ሉቃስ 18 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 18:1-43

ተግታ የለመነችው መበለት ምሳሌነት

1ደቀ መዛሙርቱ ሳይታክቱ ሁልጊዜ መጸለይ እንደሚገባቸው ለማሳየት ኢየሱስ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህም አላቸው፤ “በአንዲት ከተማ የሚኖር እግዚአብሔርን የማይፈራና ሰውን የማያከብር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ የምትኖር አንዲት መበለት ነበረች፤ እርሷም፣ ‘ከባላጋራዬ ጋር ስላለብኝ ጕዳይ ፍረድልኝ’ እያለች ወደ እርሱ ትመላለስ ነበር።

4“ዳኛውም ለተወሰነ ጊዜ አልተቀበላትም ነበር፤ በኋላ ግን በልቡ እንዲህ አለ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላከብር፣ 5ይህች መበለት ስለምትጨቀጭቀኝ እፈርድላታለሁ፤ አለዚያ ዘወትር እየተመላለሰች ታሰለቸኛለች።’ ”

6ጌታም እንዲህ አለ፤ “ዐመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ። 7እግዚአብሔርስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? ከመጠን በላይስ ችላ ይላቸዋልን? 8እላችኋለሁ፤ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል፤ ነገር ግን የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ በምድር ላይ እምነትን ያገኝ ይሆንን?”

የፈሪሳዊውና የቀረጥ ሰብሳቢው ምሳሌነት

9ራሳቸውን እንደ ጻድቃን በመቍጠር ለሚመኩና ሌሎቹን በንቀት ዐይን ለሚመለከቱ ሰዎች እንዲህ ሲል ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ 10“ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ ቤተ መቅደስ ወጡ፣ አንዱ ፈሪሳዊ፣ ሌላው ቀረጥ ሰብሳቢ ነበሩ። 11ፈሪሳዊውም ቆሞ ስለ18፥11 ወይም ለራሱ ራሱ እንዲህ ይጸልይ ነበር፤ ‘እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔ እንደ ሌላው ሰው ሁሉ ቀማኛ፣ ዐመፀኛ፣ አመንዝራ፣ ይልቁንም እንደዚህ ቀረጥ ሰብሳቢ ባለ መሆኔ አመሰግንሃለሁ፤ 12በሳምንት ሁለት ጊዜ እጾማለሁ፤ ከማገኘውም ሁሉ ዐሥራት አወጣለሁ።’

13“ቀረጥ ሰብሳቢው ግን በርቀት ቆሞ፣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ማየት እንኳ አልፈለገም፤ ነገር ግን ደረቱን እየደቃ፣ ‘እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ኀጢአተኛውን ማረኝ’ ይል ነበር።

14“እላችኋለሁ፤ ከፈሪሳዊው ይልቅ ይህኛው በእግዚአብሔር ዘንድ እንደ ጻድቅ ተቈጥሮ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ዝቅ ይላልና፤ ራሱን ዝቅ ዝቅ የሚያደርግ ግን ከፍ ይላል።”

ኢየሱስ ከሕፃናት ጋር

18፥15-17 ተጓ ምብ – ማቴ 19፥13-15ማር 10፥13-16

15ኢየሱስ እንዲዳስሳቸው ሰዎች ሕፃናትን ወደ እርሱ ያመጡ ነበር፤ ደቀ መዛሙርቱም ይህን ባዩ ጊዜ ገሠጿቸው። 16ኢየሱስ ግን ሕፃናቱን ወደ ራሱ ጠርቶ እንዲህ አለ፤ “ሕፃናት ወደ እኔ እንዲመጡ ፍቀዱላቸው፤ አትከልክሏቸው፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና። 17እውነት እላችኋለሁ፤ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ሕፃን የማይቀበል ሁሉ ከቶ አይገባባትም።”

ሀብታሙ የአይሁድ አለቃ

18፥18-30 ተጓ ምብ – ማቴ 19፥16-29ማር 10፥17-30

18ከአይሁድ አለቆች አንዱ፣ “ቸር መምህር ሆይ፤ የዘላለምን ሕይወት ለመውረስ ምን ላድርግ?” ሲል ጠየቀው።

19ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰለት፤ “ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም፤ 20‘አታመንዝር፣ አትግደል፣ አትስረቅ፣ በሐሰት አትመስክር፣ አባትህንና እናትህን አክብር’ የሚለውን ትእዛዝ ታውቃለህ።”

21ሰውየውም፣ “እነዚህንማ ከልጅነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ” አለው።

22ኢየሱስም ይህን በሰማ ጊዜ፣ “እንግዲያውስ አንድ ነገር ይቀርሃል፤ ያለህን ሁሉ ሸጠህ ለድኾች ስጥ፤ በሰማይ መዝገብ ይኖርሃል፤ ከዚያም መጥተህ ተከተለኝ” አለው።

23ሰውየው ግን ይህን ሲሰማ፣ ብዙ ሀብት ስለ ነበረው በጣም ዐዘነ። 24ኢየሱስም ሰውየውን ተመልክቶ እንዲህ አለ፤ “ብዙ ሀብት ላላቸው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ነው? 25ሀብታም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀልላል።”

26ይህን የሰሙ ሰዎችም፣ “ታዲያ፣ ማን ሊድን ይችላል?” አሉ።

27ኢየሱስም፣ “በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል” አለ።

28ጴጥሮስም፣ “እነሆ፤ እኛ ያለንን ሁሉ ትተን ተከትለንሃል” አለው።

29ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ፤ ለእግዚአብሔር መንግሥት ብሎ ቤቱን ወይም ሚስቱን ወይም ወንድሞቹን ወይም ወላጆቹን ወይም ልጆቹን የተወ፣ 30በዚህ ዘመን ብዙ ዕጥፍ፣ በሚመጣውም ዘመን የዘላለምን ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም።”

ኢየሱስ ስለ ሞቱ ዳግመኛ ተናገረ

18፥31-33 ተጓ ምብ – ማቴ 20፥17-19ማር 10፥32-34

31ኢየሱስም ዐሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ለብቻ ወስዶ እንዲህ አላቸው፤ “እንግዲህ ወደ ኢየሩሳሌም ልንወጣ ነው፤ ነቢያት ስለ ሰው ልጅ የጻፉትም ሁሉ ይፈጸማል። 32ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታል፤ እነርሱም ያፌዙበታል፤ ያንገላቱታል፤ ይተፉበታል፤ ይገርፉታል፤ ከዚያም ይገድሉታል። 33እርሱም በሦስተኛው ቀን ከሙታን ይነሣል።”

34ደቀ መዛሙርቱ ግን ከዚህ ሁሉ የተረዱት አንድም ነገር አልነበረም፤ አባባሉም ተሰውሮባቸው ነበር፤ ስለ ምን እንደ ተናገረም አላወቁም።

የዐይነ ስውሩ መፈወስ

18፥35-43 ተጓ ምብ – ማቴ 20፥29-34ማር 10፥46-52

35ኢየሱስ ወደ ኢያሪኮ በቀረበ ጊዜ፣ አንድ ዐይነ ስውር መንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን ነበር። 36ዐይነ ስውሩም ሕዝቡ በዚያ ሲያልፍ ሰምቶ ስለ ሁኔታው ጠየቃቸው። 37እነርሱም፣ “የናዝሬቱ ኢየሱስ በዚህ እያለፈ ነው” ብለው ነገሩት።

38እርሱም፣ “የዳዊት ልጅ፣ ኢየሱስ ሆይ፤ ማረኝ!” እያለ ጮኸ።

39ከፊት የሚሄዱ ሰዎችም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን፣ “የዳዊት ልጅ ሆይ፤ ማረኝ!” እያለ አብዝቶ ጮኸ።

40ኢየሱስም ቆም ብሎ ሰውየውን ወደ እርሱ እንዲያመጡት አዘዘ፤ ወደ እርሱም በቀረበ ጊዜ፣ 41“ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ?” ብሎ ጠየቀው።

ዐይነ ስውሩም፣ “ጌታ ሆይ፤ ማየት እፈልጋለሁ” አለው።

42ኢየሱስም፣ “እይ፤ እምነትህ አድኖሃል” አለው። 43ሰውየውም ወዲያውኑ ማየት ቻለ፤ እግዚአብሔርንም እያከበረ ኢየሱስን ተከተለው። ሕዝቡም ሁሉ ይህን ሲያዩ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

Thai New Contemporary Bible

ลูกา 18:1-43

คำอุปมาเรื่องหญิงม่ายผู้ไม่ลดละ

1แล้วพระเยซูตรัสคำอุปมาสอนเหล่าสาวกให้อธิษฐานเสมออย่างไม่ลดละ 2พระองค์ตรัสว่า “ในเมืองหนึ่งมีผู้พิพากษาคนหนึ่งซึ่งไม่เกรงกลัวพระเจ้าและไม่เห็นแก่หน้ามนุษย์คนใด 3ในเมืองนั้นมีหญิงม่ายคนหนึ่งที่เพียรมาหาเขา และพร่ำวิงวอนว่า ‘กรุณาให้ความยุติธรรมในคดีของข้าพเจ้าด้วยเถิด’

4“ผู้พิพากษานั้นปฏิเสธนางอยู่ระยะหนึ่ง แต่ในที่สุดเขานึกในใจว่า ‘ถึงแม้เราไม่เกรงกลัวพระเจ้า และไม่เห็นแก่หน้ามนุษย์คนใด 5แต่เพราะหญิงม่ายคนนี้คอยกวนใจเราอยู่ตลอดเวลา เราจะให้ความยุติธรรมแก่นาง เพื่อนางจะได้ไม่มารบกวนให้เราระอาใจ!’ ”

6และองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “จงฟังคำพูดของผู้พิพากษาอยุติธรรมคนนี้ 7แล้วพระเจ้าจะไม่ให้ความยุติธรรมแก่ผู้ที่พระองค์ทรงเลือกสรรหรือ? ในเมื่อเขาร้องทูลพระองค์ทั้งวันทั้งคืน พระองค์จะทรงผัดผ่อนเขาอยู่ร่ำไปหรือ? 8เราบอกท่านว่า พระองค์จะทรงดูแลให้พวกเขาได้รับความยุติธรรมโดยเร็ว แต่เมื่อบุตรมนุษย์เสด็จมา พระองค์จะพบความเชื่อในโลกหรือ?”

คำอุปมาเรื่องฟาริสีกับคนเก็บภาษี

9สำหรับบางคนที่มั่นใจในความชอบธรรมของตนเองและดูถูกคนอื่นทั้งปวงนั้น พระเยซูตรัสคำอุปมานี้ว่า 10“ชายสองคนไปที่พระวิหารเพื่ออธิษฐาน คนหนึ่งเป็นฟาริสี และอีกคนหนึ่งเป็นคนเก็บภาษี 11ฟาริสีคนนั้นยืนขึ้นอธิษฐานเกี่ยวกับ18:11 หรือต่อ ตนเองว่า ‘ข้าแต่พระเจ้าขอบพระคุณพระองค์ ที่ข้าพระองค์ไม่เหมือนคนอื่นๆ ที่เป็นโจรปล้น ทำชั่ว ล่วงประเวณี หรือเป็นอย่างคนเก็บภาษีคนนี้ 12ข้าพระองค์ถืออดอาหารสัปดาห์ละสองครั้ง และถวายสิบลดจากทุกสิ่งที่ได้มา’

13“แต่คนเก็บภาษีนั้นยืนไกลออกไป เขาไม่กล้าแม้แต่จะเงยหน้าขึ้นฟ้า แต่ทุบตีอกของตนและพูดว่า ‘ข้าแต่พระเจ้า ขอทรงเมตตาข้าพระองค์ผู้เป็นคนบาปด้วยเถิด’

14“เราบอกท่านว่า คนนี้ต่างหากที่กลับบ้านไปโดยถือว่าเป็นผู้ชอบธรรมต่อหน้าพระเจ้า เพราะทุกคนที่ยกตนเองขึ้นจะถูกทำให้ต่ำลง และผู้ที่ถ่อมตนลงจะได้รับการเชิดชูขึ้น”

พระเยซูกับเด็กเล็กๆ

(มธ.19:13-15; มก.10:13-16)

15ประชาชนอุ้มทารกมาให้พระเยซูทรงแตะต้อง เมื่อเหล่าสาวกเห็นก็ตำหนิพวกเขา 16แต่พระเยซูทรงเรียกเด็กๆ เข้ามาหาพระองค์และตรัสว่า “จงให้เด็กเล็กๆ มาหาเราและอย่าขัดขวางเขาเลย เพราะอาณาจักรของพระเจ้าเป็นของคนที่เป็นเหมือนเด็กๆ เหล่านี้ 17เราบอกความจริงแก่ท่านว่า ผู้ใดไม่รับอาณาจักรของพระเจ้าเหมือนเด็กเล็กๆ ผู้นั้นจะไม่มีวันได้เข้าอาณาจักรพระเจ้าเลย”

ขุนนางผู้ร่ำรวย

(มธ.19:16-29; มก.10:17-30)

18ขุนนางคนหนึ่งทูลถามพระองค์ว่า “ท่านอาจารย์ผู้ประเสริฐ ข้าพเจ้าจะต้องทำอะไรบ้างจึงจะได้ชีวิตนิรันดร์?”

19พระเยซูตรัสตอบว่า “ทำไมท่านจึงบอกว่าเราประเสริฐ? นอกจากพระเจ้าแล้ว ไม่มีใครอื่นที่ประเสริฐ 20ท่านก็รู้บทบัญญัติที่ว่า ‘อย่าล่วงประเวณี อย่าฆ่าคน อย่าลักขโมย อย่าเป็นพยานเท็จ จงให้เกียรติบิดามารดาของเจ้า’18:20 อพย.20:12-16ฉธบ.5:16-20

21เขาทูลว่า “ทั้งหมดนี้ ข้าพเจ้าถือปฏิบัติมาตั้งแต่เด็ก”

22เมื่อพระเยซูทรงได้ยินดังนั้น ก็ตรัสกับเขาว่า “ท่านยังขาดอยู่อย่างหนึ่ง จงขายทุกสิ่งที่มีและแจกจ่ายให้คนยากจน แล้วท่านจะมีทรัพย์สมบัติในสวรรค์ จากนั้นจงตามเรามา”

23เมื่อเขาได้ยินเช่นนั้นก็เศร้าสลด เพราะเขาร่ำรวยมาก 24พระเยซูทรงมองดูเขาและตรัสว่า “ยากนักที่คนรวยจะเข้าอาณาจักรของพระเจ้า! 25อันที่จริง ให้อูฐลอดรูเข็มยังง่ายกว่าที่คนรวยจะเข้าอาณาจักรของพระเจ้า”

26บรรดาผู้ที่ได้ฟังเช่นนี้ทูลถามว่า “ถ้าเช่นนั้น ใครจะรอดได้?”

27พระเยซูตรัสตอบว่า “สิ่งที่เป็นไปไม่ได้สำหรับมนุษย์ เป็นไปได้สำหรับพระเจ้า”

28เปโตรทูลว่า “ข้าพระองค์ทั้งหลายได้ละทุกสิ่งที่มีมาติดตามพระองค์!”

29พระเยซูตรัสแก่พวกเขาว่า “เราบอกความจริงแก่พวกท่านว่า ไม่มีผู้ใดที่ละทิ้งบ้านเรือน หรือภรรยา หรือพี่น้อง หรือบิดามารดา หรือลูกๆ เพื่ออาณาจักรของพระเจ้า 30แล้วจะไม่ได้รับผลตอบแทนหลายเท่าในยุคนี้ และชีวิตนิรันดร์ในยุคหน้า”

ทรงพยากรณ์อีกว่าจะต้องสิ้นพระชนม์

(มธ.20:17-19; มก.10:32-34)

31พระเยซูทรงพาสาวกทั้งสิบสองคนเลี่ยงออกมาและตรัสบอกพวกเขาว่า “พวกเรากำลังขึ้นไปยังกรุงเยรูซาเล็ม และทุกอย่างที่บรรดาผู้เผยพระวจนะเขียนไว้เกี่ยวกับบุตรมนุษย์จะสำเร็จ 32พระองค์จะถูกมอบให้คนต่างชาติ พวกเขาจะเยาะเย้ย ดูหมิ่น ถ่มน้ำลายรด โบยตี และฆ่าพระองค์ 33ในวันที่สามพระองค์จะเป็นขึ้นมาใหม่”

34เหล่าสาวกไม่เข้าใจสิ่งเหล่านี้เลย ความหมายของสิ่งเหล่านี้ถูกปิดบังจากพวกเขาและพวกเขาไม่รู้ว่าพระองค์กำลังตรัสถึงเรื่องอะไร

ขอทานตาบอดมองเห็น

(มธ.20:29-34; มก.10:46-52)

35เมื่อพระเยซูเสด็จมาใกล้เมืองเยรีโค มีชายตาบอดคนหนึ่งกำลังนั่งขอทานอยู่ริมทาง 36เมื่อได้ยินเสียงฝูงชนเดินผ่าน เขาจึงถามว่าเกิดอะไรขึ้น 37คนเหล่านั้นบอกเขาว่า “พระเยซูแห่งนาซาเร็ธกำลังเสด็จผ่าน”

38ชายตาบอดคนนั้นจึงร้องขึ้นว่า “พระเยซูบุตรดาวิดเจ้าข้า เมตตาข้าพระองค์ด้วยเถิด!”

39บรรดาผู้ที่เดินนำหน้าตำหนิและบอกให้เขาเงียบ แต่เขายิ่งร้องดังขึ้นอีกว่า “บุตรดาวิดเจ้าข้า เมตตาข้าพระองค์ด้วยเถิด!”

40พระเยซูทรงหยุดและตรัสสั่งให้คนพาเขามาหาพระองค์ เมื่อเขาเข้ามาใกล้พระเยซูตรัสถามว่า 41“ท่านต้องการให้เราทำอะไรให้?”

เขาทูลว่า “พระองค์เจ้าข้า ข้าพระองค์อยากมองเห็น”

42พระเยซูตรัสกับเขาว่า “จงมองเห็นเถิด ความเชื่อของท่านทำให้ท่านหายแล้ว” 43ทันใดนั้นเขาก็มองเห็นได้และตามพระเยซูไป พร้อมกับสรรเสริญพระเจ้า เมื่อคนทั้งปวงเห็นเช่นนั้นก็สรรเสริญพระเจ้าด้วย