ሉቃስ 4 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 4:1-44

የኢየሱስ መፈተን

4፥1-13 ተጓ ምብ – ማቴ 4፥1-11ማር 1፥1213

1ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ከዮርዳኖስ እንደ ተመለሰ፣ መንፈስ ወደ በረሓ ወሰደው፤ 2በዚያም አርባ ቀን በዲያብሎስ ተፈተነ፤ በእነዚያም ቀናት ምንም ሳይበላ ቈይቶ በመጨረሻ ተራበ።

3ዲያብሎስም፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፣ እስቲ ይህ ድንጋይ እንጀራ እንዲሆን እዘዘው” አለው።

4ኢየሱስም፣ “ ‘ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም’ ተብሎ ተጽፏል” ብሎ መለሰለት።

5ከዚያም ዲያብሎስ ወደ አንድ ከፍታ ቦታ አውጥቶት የዓለምን መንግሥታት ሁሉ በቅጽበት አሳየው፤ 6እንዲህም አለው፤ “የእነዚህ መንግሥታት ሥልጣንና ክብር ሁሉ ለእኔ ተሰጥቷል፤ እኔም ለምወድደው ስለምሰጥ፣ ለአንተ እሰጥሃለሁ፤ 7ስለዚህ ብትሰግድልኝ ይህ ሁሉ የአንተ ይሆናል።”

8ኢየሱስም መልሶ፣ “ ‘ለጌታ ለአምላክህ ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ’ ተብሎ ተጽፏል” አለው።

9ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም ወስዶ በቤተ መቅደስ ጕልላት ላይ አቆመውና እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፣ እስቲ ራስህን ከዚህ ወደ ታች ወርውር፤ 10ምክንያቱም እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፤

“ ‘ይጠብቁህ ዘንድ፣

መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋል፤

11እግርህም ከድንጋይ ጋር እንዳይጋጭ፣

በእጆቻቸው ወደ ላይ አንሥተው ይይዙሃል።’ ”

12ኢየሱስም፣ “ ‘ጌታ አምላክህን አትፈታተነው’ ተብሏል” ብሎ መለሰለት።

13ዲያብሎስም ፈተናውን ሁሉ ከጨረሰ በኋላ፣ ሌላ አመቺ ጊዜ እስኪያገኝ ድረስ ከእርሱ ተለየ።

ኢየሱስ በናዝሬት ተቀባይነት ማጣቱ

14ኢየሱስም በመንፈስ ኀይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ዝናውም በአካባቢው ባለው አገር ሁሉ ወጣ። 15እርሱም በምኵራባቸው ያስተምር ነበር፤ ሰውም ሁሉ ያመሰግነው ነበር።

16ከዚያም ወዳደገበት ከተማ ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ወደ ምኵራብ ገባ፤ ሊያነብብም ተነሥቶ ቆመ። 17የነቢዩ ኢሳይያስ ጥቅልል መጽሐፍም ተሰጠው፤ ጥቅልሉንም መጽሐፍ በተረተረው ጊዜ እንዲህ ተብሎ የተጻፈበትን ክፍል አገኘ፤

18“የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፤

ለድኾች ወንጌልን እንድሰብክ፣

እርሱ ቀብቶኛልና፤

ለታሰሩት መፈታትን፣

ለታወሩትም ማየትን እንዳውጅ፣

የተጨቈኑትን ነጻ እንዳወጣ፣

19የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እንዳውጅ ልኮኛል።”

20ከዚያም መጽሐፉን ጠቅልሎ ለአገልጋዩ መልሶ ሰጠውና ተቀመጠ፤ በምኵራብ የነበሩትም ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር። 21እርሱም፣ “ይህ በጆሯችሁ የሰማችሁት የመጽሐፍ ቃል ዛሬ ተፈጸመ” ይላቸው ጀመር።

22ሁሉም ስለ እርሱ በበጎ ይናገሩ ነበር፤ ደግሞም ከአንደበቱ በሚወጣ የጸጋ ቃል እየተገረሙ፣ “ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን?” ይሉ ነበር።

23እርሱም፣ “ ‘ባለ መድኀኒት ሆይ፤ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም ስታደርግ የሰማነውን ነገር እዚህ በራስህ ከተማ ደግሞ አድርግ’ የሚለውን ምሳሌ እንደምትጠቅሱብኝ ጥርጥር የለውም” አላቸው።

24ደግሞም እንዲህ አላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ፤ ነቢይ በገዛ አገሩ አይከበርም። 25ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ፤ ሰማይ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ ተዘግቶ ጽኑ ራብ በምድሪቱ ሁሉ ላይ በነበረበት በኤልያስ ዘመን፣ ብዙ መበለቶች በእስራኤል ነበሩ፤ 26ኤልያስ ከእነዚህ መካከል ወደ አንዷም አልተላከም፤ ነገር ግን በሲዶና አገር በሰራፕታ ወደ ነበረችው መበለት ተላከ። 27በነቢዩ በኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች4፥27 የግሪኩ ቃል የግድ ከለምጽ ጋር ብቻ የተያያዘ ሳይሆን፣ የተለያየ የቈዳ በሽታዎች ለመግለጽ ጥቅም ላይ ይውላል። ነበሩ፤ ነገር ግን ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነዚያ መካከል ማንም አልነጻም።”

28በምኵራብ የነበሩ ሰዎች ሁሉ ይህን በሰሙ ጊዜ በቍጣ ገነፈሉ፤ 29ከተቀመጡበትም ተነሥተው ከከተማው አስወጡት፤ ቍልቍል ሊጥሉትም ከተማቸው ወደ ተሠራችበት ኰረብታ አፋፍ ወሰዱት፤ 30እርሱ ግን በመካከላቸው ሰንጥቆ ሄደ።

ኢየሱስ ርኩስ መንፈስ አስወጣ

4፥31-37 ተጓ ምብ – ማር 1፥21-28

31ከዚያም በገሊላ አውራጃ ወደምትገኘው ከተማ ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፤ በዚያም በሰንበት ዕለት ሕዝቡን ያስተምር ጀመር፤ 32የሚናገረው በሥልጣን ስለ ነበር በትምህርቱ ተደነቁ።

33በምኵራብም የርኩስ ጋኔን መንፈስ ያደረበት ሰው ነበረ፤ እርሱም ከፍ ባለ ድምፅ ጮኾ፣ 34“ወዮ! የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፤ ምን የሚያገናኘን ጕዳይ አለ? የመጣኸው ልታጠፋን ነውን? አንተ ማን እንደ ሆንህ ዐውቃለሁ፤ አንተ የእግዚአብሔር ቅዱስ ነህ!” አለው።

35ኢየሱስም፣ “ጸጥ ብለህ ከዚህ ሰው ውጣ!” ብሎ ገሠጸው። ጋኔኑም ሰውየውን በሕዝቡ ሁሉ ፊት ጣለውና ምንም ጕዳት ሳያደርስበት ለቅቆት ወጣ።

36ሰዎቹም ሁሉ ተገረሙ፤ እርስ በእርሳቸውም፣ “ለመሆኑ ይህ ትምህርት ምንድን ነው? በሥልጣንና በኀይል ርኩሳን መናፍስትን ያዝዛል፤ እነርሱም እኮ ይወጣሉ” ተባባሉ። 37የእርሱም ዝና በአካባቢው ወዳለው ስፍራ ሁሉ ወጣ።

ኢየሱስ ብዙ በሽተኞችን ፈወሰ

4፥38-41 ተጓ ምብ – ማቴ 8፥14-17

4፥38-43 ተጓ ምብ – ማር 1፥29-38

38ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ከምኵራብ ወጥቶ ወደ ስምዖን ቤት ገባ። የስምዖንም ዐማት ኀይለኛ ትኵሳት ይዟት ታማ ነበር፤ እንዲፈውሳትም ስለ እርሷ ለመኑት። 39እርሱም ወደ ተኛችበት ጠጋ ብሎ በማጐንበስ ትኵሳቱን ገሠጸው፤ ትኵሳቱም ለቀቃትና ወዲያው ተነሥታ አስተናገደቻቸው።

40ፀሓይ መጥለቂያ ላይም፣ የተለያየ ሕመም ያደረባቸውን ሰዎች ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤ እርሱም በእያንዳንዳቸው ላይ እጁን ጭኖ ፈወሳቸው። 41አጋንንትም ደግሞ፣ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ!” እያሉና እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ወጡ። እርሱ ግን ገሠጻቸው፤ ክርስቶስ4፥41 ወይም መሲሕ መሆኑንም ያውቁ ስለ ነበር፣ አንዳች እንዲናገሩ አልፈቀደላቸውም።

42ሲነጋም ኢየሱስ ወደ አንድ ገለልተኛ ስፍራ ሄደ፤ ሕዝቡም ይፈልጉት ነበር፤ እርሱ ወዳለበትም ቦታ መጡ፤ ከእነርሱ ተለይቶ እንዳይሄድ ሊከለክሉት ሞከሩ። 43እርሱ ግን፣ “ወደ ሌሎቹም ከተሞች ሄጄ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል መስበክ ይገባኛል፤ የተላክሁት ለዚሁ ዐላማ ነውና” አላቸው። 44በይሁዳ ምኵራቦችም መስበኩን ቀጠለ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי לוקס 4:1-44

1ישוע חזר מן הירדן מלא רוח הקודש, והרוח הובילה אותו אל המדבר – 2שם ניסה אותו השטן במשך ארבעים יום. במשך כל אותו זמן לא אכל ישוע דבר, ובתום ימי הניסיון היה רעב מאוד.

3”אם אתה באמת בן־אלוהים,“ אמר לו השטן, ”צווה על האבן הזאת להפוך ללחם!“

4אולם ישוע השיב: ”כתוב:4‏.4 ד 4 דברים ח 3 ’לא על הלחם לבדו יחיה האדם, (כי על כל מוצא פי ה)‘. “

5לאחר מכן העלה השטן את ישוע, בחזיון רגעי הראה לו את כל המדינות המפוארות שבעולם ואמר: 6‏-7”אני אתן לך את כל הממלכות המפוארות האלה ואת כבודן – כי לי נמסר השלטון ורשאי אני לתת אותו למי שארצה – אבל בתנאי אחד: עליך לכרוע ברך ולהשתחוות לפני.“

8אולם ישוע השיב לו: ”אך כתוב: ’לה׳ אלוהיך תשתחווה, ואותו לבדו תעבוד‘. “

9השטן לקח את ישוע לירושלים, העלהו על גג בית־המקדש ואמר: ”אם אתה באמת בן־אלוהים, קפוץ למטה! 10הרי כתוב בתנ״ך:4‏.10 ד 10 תהלים צא 12‏-11 ’כי מלאכיו יצווה לך לשמרך… 11על כפיים ישאונך פן תיגוף באבן רגלך‘. “

12”אולם כתוב: ’לא תנסה את ה׳ אלוהיך‘, “ השיב לו ישוע.

13כאשר סיים השטן לנסות את ישוע עזב אותו לנפשו עד לעת מועד.

14לאחר מכן חזר ישוע לגליל כשהוא מלא בכוח רוח הקודש, ועד מהרה התפרסם בכל האזור. 15ישוע לימד את העם בבתי־הכנסת וכולם הללו ושיבחו אותו. 16ישוע בא אל נצרת – העיר שבה בילה את ילדותו – ובשבת הלך כמנהגו לבית־הכנסת. כשקם על רגליו כדי לקרוא את ההפטרה, 17הגישו לו את ספר ישעיהו. ישוע פתח את המגילה וקרא בקול:4‏.17 ד 17 ישעיהו סא 1‏-2

18”רוח ה׳ עלי, יען משח ה׳ אותי לבשר ענוים;

שלחני לחבש לנשברי לב,

לקרוא לשבוים דרור ולאסורים – פְּקַח־קוֹחַ;

19לקרוא שנת רצון לה׳.“

20ישוע גלל את המגילה, החזירה לחזן וישב במקומו. כל באי בית־הכנסת נעצו בו את עיניהם בציפייה, 21וישוע הוסיף: ”היום התקיימו דברי הפסוקים האלה בקרבכם!“

22כולם הקשיבו לדבריו והתפלאו על דברי החן והחוכמה שיצאו מפיו. ”איך ייתכן הדבר?“ שאלו איש את רעהו. ”האין זה בנו של יוסף?“ 23ישוע ענה להם: ”ודאי תאמרו לי: ’רופא, רפא תחילה את עצמך!‘ או במילים אחרות: ’מדוע אינך מחולל כאן, בעיר מולדתך, את הניסים והנפלאות שחוללת בכפר־נחום?‘ 24אני אומר לכם: אין נביא בעירו! את הנביא מכבדים בכל מקום חוץ מאשר בביתו ובין בני־עמו.

25”בימי אליהו הנביא לא ירד גשם במשך שלוש וחצי שנים, והבצורת גרמה לרעב גדול בכל הארץ. למרות שהיו בישראל אלמנות רבות שרעבו ללחם, 26לא שלח אלוהים את אליהו אל אף אחת מהן! אלוהים שלח את אליהו רק אל אלמנה לא יהודיה בעיירה צרפת שבצידון. 27או קחו לדוגמה את אלישע; אף כי בימי אלישע הנביא היו מצורעים רבים בישראל, הוא לא ריפא איש מהם, אלא דווקא את נעמן הארמי.“

28דברי ישוע עוררו את זעמם. 29הם קפצו מכיסאותיהם ודחפו אותו אל מחוץ לעיר, אל פסגת ההר שעליו נבנתה נצרת, במטרה להשליכו במדרון. 30אולם ישוע התחמק מהם והלך לדרכו. 31לאחר מכן הלך ישוע לכפר־נחום שבגליל, ומדי שבת לימד בבית־הכנסת. 32גם כאן נדהמו השומעים, כי ישוע דיבר בסמכות בלתי רגילה.

33פעם כשלימד ישוע בבית־הכנסת צעק לפתע איש אחד אחוז רוח שד טמא: 34”מדוע אתה מטריד אותנו, ישוע מנצרת, האם באת להשמיד את השדים? אני מכיר אותך; אתה בנו הקדוש של אלוהים!“

35ישוע נזף בשד וציווה עליו: ”שתוק וצא החוצה!“ השד השליך את האיש על הרצפה לעיני כולם, ויצא ממנו בלי לפגוע בו שוב.

36כולם נדהמו ושאלו איש את רעהו במבוכה: ”מה המיוחד בדברי האיש הזה עד כי אפילו שדים מצייתים לו?“ 37עד מהרה התפרסם סיפור המעשה בכל האזור.

38לאחר שעזב ישוע את בית־הכנסת, הלך לביתו של שמעון וראה את חמותו של שמעון קודחת מחום. ”אנא, רפא אותה“, התחננו לפניו כולם.

39ישוע עמד ליד מיטתה וגער בקדחת. מיד ירד החום, והיא קמה ממיטתה והכינה להם אוכל.

40עם שקיעת השמש הביאו תושבי הסביבה אל ישוע חברים ובני משפחה שחלו במחלות שונות. ישוע הניח את ידיו עליהם וריפא אותם. 41ישוע גם גירש שדים מאנשים רבים, ובצאתם נהגו השדים לקרוא בקול: ”אתה הוא בן־האלוהים!“ אולם ישוע השתיק אותם, בגלל שהם ידעו שהוא המשיח.

42למחרת, השכם בבוקר, הלך ישוע למקום שומם כדי להתבודד. המוני העם חיפשו אותו בכל מקום, וכשמצאו אותו התחננו לפניו: ”אנא, אל תעזוב אותנו; הישאר איתנו בכפר־נחום.“

43אולם ישוע השיב להם: ”עלי לבשר את דבר מלכות האלוהים גם בערים אחרות, כי זוהי מטרת שליחותי.“ 44וישוע המשיך ללמד בבתי־הכנסת השונים שבאזור יהודה.