ሉቃስ 2 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 2:1-52

የኢየሱስ መወለድ

1በዚያን ዘመን፣ የዓለሙ ሁሉ ሕዝብ እንዲቈጠርና እንዲመዘገብ ከአውግስጦስ ቄሳር ትእዛዝ ወጣ። 2ይህም ቄሬኔዎስ የሶርያ ገዥ በነበረበት ጊዜ የተደረገ የመጀመሪያው የሕዝብ ቈጠራ ነበር። 3ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው ለመመዝገብ ወደየራሱ ከተማ ሄደ።

4ዮሴፍም ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ፣ በገሊላ አውራጃ ከምትገኘው ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ የዳዊት ከተማ ወደ ሆነችው፣ ቤተ ልሔም ወደምትባል ከተማ ወደ ይሁዳ ወጣ። 5ወደዚያም ለመመዝገብ የተጓዘው፣ የመውለጃ ጊዜዋ ከተቃረበው ከዕጮኛው ከማርያም ጋር ነበር። 6በዚያም እንዳሉ የምትወልድበት ጊዜ ደረሰ፤ 7የበኵር ልጇ የሆነውን ወንድ ልጅ ወለደች፤ በጨርቅም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማረፊያ ቦታ ስላላገኙ በግርግም አስተኛችው።

እረኞችና መላእክት

8በዚያው አገር በሌሊት መንጋቸውን ሲጠብቁ በሜዳ የሚያድሩ እረኞች ነበሩ። 9የጌታም መልአክ ድንገት መጥቶ በአጠገባቸው ቆመ፤ የጌታም ክብር በዙሪያቸው አበራ፤ ታላቅም ፍርሀት ያዛቸው። 10መልአኩ ግን እንዲህ አላቸው፤ “አትፍሩ፤ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች አምጥቼላችኋለሁና። 11ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋልና፤ እርሱም ጌታ ክርስቶስ2፥11 ወይም መሲሕ፤ ክርስቶስ በግሪክ፣ መሲሕ በዕብራይስጥ፤ የሁለቱም ቃላት ትርጕም የተቀባው ማለት ነው፤ እንዲሁም 26 ይመ ነው። 12ይህ ምልክት ይሁናችሁ፤ ሕፃን ልጅ በጨርቅ ተጠቅልሎ በግርግም ተኝቶ ታገኛላችሁ።”

13ድንገትም ብዙ የሰማይ ሰራዊት ከመልአኩ ጋር ታዩ፤ እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ፣ እንዲህ አሉ፤

14“ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም፣ ሰላምም እርሱ

ለሚወድዳቸው ሰዎች በምድር ይሁን!”

15መላእክቱ ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ ከወጡ በኋላ እረኞቹ፣ “ጌታ የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንድናይ ወደ ቤተ ልሔም እንሂድ” ተባባሉ።

16እነርሱም ፈጥነው ሄዱ፤ ማርያምንና ዮሴፍን፣ ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ። 17ካዩም በኋላ፣ ስለ ሕፃኑ የተነገራቸውን ገልጠው አወሩ። 18ይህንም የሰሙ ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር ተደነቁ፤ 19ማርያም ግን ይህን ሁሉ በልቧ ይዛ ታሰላስል ነበር። 20እረኞቹም ሁሉም ነገር እንደ ተነገራቸው ሆኖ በማግኘታቸው፣ ስለ ሰሙትና ስላዩት ሁሉ እግዚአብሔርን እያከበሩና እያመሰገኑ ተመለሱ።

ሕፃኑን ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት

21ስምንት ቀን ሆኖት የመገረዣ ጊዜው ሲደርስ፣ ከመፀነሱ በፊት መልአኩ ባወጣለት ስም ኢየሱስ ተባለ።

22በሙሴ ሕግ መሠረት የመንጻታቸው ወቅት በተፈጸመ ጊዜ፣ ዮሴፍና ማርያም ሕፃኑን ለጌታ ለማቅረብ ወደ ኢየሩሳሌም ይዘውት ወጡ፤ 23ይኸውም በጌታ ሕግ፣ “ተባዕት የሆነ በኵር ሁሉ ለጌታ የተቀደሰ ይሆናል” ተብሎ እንደ ተጻፈ ለመፈጸምና 24ደግሞም በጌታ ሕግ፣ “ሁለት ዋኖሶች ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች እንደ ተባለ፣” መሥዋዕት ለማቅረብ ነበር።

25በዚያን ጊዜ ጻድቅና ትጉህ የሆነ ስምዖን የሚባል አንድ ሰው በኢየሩሳሌም ይኖር ነበር፤ እርሱም የእስራኤልን መጽናናት የሚጠባበቅና መንፈስ ቅዱስ በላዩ ያደረ ሰው ነበር። 26ደግሞም የጌታን መሲሕ ሳያይ እንደማይሞት በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ነበር፤ 27እርሱም በዚህ ጊዜ በመንፈስ ተመርቶ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ፤ የልጁም ወላጆች በሕጉ ልማድ መሠረት ተገቢውን ሊፈጽሙለት ሕፃኑን ኢየሱስን ይዘው በገቡ ጊዜ፣ 28ስምዖን ተቀብሎ ዐቀፈው፤ እግዚአብሔርን እያመሰገነ እንዲህ አለ፤

29“ጌታ ሆይ፤ ቃል በገባኸው መሠረት፣

አሁን ባሪያህን በሰላም አሰናብተው፤

30ዐይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን፣

31ማዳንህን አይተዋልና።

32ይህም ለአሕዛብ መገለጥን የሚሰጥ ብርሃን፣

ለሕዝብህ ለእስራኤልም ክብር ነው።”

33አባቱና እናቱም ስለ እርሱ በተነገረው ነገር ተገረሙ። 34ስምዖንም ባረካቸው፤ እናቱን ማርያምንም እንዲህ አላት፤ “ይህ ሕፃን በእስራኤል ለብዙዎች መነሣትና መውደቅ ምክንያት እንዲሆን፣ ደግሞም ክፉ ለሚያስወሩበት ምልክት እንዲሆን ተወስኗል፤ 35የብዙዎችም የልብ ሐሳብ የተገለጠ እንዲሆን፣ የአንቺም ነፍስ ደግሞ በሰይፍ ይወጋል።”

36ደግሞም ከአሴር ወገን የሆነች የፋኑኤል ልጅ፣ ሐና የምትባል ነቢይት በዚያ ነበረች፤ እርሷም በጣም አርጅታ ነበር፤ በድንግልናዋ ካገባችው ባሏም ጋር ሰባት ዓመት የኖረች ነበረች፤ 37ዕድሜዋም ሰማንያ አራት ዓመት2፥37 ወይም ለሰማንያ አራት ዓመት መበለት የነበረች እስኪሆናት ድረስ ቀንና ሌሊት ከቤተ መቅደስ ሳትለይ፣ በጾምና በጸሎት የምታገለግል መበለት ሆና ቈየች። 38በዚያኑም ጊዜ ቀርባ እግዚአብሔርን አመሰገነች፤ የኢየሩሳሌምንም መቤዠት ለሚጠባበቁ ሁሉ ስለ ሕፃኑ ተናገረች።

39ዮሴፍና ማርያም በጌታ ሕግ የታዘዘውን ሁሉ ከፈጸሙ በኋላ፣ በገሊላ አውራጃ ወዳለችው ከተማቸው ወደ ናዝሬት ተመለሱ። 40ሕፃኑም እያደገና እየጠነከረ ሄደ፤ በጥበብ ተሞላ፤ የእግዚአብሔርም ጸጋ በእርሱ ላይ ነበረ።

ኢየሱስ በዐሥራ ሁለት ዓመቱ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ

41ወላጆቹም በየዓመቱ ለፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይሄዱ ነበር። 42ልጁም ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ፣ እንደተለመደው ወደ በዓሉ ወጡ። 43በዓሉን ከፈጸሙ በኋላ፣ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀረ፤ ወላጆቹ ግን መቅረቱን አላወቁም ነበር። 44አብሯቸው ያለ መስሏቸው የአንድ ቀን መንገድ ተጓዙ፤ በኋላ ግን ከዘመዶቻቸውና ከወዳጆቻቸው ዘንድ ይፈልጉት ጀመር፤ 45ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።

46ከሦስት ቀንም በኋላ፣ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲያዳምጣቸውና ጥያቄ ሲያቀርብላቸው በቤተ መቅደስ ውስጥ አገኙት፤ 47የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ይደነቁ ነበር። 48ወላጆቹም ባዩት ጊዜ ተገረሙ፤ እናቱም፣ “ልጄ ሆይ፤ ለምን እንዲህ አደረግኸን? አባትህና እኔ እኮ ተጨንቀን ስንፈልግህ ነበር” አለችው።

49እርሱም፣ “ለምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት መገኘት እንደሚገባኝ አላወቃችሁምን?” አላቸው። 50እነርሱ ግን የተናገራቸው ነገር አልገባቸውም።

51ከዚያም አብሯቸው ወደ ናዝሬት ወረደ፤ ይታዘዝላቸውም ነበር። እናቱም ይህን ሁሉ ነገር በልቧ ትጠብቀው ነበር። 52ኢየሱስም በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት አደገ።

Knijga O Kristu

Luka 2:1-52

Isusovo rođenje

1U to vrijeme rimski car August zapovjedi da se svi žitelji Carstva popišu. 2Bio je to prvi popis stanovništva proveden za Kvirinijeva upravljanja Sirijom. 3Svatko je putovao u svoj grad da se ondje upiše.

4Tako je i Josip iz gradića Nazareta u Galileji, jer je bio iz loze kralja Davida, pošao u Davidov grad zvani Betlehem 5da se upiše skupa sa svojom zaručnicom Marijom koja je već bila trudna. 6Dok su bili ondje, dođe joj vrijeme da rodi 7te ona rodi sina, svojeg prvorođenca. Povila ga je i položila u jasle jer u seoskome svratištu nije za njih bilo mjesta.

Pastiri i anđeli

8U tome su kraju boravili pastiri. Noću su pod vedrim nebom čuvali stada ovaca. 9Odjednom se pokraj njih pojavi anđeo Gospodnji i obasja ih Gospodnja slava. Oni se silno prestraše, 10ali anđeo im reče: “Ne bojte se! Donosim vam, evo, radosnu vijest, na veliko veselje svemu narodu! 11Spasitelj—Krist, Gospodin rodio vam se danas u Davidovu gradu! 12Evo znaka po kojemu ćete ga prepoznati: naći ćete povijeno novorođenče da leži u jaslama.”

13Anđelu se odjednom pridruži silna nebeska vojska slaveći Boga:

14“Slava Bogu na visini,

a na zemlji mir ljudima, njegovim miljenicima.”

15Čim su se anđeli vratili na nebo, pastiri stanu poticati jedni druge: “Hajdemo u Betlehem! Hajdemo vidjeti taj događaj koji nam je Gospodin objavio!”

16Pohitaju do sela i ondje pronađu Mariju i Josipa s novorođenčetom koje je ležalo u jaslama. 17Kad su ga vidjeli, svima su ispričali što im je anđeo rekao o djetetu. 18A svi koji su pastire slušali divili su se. 19Marija je pomnjivo pamtila sve što su govorili i razmišljala je o tome. 20Pastiri se zatim vrate slaveći i hvaleći Boga za sve što su čuli i vidjeli te što se dogodilo onako kako im je anđeo rekao.

21Osam dana poslije, kad je dječaka trebalo obrezati, nadjenuli su mu ime Isus koje mu je anđeo dao još prije začeća.

Isusa prikazuju u Hramu

22Kad je došlo vrijeme za obred očišćenja koji je prema Mojsijevu zakonu2:22 Vidjeti Levitski zakonik 12:1-4. trebalo obaviti nakon djetetova rođenja, donijeli su ga u Jeruzalem da ga prikažu Gospodinu, 23kako piše u Zakonu Gospodnjemu: “Svako muško prvorođenče neka se posveti Gospodinu”,2:23 Izlazak 13:2. 24te su prinijeli i žrtvu prema zakonskoj odredbi: “dvije grlice ili dva golubića”.

Šimunovo proročanstvo

25Živio je tada u Jeruzalemu neki čovjek imenom Šimun. Bio je to vrlo pravedan i pobožan čovjek; Sveti je Duh bio na njemu te je iščekivao da dođe Mesija i izbavi Izrael.2:25 …iščekivao da dođe Mesija i izbavi Izrael. U grčkome: iščekivao utjehu Izraelovu. 26Sveti mu je Duh otkrio da neće umrijeti dok ne vidi Mesiju Gospodnjega. 27Potaknut Svetim Duhom, on ode u Hram. Kad su roditelji unijeli Isusa da obave obred propisan Zakonom, 28Šimun uzme dijete u naručje te stane slaviti Boga:

29“Sada možeš pustiti svojega slugu, Gospodine,

da ode u miru, kao što si mi rekao.

30Jer oči su mi vidjele tvoje spasenje

31koje si pripravio za sve narode,

32svjetlo da prosvijetli pogane,

slavu tvojega izraelskog naroda.”

33Isusovi roditelji divili su se riječima izgovorenima o njemu. 34Šimun ih zatim blagoslovi i reče Mariji: “Određen je za to da mnogima u Izraelu bude na propast i mnogima na uskrsnuće, za osporavani znak. 35A tebi će mač probosti dušu da se razotkriju namisli mnogih srca!”

Anino proročanstvo

36Bila je ondje i neka proročica Ana, Penuelova kći iz Ašerova plemena, vrlo stara žena. Poslije djevojaštva živjela je u braku sedam godina, 37a zatim sama, kao udovica do osamdeset četvrte godine. Nije napuštala Hram, već je postom i molitvom danonoćno služila Bogu. 38Ona baš tada naiđe te počne zahvaljivati Bogu i govoriti o Isusu svima koji su iščekivali obećanog Mesiju i otkupljenje Jeruzalema.2:38 U grčkome: samo koji su iščekivali otkupljenje Jeruzalema.

39Kad Isusovi roditelji ispune sve odredbe Gospodnjeg zakona, vrate se u Nazaret, u Galileju. 40Dijete je raslo i jačalo. Punilo se mudrošću i Božja je milost bila s njim.

Isus razgovara s učiteljima

41Isusovi su roditelji svake godine o blagdanu Pashe išli u Jeruzalem. 42Kad mu je bilo dvanaest godina, pošli su kao obično na svetkovinu. 43Nakon svetkovine dječak Isus ostao je u Jeruzalemu, a njegovi roditelji to nisu znali. 44Pretpostavljali su da je među ostalim suputnicima. Odmaknuli su tako dan hoda, a onda ga počeli tražiti među rodbinom i znancima, 45ali ga nisu našli. Vrate se stoga u Jeruzalem ondje ga potražiti. 46Nakon tri dana pronađu ga u Hramu među vjerskim učiteljima kako ih sluša i postavlja im pitanja. 47Svi koji su ga slušali divili su se njegovoj oštroumnosti i odgovorima.

48Roditelji nisu znali što da misle. “Sine!” reče mu majka. “Zašto si nam to učinio? Tvoj otac i ja silno smo se zabrinuli i posvuda smo te tražili!”

49“Zašto ste me tražili?” odgovori on. “Zar niste znali da ja moram biti u onomu što je mojega Oca?” 50Ali oni nisu razumjeli što im je htio kazati.

51Vratio se zatim s njima u Nazaret i bio im je poslušan, a njegova je majka sve to brižno čuvala u svojemu srcu. 52A Isus je napredovao u mudrosti, rastu i milosti kod Boga i ljudi.