ሆሴዕ 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 9:1-17

በእስራኤል ላይ የሚደርሰው ቅጣት

1እስራኤል ሆይ፤ ደስ አይበልሽ፤

እንደ ሌሎችም ሕዝቦች ሐሤት አታድርጊ፤

ለአምላክሽ ታማኝ አልሆንሽምና፤

በየእህል ዐውድማውም ላይ፣

ለጋለሞታ የሚከፈለውን ዋጋ ወድደሻል።

2የእህል ዐውድማዎችና የወይን መጭመቂያዎች ሕዝቡን አይመግቡም፤

አዲሱም የወይን ጠጅ ይጐድልባቸዋል።

3በእግዚአብሔር ምድር አይቀመጡም፤

ኤፍሬም ወደ ግብፅ ይመለሳል፤

የረከሰውንም ምግብ9፥3 በሥርዐቱ መሠረት ያልነጻ ማለት ነው በአሦር ይበላል።

4የወይን ጠጅን ቍርባን ለእግዚአብሔር አያፈስሱም፤

መሥዋዕታቸውም ደስ አያሰኘውም፤

እንዲህ ዐይነቱ መሥዋዕት ለእነርሱ የሐዘንተኞች እንጀራ ይሆንባቸዋል፤

የሚበሉትም ሁሉ ይረክሳሉ።

ይህ ምግብ ለገዛ ራሳቸው ይሆናል፤

ወደ እግዚአብሔርም ቤተ መቅደስ አይገባም።

5በእግዚአብሔር የበዓል ቀናት፣

በዓመት በዓሎቻችሁም ቀን ምን ታደርጋላችሁ?

6ከጥፋት ቢያመልጡም እንኳ፣

ግብፅ ትሰበስባቸዋለች፤

ሜምፎስም ትቀብራቸዋለች።

የብር ሀብታቸውን ዳዋ ያለብሰዋል፤

ድንኳኖቻቸውንም እሾኽ ይወርሳቸዋል።

7የቅጣት ቀን መጥቷል፤

የፍርድም ቀን ቀርቧል፤

እስራኤልም ይህን ይወቅ!

ኀጢአታችሁ ብዙ፣

ጠላትነታችሁም ታላቅ ስለሆነ፣

ነቢዩ እንደ ሞኝ፣

መንፈሳዊውም ሰው እንደ እብድ ተቈጥሯል።

8ነቢዩ ከአምላኬ ጋር ሆኖ፣

የኤፍሬም ጠባቂ ነው፤9፥8 ወይም ነቢዩ የኤፍሬም ጠባቂ ነው፤ የአምላኬ ሕዝብ…

ዳሩ ግን በመንገዱ ሁሉ ወጥመድ፣

በአምላኩም ቤት ጠላትነት ይጠብቀዋል።

9በጊብዓ እንደ ነበረው፣

በርኩሰት ውስጥ ተዘፍቀዋል፤

እግዚአብሔር ክፋታቸውን ያስባል፤

ስለ ኀጢአታቸውም ይቀጣቸዋል።

10“እስራኤልን ማግኘቴ፣

የወይንን ፍሬ በምድረ በዳ የማግኘት ያህል ነበር፤

አባቶቻችሁንም ማየቴ፣

የመጀመሪያውን የበለስ ፍሬ የማየት ያህል ነበር፤

ወደ ብዔልፌጎር በመጡ ጊዜ ግን፣

ለዚያ አሳፋሪ ጣዖት ራሳቸውን ለዩ፤

እንደ ወደዱትም ጣዖት የረከሱ ሆኑ።

11የኤፍሬም ክብር እንደ ወፍ በርሮ ይጠፋል፤

መውለድ፣ ማርገዝና መፅነስ የለም።

12ልጆችን ቢያሳድጉ እንኳ፣

ልጅ አልባ እስኪሆኑ ድረስ እነጥቃቸዋለሁ፤

ፊቴን ከእነርሱ በመለስሁ ጊዜ፣

ወዮ ለእነርሱ!

13ኤፍሬምን እንደ ጢሮስ፣

በመልካም ስፍራ ተተክሎ አየሁት፤

አሁን ግን ኤፍሬም ልጆቹን፣

ለነፍሰ ገዳዮች አሳልፎ ይሰጣል።”

14እግዚአብሔር ሆይ፤ ስጣቸው፤

ምን ትሰጣቸዋለህ?

የሚጨነግፉ ማሕፀኖችን፣

የደረቁ ጡቶችን ስጣቸው።

15“በጌልገላ ካደረጉት ክፋታቸው ሁሉ የተነሣ፣

እኔ በዚያ ጠላኋቸው፤

ስለ ሠሩት ኀጢአት፣

ከቤቴ አሳድዳቸዋለሁ፤

ከእንግዲህም አልወድዳቸውም፤

መሪዎቻቸው ሁሉ ዐመፀኞች ናቸው።

16ኤፍሬም ተመታ፤

ሥራቸው ደረቀ፤

ፍሬም አያፈሩም፤

ልጆች ቢወልዱም እንኳ፣

ተንከባክበው ያሳደጓቸውን ልጆቻቸውን እገድላለሁ።”

17ባለመታዘዛቸው ምክንያት፣

አምላኬ ይጥላቸዋል፤

በአሕዛብም መካከል ተንከራታች ይሆናሉ።

Thai New Contemporary Bible

โฮเชยา 9:1-17

การลงโทษอิสราเอล

1อิสราเอลเอ๋ย อย่าชื่นชมยินดี

อย่าเปรมปรีดิ์เหมือนชาติอื่นๆ

เพราะเจ้าไม่ได้ซื่อสัตย์ต่อพระเจ้าของเจ้า

เจ้ารักค่าจ้างของหญิงโสเภณี

ตามลานนวดข้าวทุกแห่ง

2ลานนวดข้าวและบ่อย่ำองุ่นจะไม่พอเลี้ยงประชากร

เหล้าองุ่นใหม่ดับความกระหายของเขาไม่ได้

3พวกเขาจะไม่ได้อาศัยอยู่ในแผ่นดินขององค์พระผู้เป็นเจ้า

เอฟราอิมจะกลับไปอียิปต์

และกินอาหารที่มีมลทิน9:3 คือ เป็นมลทินตามระเบียบพิธีในอัสซีเรีย

4พวกเขาจะไม่ได้รินเหล้าองุ่นบูชาถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า

และเครื่องบูชาของเขาก็ไม่เป็นที่พอพระทัยพระองค์

เครื่องบูชาเหล่านี้จะเป็นเหมือนอาหารผู้ไว้ทุกข์สำหรับเขา

ผู้ที่กินเข้าไปจะเป็นมลทิน

อาหารนี้จะมีไว้เพื่อตัวเขาเอง

ไม่เหมาะที่จะนำเข้ามาในวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า

5พวกเจ้าจะทำอะไรในงานเลี้ยงฉลองตามกำหนด

ในวันเทศกาลขององค์พระผู้เป็นเจ้า?

6ถึงแม้พวกเขาจะรอดพ้นจากความพินาศย่อยยับ

อียิปต์ก็จะรวบรวมพวกเขา

และเมมฟิสจะฝังพวกเขาไว้

คลังเงินของพวกเขาจะถูกปกคลุมด้วยพืชหนาม

ต้นหนามจะงอกขึ้นท่วมเต็นท์ของพวกเขา

7วันแห่งการลงโทษกำลังมาถึง

วันลงอาญามาใกล้แล้ว

อิสราเอลจงรู้เถิด

เพราะบาปของพวกเจ้ามากมายนัก

เจตนาร้ายของพวกเจ้าใหญ่หลวงนัก

ผู้เผยพระวจนะถูกนับว่าเป็นคนโง่

ผู้ที่พระเจ้าดลใจกลับถูกหาว่าเป็นคนบ้าคลั่ง

8ผู้เผยพระวจนะพร้อมกับพระเจ้าของข้าพเจ้า

เป็นยามดูแลเอฟราอิม9:8 หรือผู้เผยพระวจนะเป็นยามดูแลเอฟราอิม / ผู้เป็นประชากรของพระเจ้าของข้าพเจ้า

แต่กับดักรอเขาอยู่ตลอดเส้นทาง

และมีศัตรูในพระนิเวศของพระเจ้าของพวกเขา

9พวกเขาจมดิ่งลงในความเสื่อมทราม

เหมือนสมัยกิเบอาห์

พระเจ้าจะทรงระลึกถึงความชั่วช้าของพวกเขา

และลงโทษบาปทั้งหลายของพวกเขา

10“เมื่อเราพบอิสราเอล

ก็เหมือนพบองุ่นในถิ่นกันดาร

เมื่อเราเห็นบรรพบุรุษของพวกเจ้า

ก็เหมือนเห็นผลมะเดื่อรุ่นแรก

แต่เมื่อพวกเขามาที่บาอัลเปโอร์

พวกเขาก็อุทิศตัวแก่เทวรูปอันน่าอับอายนั้น

และชั่วช้าไปเหมือนสิ่งที่พวกเขารัก

11ศักดิ์ศรีของเอฟราอิมจะบินหายลับไปเหมือนนก

ไม่มีการเกิด ไม่มีการตั้งครรภ์ และไม่มีการปฏิสนธิ

12ถึงแม้พวกเขาจะเลี้ยงดูลูกๆ ได้

เราก็จะพรากทุกคนไปจากพวกเขา

วิบัติแก่พวกเขา

เมื่อเราหันหนีไปจากพวกเขา!

13เราได้เห็นเอฟราอิม

ถูกปลูกไว้ในที่ร่มรื่นเช่นเดียวกับเมืองไทระ

แต่เอฟราอิมจะพาลูกๆ ของพวกเขา

ออกมาให้เพชฌฆาต”

14ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ขอโปรดประทาน

พระองค์จะประทานสิ่งใดแก่พวกเขา?

โปรดประทานครรภ์ที่แท้ง

และทรวงอกที่ไม่มีน้ำนม

15“เพราะความชั่วร้ายทั้งปวงของพวกเขาในกิลกาล

ที่นั่นเราจึงเกลียดชังพวกเขา

เพราะการกระทำอันบาปหนาของพวกเขา

เราจะขับไล่พวกเขาออกจากนิเวศของเรา

เราจะไม่รักพวกเขาอีกต่อไป

ผู้นำทั้งหมดของพวกเขาเป็นคนชอบกบฏ

16เอฟราอิมย่อยยับไปแล้ว

รากของพวกเขาเหี่ยวเฉา

พวกเขาไม่เกิดผล

ถึงแม้พวกเขามีลูก

เราก็จะประหารวงศ์วานที่รักยิ่งของพวกเขา”

17พระเจ้าของข้าพเจ้าจะปฏิเสธพวกเขา

เพราะพวกเขาไม่เชื่อฟังพระองค์

พวกเขาจะเป็นคนเร่ร่อนอยู่ท่ามกลางชนชาติต่างๆ