกาดาราเช่นเดียวกับข้อ 37ซึ่งอยู่คนละฟากกับกาลิลี 27เมื่อพระเยซูทรงขึ้นจากเรือ พระองค์ทรงพบชายคนหนึ่งจากเมืองนั้นซึ่งถูกผีเข้าสิง นานแล้วที่ชายคนนี้ไม่สวมเสื้อผ้าไม่อยู่ในบ้าน แต่อาศัยอยู่ตามอุโมงค์ฝังศพ 28เมื่อเขาเห็นพระเยซูก็ส่งเสียงร้องและซบลงแทบพระบาทแล้วตะโกนสุดเสียงว่า “พระเยซู พระบุตรของพระเจ้าสูงสุด พระองค์ต้องการอะไรจากข้าพระองค์? ขอโปรดอย่าทรมานข้าพระองค์เลย!” 29เพราะพระเยซูได้ตรัสสั่งวิญญาณชั่ว8:29 ภาษากรีกว่าโสโครกให้ออกมาจากชายผู้นี้ ผีได้สิงเขาหลายครั้งแล้ว แม้เอาโซ่ล่ามมือเท้าของเขาและวางยามเฝ้า เขาก็หักโซ่ตรวนเสียและผีขับไสเขาให้ออกไปอยู่ในที่เปลี่ยว

30พระเยซูตรัสถามเขาว่า “เจ้าชื่ออะไร?”

เขาทูลว่า “ชื่อกอง” เพราะมีผีหลายตนสิงอยู่ในตัวเขา 31และพวกมันพร่ำอ้อนวอนพระองค์ไม่ให้ทรงสั่งให้มันกลับไปยังนรกขุมลึก

32แถวนั้นมีสุกรฝูงใหญ่หากินอยู่แถบเนินเขา พวกผีจึงทูลวิงวอนพระเยซูให้ทรงอนุญาตให้พวกมันไปสิงในฝูงสุกรและพระองค์ทรงอนุญาต 33พวกผีจึงออกจากชายคนนั้นเข้าไปสิงในสุกร แล้วสุกรทั้งฝูงก็กระโจนจากหน้าผาลงทะเลสาบจมน้ำตายหมด

34เมื่อบรรดาคนเลี้ยงสุกรเห็นสิ่งที่เกิดขึ้นก็วิ่งเข้าไปเล่าเรื่องนี้ในเมืองและหมู่บ้าน 35ผู้คนพากันออกมาดูว่าเกิดอะไรขึ้น เมื่อพวกเขามาหาพระเยซูก็พบว่าผีได้ออกจากชายคนนั้นไปแล้ว เขานั่งอยู่แทบพระบาทพระเยซูสวมใส่เสื้อผ้าและมีสติดี พวกเขาก็กลัว 36ผู้ที่เห็นเหตุการณ์จึงเล่าให้ผู้คนฟังว่าชายซึ่งถูกผีสิงหายเป็นปกติได้อย่างไร 37ชาวเกราซาทั้งปวงจึงขอร้องพระเยซูให้ทรงไปจากพวกเขาเพราะพวกเขากลัวมาก พระองค์จึงเสด็จลงเรือจากไป

38ชายคนที่ผีได้ออกไปจากเขาแล้วนั้นอ้อนวอนขอไปกับพระองค์ แต่พระเยซูทรงส่งเขากลับไปและตรัสสั่งว่า 39“จงกลับไปบ้านและเล่าให้ใครๆ ฟังว่าพระเจ้าทรงกระทำการเพื่อท่านมากเพียงใด” คนนั้นจึงไปเล่าให้คนทั่วเมืองฟังว่าพระเยซูทรงกระทำการเพื่อเขามากเพียงใด

เด็กผู้หญิงที่เสียชีวิตและหญิงที่ป่วย

(มธ.9:18-26; มก.5:22-43)

40เมื่อพระเยซูทรงข้ามฟากกลับมา ฝูงชนพากันต้อนรับพระองค์เพราะพวกเขากำลังรอคอยพระองค์อยู่ 41แล้วมีชายคนหนึ่งชื่อไยรัสเป็นนายธรรมศาลา มาหมอบลงแทบพระบาทพระเยซูและทูลอ้อนวอนให้พระองค์เสด็จไปที่บ้านของเขา 42เพราะลูกสาวคนเดียวของเขากำลังจะตาย เด็กหญิงนี้อายุราวสิบสองขวบ

ขณะพระเยซูเสด็จไปผู้คนเบียดเสียดพระองค์แน่นขนัด 43ที่นั่นมีหญิงคนหนึ่งตกเลือดเรื้อรังมาสิบสองปี8:43 สำเนาต้นฉบับหลายสำเนาว่าสิบสองปีและนางเสียเงินหาหมอมาหลายคนจนหมดตัวแล้ว แต่ไม่มีใครรักษานางให้หายได้ 44นางมาข้างหลังพระองค์และแตะชายฉลองพระองค์ ทันใดนั้นเลือดก็หยุดไหล

45พระเยซูตรัสถามว่า “ใครแตะต้องเรา?”

คนทั้งปวงต่างก็ปฏิเสธ เปโตรทูลว่า “พระอาจารย์ ผู้คนรุมล้อมเบียดเสียดพระองค์”

46แต่พระเยซูตรัสว่า “มีคนแตะเรา เรารู้ว่าฤทธิ์อำนาจซ่านออกจากตัวเรา”

47ฝ่ายหญิงนั้นเห็นว่าไม่อาจหลบเลี่ยงไปได้ก็กลัวจนตัวสั่นและเข้ามาหมอบลงแทบพระบาท นางกราบทูลพระองค์ต่อหน้าคนทั้งปวงถึงสาเหตุที่แตะต้องพระองค์และที่นางหายโรคทันที 48พระองค์จึงตรัสกับนางว่า “ลูกสาวเอ๋ย ความเชื่อของเจ้าทำให้เจ้าหายโรค จงกลับไปด้วยสันติสุขเถิด”

49พระเยซูตรัสยังไม่ทันขาดคำก็มีคนจากบ้านของไยรัสนายธรรมศาลามาบอกว่า “ลูกสาวของท่านเสียชีวิตแล้ว อย่ารบกวนพระอาจารย์อีกเลย”

50พระเยซูทรงได้ยินก็ตรัสกับไยรัสว่า “อย่ากลัวเลย จงเชื่อเท่านั้นแล้วลูกสาวจะหาย” 51เมื่อมาถึงบ้านของไยรัส พระองค์ไม่ทรงอนุญาตให้ใครติดตามเข้าไปยกเว้นเปโตร ยากอบกับยอห์น และบิดามารดาของเด็ก 52ขณะนั้นคนทั้งปวงกำลังร้องไห้ไว้อาลัยแก่เด็กนั้น พระเยซูตรัสว่า “หยุดร้องไห้เถิด เด็กน้อยยังไม่ตายเพียงแต่หลับอยู่”

53พวกเขาหัวเราะเยาะพระองค์เพราะรู้ว่าเด็กตายแล้ว 54แต่พระเยซูทรงจับมือเด็กน้อยและตรัสว่า “ลูกเอ๋ย ลุกขึ้นเถิด!” 55วิญญาณของเด็กก็กลับมา ทันใดนั้นเด็กหญิงก็ลุกขึ้นยืน แล้วพระเยซูตรัสสั่งให้นำอาหารมาให้เด็กรับประทาน 56บิดามารดาของเด็กต่างประหลาดใจ แต่พระองค์ทรงสั่งพวกเขาไม่ให้บอกเรื่องที่เกิดขึ้นนี้กับใคร