ሉቃስ 24 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 24:1-53

የኢየሱስ ትንሣኤ

24፥1-10 ተጓ ምብ – ማቴ 28፥1-8ማር 16፥1-8ዮሐ 20፥1-8

1በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ሴቶቹ ያዘጋጁትን ሽቱ ይዘው እጅግ ማለዳ ሳለ ወደ መቃብሩ ሄዱ። 2ድንጋዩም ከመቃብሩ ደጃፍ ተንከባልሎ አገኙት፤ 3ወደ ውስጥ ዘልቀው በገቡ ጊዜ ግን የጌታ ኢየሱስን ሥጋ አላገኙም። 4በሁኔታው ግራ ተጋብተው ሳሉ፣ እነሆ፤ እጅግ የሚያንጸባርቅ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች ድንገት አጠገባቸው ቆሙ። 5ሴቶቹም ከመፍራታቸው የተነሣ ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፣ ሰዎቹ እንዲህ አሏቸው፤ “ሕያው የሆነውን እርሱን ለምን ከሙታን መካከል ትፈልጋላችሁ? 6እርሱ ተነሥቷል! እዚህ የለም፤ ደግሞም በገሊላ በነበረ ጊዜ ምን እንዳላችሁ አስታውሱ፤ 7‘የሰው ልጅ በኀጢአተኞች እጅ ዐልፎ ሊሰጥ፣ ሊሰቀልና በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ይገባል’ ብሎ ነበርና።” 8ሴቶቹም በዚህ ጊዜ ቃሉን አስታወሱ።

9ሴቶቹ ከመቃብሩ ስፍራ ተመልሰው ይህን ሁሉ ነገር ለዐሥራ አንዱና ለተቀሩት ሁሉ ነገሯቸው። 10ይህን ለሐዋርያት የነገሯቸውም፣ መግደላዊት ማርያም፣ ዮሐና፣ የያዕቆብ እናት ማርያምና ከእነርሱ ጋር የነበሩት ሌሎች ሴቶች ነበሩ። 11እነርሱ ግን ሴቶቹ የተናገሩት ቃል መቀባዠር ስለ መሰላቸው አላመኗቸውም። 12ጴጥሮስ ግን ተነሥቶ ወደ መቃብሩ ሮጠ፤ እዚያ ደርሶም ጐንበስ ብሎ ወደ ውስጥ ሲመለከት፣ በፍታው እንዳለ ለብቻው ተቀምጦ አየ፤ በሆነውም ነገር እየተገረመ ወደ ቤቱ ተመለሰ።

በኤማሁስ መንገድ ላይ

13በዚሁ ቀን ከደቀ መዛሙርት ሁለቱ፣ ከኢየሩሳሌም ዐሥራ አንድ ኪሎ ሜትር24፥13 ግሪኩ ስድሳ ምዕራፍ ይላል። ያህል ወደሚርቅ፣ ኤማሁስ ወደሚባል መንደር ይሄዱ ነበር፤ 14እነርሱም ስለ ሆነው ነገር ሁሉ እርስ በርስ ይነጋገሩ ነበር። 15እየተነጋገሩና እየተወያዩ ሳሉም ኢየሱስ ራሱ ቀርቦ ከእነርሱ ጋር ይሄድ ጀመር፤ 16ነገር ግን እንዳያውቁት ዐይናቸው ተይዞ ነበር።

17እርሱም፣ “እየሄዳችሁ፣ መንገድ ላይ እርስ በርስ እንዲህ የምትወያዩት ምንድን ነው?” አላቸው።

እነርሱም በሐዘን ክው ብለው ቆሙ። 18ከእነርሱም አንዱ፣ ቀለዮጳ የተባለው፣ “በእነዚህ ቀናት እዚህ በኢየሩሳሌም የሆነውን ነገር የማታውቅ፣ አንተ ብቻ ለአገሩ እንግዳ ነህን?” ሲል መለሰለት።

19እርሱም፣ “የሆነው ነገር ምንድን ነው?” አላቸው።

እነርሱም እንዲህ አሉት፤ “በእግዚአብሔርና በሰው ሁሉ ፊት በተግባርና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ኢየሱስ ነው፤ 20እርሱን የካህናት አለቆችና ገዦቻችን ለሞት ፍርድ አሳልፈው ሰጡት፤ ሰቀሉትም። 21እኛ ግን እስራኤልን ይቤዣል ብለን ተስፋ ያደረግነው እርሱን ነበር፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ፣ ይህ ከሆነ ዛሬ ሦስተኛው ቀን ነው። 22ደግሞም ከእኛው መካከል አንዳንድ ሴቶች አስገረሙን፤ እነርሱም ማልደው ወደ መቃብሩ ሄደው ነበር፤ 23ሥጋውንም ባጡ ጊዜ መጥተው እርሱ በሕይወት እንዳለ የነገሯቸውን መላእክት በራእይ እንዳዩ አወሩልን። 24ከእኛም መካከል አንዳንዶች ወደ መቃብሩ ሄደው፣ ልክ ሴቶቹ እንዳሉት ሆኖ አገኙት፤ እርሱን ግን አላዩትም።”

25እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “እናንተ የማታስተውሉ ሰዎች፣ ልባችሁም ነቢያት የተናገሩትን ሁሉ ከማመን የዘገየ፣ 26ክርስቶስ24፥26 ወይም መሲሕ እንዲሁም 46 ይመ ይህን መከራ መቀበልና ወደ ክብሩም መግባት አይገባውምን?” 27ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እርሱ የተጻፈውን አስረዳቸው።

28ወደሚሄዱበትም መንደር በተቃረቡ ጊዜ፣ ኢየሱስ ዐልፎ የሚሄድ መሰለ። 29እነርሱ ግን፣ “ምሽት እየተቃረበ፣ ቀኑም እየተገባደደ ስለሆነ ከእኛ ጋር ዕደር” ብለው አጥብቀው ለመኑት፤ ስለዚህ ከእነርሱ ጋር ለማደር ገባ።

30አብሯቸውም በማእድ በተቀመጠ ጊዜ፣ እንጀራውን አንሥቶ ባረከ፤ ቈርሶም ሰጣቸው። 31በዚህ ጊዜ ዐይናቸው ተከፈተ፤ ዐወቁትም፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ። 32እነርሱም፣ “በመንገድ ሳለን፣ እያነጋገረን ቅዱሳት መጻሕፍትንም ገልጦ ሲያስረዳን፣ ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን?” ተባባሉ።

33በዚያኑም ሰዓት ተነሥተው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ ዐሥራ አንዱና ከእነርሱ ጋር የነበሩትም በዚያ በአንድነት ተሰብስበው አገኟቸው፤ 34“እነርሱም ጌታ በርግጥ ተነሥቷል! ለስምዖንም ታይቷል” ይባባሉ ነበር። 35ሁለቱ ደቀ መዛሙርትም በመንገድ ላይ የሆነውንና ኢየሱስ እንጀራውን በቈረሰ ጊዜ እንዴት እንዳወቁት ተረኩላቸው።

ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርት ተገለጠ

36ይህን እየተነጋገሩ ሳሉ፣ ኢየሱስ ራሱ በመካከላቸው ቆሞ፣ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው።

37እነርሱ ግን ደንግጠው በፍርሀት ተዋጡ፤ መንፈስም ያዩ መሰላቸው። 38እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “ለምን ትጨነቃላችሁ? ለምንስ ጥርጣሬ በልባችሁ ይገባል? 39እጆቼንና እግሮቼን ተመልከቱ፤ እኔው ራሴ ነኝ። ደግሞም ንኩኝና እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት መንፈስ ሥጋና ዐጥንት የለውምና።”

40ይህንም ብሎ እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው። 41እነርሱም ከመደሰትና ከመገረም የተነሣ ገና ሳያምኑ፣ “በዚያ ቦታ አንዳች የሚበላ ነገር አላችሁን?” አላቸው። 42እነርሱም ከተጠበሰ ዓሣ አንድ ቍራሽ ሰጡት፤ 43እርሱም ተቀብሎ በፊታቸው በላ።

44እርሱም፣ “ከእናንተ ጋር በነበርሁበት ጊዜ፣ ‘በሙሴ ሕግ፣ በነቢያትና በመዝሙር መጻሕፍት ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል’ ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው” አላቸው።

45በዚህ ጊዜ ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዲያስተውሉ አእምሯቸውን ከፈተላቸው፤ 46እንዲህም አላቸው፤ “ ‘እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፤ ክርስቶስ መከራን ይቀበላል፤ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፤ 47ከኢየሩሳሌም ጀምሮ ለሕዝቦች ሁሉ ንስሓና የኀጢአት ስርየት በስሙ ይሰበካል፤’ 48እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ። 49እኔም አባቴ የሰጠውን ተስፋ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኀይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቈዩ።”

የኢየሱስ ዕርገት

50ከዚህ በኋላ እስከ ቢታንያ ይዟቸው ወጣ፤ እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው። 51እየባረካቸውም ሳለ፣ ከእነርሱ ተለይቶ ወደ ሰማይ ዐረገ። 52እነርሱም ሰገዱለት፤ በታላቅ ደስታም ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ 53እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ ዘወትር በቤተ መቅደስ ነበሩ።

New International Reader’s Version

Luke 24:1-53

Jesus Rises From the Dead

1It was very early in the morning on the first day of the week. The women took the spices they had prepared. Then they went to the tomb. 2They found the stone rolled away from it. 3When they entered the tomb, they did not find the body of the Lord Jesus. 4They were wondering about this. Suddenly two men in clothes as bright as lightning stood beside them. 5The women were terrified. They bowed down with their faces to the ground. Then the men said to them, “Why do you look for the living among the dead? 6Jesus is not here! He has risen! Remember how he told you he would rise. It was while he was still with you in Galilee. 7He said, ‘The Son of Man must be handed over to sinful people. He must be nailed to a cross. On the third day he will rise from the dead.’ ” 8Then the women remembered Jesus’ words.

9They came back from the tomb. They told all these things to the 11 apostles and to all the others. 10Mary Magdalene, Joanna, Mary the mother of James, and the others with them were the ones who told the apostles. 11But the apostles did not believe the women. Their words didn’t make any sense to them. 12But Peter got up and ran to the tomb. He bent over and saw the strips of linen lying by themselves. Then he went away, wondering what had happened.

On the Road to Emmaus

13That same day two of Jesus’ followers were going to a village called Emmaus. It was about seven miles from Jerusalem. 14They were talking with each other about everything that had happened. 15As they talked about those things, Jesus himself came up and walked along with them. 16But God kept them from recognizing him.

17Jesus asked them, “What are you talking about as you walk along?”

They stood still, and their faces were sad. 18One of them was named Cleopas. He said to Jesus, “Are you the only person visiting Jerusalem who doesn’t know? Don’t you know about the things that have happened there in the last few days?”

19“What things?” Jesus asked.

“About Jesus of Nazareth,” they replied. “He was a prophet. He was powerful in what he said and did in the sight of God and all the people. 20The chief priests and our rulers handed Jesus over to be sentenced to death. They nailed him to a cross. 21But we had hoped that he was the one who was going to set Israel free. Also, it is the third day since all this happened. 22Some of our women amazed us too. Early this morning they went to the tomb. 23But they didn’t find his body. So they came and told us what they had seen. They saw angels, who said Jesus was alive. 24Then some of our friends went to the tomb. They saw it was empty, just as the women had said. They didn’t see Jesus’ body there.”

25Jesus said to them, “How foolish you are! How long it takes you to believe all that the prophets said! 26Didn’t the Messiah have to suffer these things and then receive his glory?” 27Jesus explained to them what was said about himself in all the Scriptures. He began with Moses and all the Prophets.

28They approached the village where they were going. Jesus kept walking as if he were going farther. 29But they tried hard to keep him from leaving. They said, “Stay with us. It is nearly evening. The day is almost over.” So he went in to stay with them.

30He joined them at the table. Then he took bread and gave thanks. He broke it and began to give it to them. 31Their eyes were opened, and they recognized him. But then he disappeared from their sight. 32They said to each other, “He explained to us what the Scriptures meant. Weren’t we excited as he talked with us on the road?”

33They got up and returned at once to Jerusalem. There they found the 11 disciples and those with them. They were all gathered together. 34They were saying, “It’s true! The Lord has risen! He has appeared to Simon!” 35Then the two of them told what had happened to them on the way. They told how they had recognized Jesus when he broke the bread.

Jesus Appears to the Disciples

36The disciples were still talking about this when Jesus himself suddenly stood among them. He said, “May you have peace!”

37They were surprised and terrified. They thought they were seeing a ghost. 38Jesus said to them, “Why are you troubled? Why do you have doubts in your minds? 39Look at my hands and my feet. It’s really me! Touch me and see. A ghost does not have a body or bones. But you can see that I do.”

40After he said that, he showed them his hands and feet. 41But they still did not believe it. They were amazed and filled with joy. So Jesus asked them, “Do you have anything here to eat?” 42They gave him a piece of cooked fish. 43He took it and ate it in front of them.

44Jesus said to them, “This is what I told you while I was still with you. Everything written about me in the Law of Moses, the Prophets and the Psalms must come true.”

45Then he opened their minds so they could understand the Scriptures. 46He told them, “This is what is written. The Messiah will suffer. He will rise from the dead on the third day. 47His followers will preach in his name. They will tell others to turn away from their sins and be forgiven. People from every nation will hear it, beginning at Jerusalem. 48You have seen these things with your own eyes. 49I am going to send you what my Father has promised. But for now, stay in the city. Stay there until you have received power from heaven.”

Jesus Is Taken Up Into Heaven

50Jesus led his disciples out to the area near Bethany. Then he lifted up his hands and blessed them. 51While he was blessing them, he left them. He was taken up into heaven. 52Then they worshiped him. With great joy, they returned to Jerusalem. 53Every day they went to the temple, praising God.