ሉቃስ 16 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ሉቃስ 16:1-31

የብልኁ መጋቢ ምሳሌነት

1ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ፤ “አንድ ሀብታም ሰው አንድ መጋቢ ነበረው፤ ይኸው መጋቢ የሀብታሙን ሰው ንብረት እንደሚያባክን ለዚሁ ሰው ወሬ ደረሰው። 2ስለዚህ አስጠራውና፣ ‘ይህ የምሰማብህ ምንድን ነው? ከእንግዲህ አንተ መጋቢ ልትሆነኝ ስለማትችል፣ የምታስተዳድረውን ንብረት መቈጣጠሪያ ሒሳብ አስረክበኝ’ አለው።

3“መጋቢውም በልቡ እንዲህ አለ፤ ‘ጌታዬ ከመጋቢነት ሊሽረኝ ነው፤ ለማረስ ጕልበት የለኝም፤ መለመን ደግሞ ዐፍራለሁ፤ ስለዚህ ምን ላድርግ? 4ከመጋቢነት የተሻርሁ እንደ ሆነ፣ ሰዎች በቤታቸው እንዲቀበሉኝ የማደርገውን ዐውቃለሁ።’

5“ስለዚህ የጌታው ዕዳ ያለባቸውን ሰዎች እያንዳንዳቸውን ጠራ፤ የመጀመሪያውንም ሰው ‘የጌታዬ ዕዳ ምን ያህል አለብህ?’ አለው።

6“እርሱም፣ ‘አንድ መቶ ማድጋ16፥6 ምናልባት 3 ሺሕ ሊትር ይሆናል ዘይት አለብኝ’ አለ።

“መጋቢውም፣ ‘የውል ወረቀትህን ዕንካ፤ ቶሎ ተቀምጠህ “አምሳ ማድጋ” ብለህ ጻፍ’ አለው።

7“ከዚያም ሌላውን፣ ‘አንተስ ስንት አለብህ?’ አለው።

“እርሱም፣ ‘አምሳ ዳውላ16፥7 ምናልባት አንድ መቶ የቆሮስ መስፈሪያ ወይም 35 ሺሕ ሊትር ይሆናል። ስንዴ’ አለው።

“መጋቢውም፣ ‘የብድር ደብዳቤህን ዕንካ፤ “አርባ ዳውላ” ብለህ ጻፍ’ አለው።

8“ጌታውም አጭበርባሪውን መጋቢ በብልኅነቱ አደነቀው፤ የዚህ ዓለም ልጆች ከመሰሎቻቸው ጋር በሚኖራቸው ግንኙነት ከብርሃን ልጆች ይልቅ ብልኆች ናቸውና። 9ስለዚህ እላችኋለሁ፤ የዚህ ዓለም ገንዘብ ባለቀ ጊዜ በዘላለም ቤት ተቀባይነት እንዲኖራችሁ፣ በዚሁ ገንዘብ ወዳጆችን ለራሳችሁ አፍሩበት።

10“በትንሽ ነገር ታማኝ የሆነ በትልቁም ይታመናል፤ በትንሽ ነገር ያልታመነ በትልቁም አይታመንም። 11እንግዲህ፣ በዚህ ዓለም ሀብት ካልታመናችሁ፣ እውነተኛውንማ ሀብት ማን ዐደራ ብሎ ይሰጣችኋል? 12በሌላው ሰው ሀብት ካልታመናችሁ፣ የራሳችሁ የሆነውን ሀብት ማን ይሰጣችኋል?

13“በአንድ ጊዜ ሁለት ጌቶችን ማገልገል የሚችል ማንም ባሪያ የለም፤ አንዱን ጠልቶ ሌላውን ይወድዳል፤ ወይም አንዱን ይጠጋል፤ ሌላውን ይንቃል። የእግዚአብሔርም የገንዘብም ባሪያ መሆን አትችሉም።”

14ገንዘብ የሚወድዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው በኢየሱስ ላይ አፌዙበት። 15እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “እናንተ በሰዎች ፊት ራሳችሁን የምታጸድቁ ናችሁ፤ እግዚአብሔር ግን ልባችሁን ያውቃል፤ በሰዎች ዘንድ የከበረ፣ በእግዚአብሔር ፊት የረከሰ ነውና።

16“ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ድረስ ሲነገሩ ኖረዋል፤ ከዚያ በኋላ ግን የእግዚአብሔር መንግሥት የምሥራች ተሰብኳል፤ ሰውም ሁሉ ወደዚያ ለመግባት ይሻማል። 17ነገር ግን ከሕግ አንዲት ነጥብ ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀልላል።

18“ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፤ ከባሏ የተፋታችውንም ሴት የሚያገባ ያመነዝራል።”

ሀብታሙ ሰውና አልዓዛር

19ደግሞም ኢየሱስ እንዲህ አለ፤ “ሐምራዊና ቀጭን በፍታ የለበሰ፣ በየቀኑም በተድላ ደስታ የሚኖር አንድ ሀብታም ሰው ነበረ። 20በአንጻሩም፣ መላ ሰውነቱ በቍስል የተወረረ አንድ አልዓዛር የሚባል ድኻ በዚህ ሀብታም ሰው ደጃፍ ይተኛ ነበር፤ 21ከሀብታሙ ሰው ማእድ የወደቀውን ፍርፋሪ እንኳ ሊመገብ ይመኝ ነበር፤ ውሾችም ሳይቀሩ መጥተው ቍስሉን ይልሱ ነበር።

22“ይህም ድኻ ሞተ፤ መላእክትም ወደ አብርሃም ዕቅፍ ወሰዱት። ሀብታሙም ሰው ደግሞ ሞቶ ተቀበረ። 23በሲኦልም እየተሠቃየ ሳለ ቀና ብሎ ከሩቅ አብርሃምን አየ፤ አልዓዛርንም በዕቅፉ ይዞት አየ። 24እርሱም፣ ‘አብርሃም አባት ሆይ፤ ራራልኝ፤ በዚህ ነበልባል እየተሠቃየሁ ስለሆነ፣ አልዓዛር የጣቱን ጫፍ ውሃ ነክሮ ምላሴን እንዲያቀዘቅዝልኝ እባክህ ላክልኝ’ እያለ ጮኸ።

25“አብርሃም ግን እንዲህ አለው፤ ‘ልጄ ሆይ፤ አንተ በምድራዊ ሕይወትህ ዘመን መልካም ነገሮችን እንደ ተቀበልህ፣ አልዓዛርም ደግሞ ክፉ ነገሮችን እንደ ተቀበለ አስታውስ፤ አሁን ግን እርሱ እዚህ ሲጽናና፣ አንተ በሥቃይ ላይ ትገኛለህ። 26ከሁሉም በላይ ከዚህ ወደ እናንተ ለማለፍ የሚፈልጉ እንደማይችሉ፣ እዚያ ያሉትም ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ፣ በእኛና በእናንተ መካከል ትልቅ ገደል ተደርጓል።’

27“እርሱም እንዲህ አለ፤ ‘አባት ሆይ፤ እንግዲያውስ አልዓዛርን ወደ አባቴ ቤት እንድትሰድደው እለምንሃለሁ፤ 28አምስት ወንድሞች ስላሉኝ፣ እነርሱም ወደዚህ የሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ያስጠንቅቃቸው።’

29“አብርሃም ግን፣ ‘ሙሴና ነቢያት አሏቸው፤ እነርሱን ይስሙ’ አለው።

30“እርሱም፣ ‘አብርሃም አባት ሆይ፤ እንደዚህ አይደለም፤ አንድ ሰው ከሙታን ተነሥቶ ቢሄድላቸው ንስሓ ይገባሉ’ አለ።

31“አብርሃምም፣ ‘ሙሴንና ነቢያትን የማይሰሙ ከሆነ፣ አንድ ሰው ከሙታን ቢነሣ እንኳ አያምኑም’ አለው።”

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי לוקס 16:1-31

1ישוע סיפר לתלמידיו את המשל הבא: ”לעשיר אחד היה עובד שניהל את הונו. יום אחד הגיעו שמועות לאוזני העשיר שמנהל עסקיו בוגד בו ומבזבז את רכושו וכספו.

2”קרא אליו העשיר את המנהל ואמר: ’שמעתי שאתה מרמה אותי ומועל באמוני. הכן לי דו״ח על מצב העסקים, משום שאני עומד לפטר אותך‘.

3”מנהל העסקים חשב לעצמו: ’מה אעשה לאחר שמעבידי יפטר אותי? אין לי כוח לעבוד עבודה פיזית, ואילו לבקש נדבות זה לא בכבוד שלי. 4יש לי רעיון! אני יודע מה אעשה כדי שאנשים יאספו אותי אל בתיהם לאחר שיפטרו אותי‘.

5”הוא הזמין אליו כל אחד מהאנשים שהיו חייבים כסף לאדוניו. ’כמה אתה חייב לאדוני?‘ שאל את הראשון. 6’מאה חביות שמן‘, ענה בעל החוב. ’נכון. קח את שטר־החוב שלך, קרע אותו וכתוב שטר חדש על חמישים חביות בלבד!‘

7” ’וכמה אתה חייב לאדוני?‘ שאל מנהל העסקים את בעל החוב הבא. ’מאה שקי חיטה‘, השיב האיש. אמר לו מנהל העסקים: ’קח את השטר הזה וכתוב במקומו שטר התחייבות על שמונים שקים בלבד‘.

8”האיש העשיר התפעל מעורמתו של המנהל שלו, שהרי בני העולם הזה יותר פיקחים מבני האור. 9מוסר ההשכל הוא זה: השתמשו במשאבים החומריים שלכם כדי לעזור לאחרים ולהשקיע במערכות יחסים. כי כאשר רכושכם בעולם הזה יאזל לכם, חבריכם יקבלו אתכם בשמחה לביתכם הנצחי.

10”מי שמרמה בדבר פעוט ירמה בדבר גדול. מי שמוכיח את יושרו ונאמנותו בדבר פעוט יהיה ישר ונאמן גם בדברים גדולים. 11ואם אי־אפשר לסמוך עליכם ולהפקיד בידיכם עושר הבא מן העולם הזה, מי יפקיד בידיכם את העושר האמיתי הבא מן השמים? 12ואם אי־אפשר לסמוך עליכם במה שנוגע לרכושם של אחרים, מי ייתן לכם רכוש משלכם?

13”אינך יכול לשרת שני אדונים; אתה תשנא את האחד ותאהב את האחר, או להיפך – תהיה נאמן לאחד ותזלזל באחר. אינך יכול לעבוד את האלוהים ואת הכסף!“

14הפרושים אהבו מאוד את כספם ולכן לעגו לישוע.

15אולם ישוע אמר להם: ”בפני הציבור אתם מעמידים פני צדיקים תמימים, אבל אלוהים יודע היטב מה מתרחש בלבכם. העמדת הפנים שלכם רכשה לכם כבוד בעיני בני־אדם, אולם היא שנואה ומתועבת בעיני אלוהים.

16”התורה והנביאים התבשרו עד ימי יוחנן המטביל. מאז, בשורת מלכות האלוהים מוכרזת ואנשים מתאמצים להיכנס אליה. 17אולם נקל יותר שהשמים והארץ ייעלמו מאשר שפרט קטן בתורה יאבד מאמיתותו.

18”איש שמגרש את אשתו ומתחתן עם אחרת הוא נואף. גם מי שמתחתן עם גרושה הוא נואף.“

19”פעם היה איש עשיר,“ סיפר ישוע, ”שהתלבש בצורה מפוארת ובילה את ימיו בעונג, בשחצנות ובבזבוז. 20בשער ביתו המפואר שכב קבצן אחד שהיה מכוסה כולו פצעים. ’אלעזר‘ קראו לו. 21הוא השתוקק להשביע את רעבונו מהפירורים שנפלו משולחנו של העשיר, והכלבים היו באים ומלקקים את פצעיו. 22יום אחד מת אלעזר הקבצן, והמלאכים נשאוהו אל חיק אברהם אבינו. כעבור זמן־מה מת גם העשיר, 23אולם הוא נלקח אל הגיהינום, שם התענה עינויים גדולים. כשהרים את ראשו בכאב, ראה מרחוק את אלעזר בחיקו של אברהם.

24” ’אברהם, אבי‘, קרא העשיר, ’אנא, רחם עלי. שלח אלי את אלעזר כדי שיטבול את אצבעו במים ויקרר את לשוני, כי אני מתענה באש הנוראה הזאת‘.

25”אולם אברהם ענה לו: ’בני, אל תשכח שנהנית בחייך מכל טוב, ואילו אלעזר סבל עוני וחולי. עכשיו התהפך הגלגל – אלעזר מנוחם ואילו אתה מתענה. 26מלבד זאת, תהום גדולה מפרידה בינינו. איש מאיתנו אינו יכול לעבור אליכם ואיש מכם אינו יכול לעבור אלינו‘.

27‏-28” ’אם כך, אבי‘ התחנן העשיר, ’עשה לי טובה; שלח בבקשה את אלעזר אל בית אבי, כדי שיזהיר את חמשת אחי מפני המקום הנורא הזה‘.

29”אולם אברהם השיב לו: ’כתבי־הקודש הזהירו את אחיך פעמים רבות. אחיך יכולים לקרוא את דברי משה והנביאים בכל עת שירצו‘.

30” ’אני מכיר אותם היטב‘, אמר לו העשיר. ’הם לא יטרחו לקרוא את דברי הנביאים. אבל אם יבוא אליהם מישהו מן המתים הם יחזרו בתשובה‘.

31”אך אברהם השיב: ’אם הם לא הקשיבו למשה ולנביאים, הם לא יקשיבו גם למי שיקום מן המתים‘. “