ሆሴዕ 7 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 7:1-16

1እስራኤልን በምፈውስበት ጊዜ፣

የኤፍሬም ኀጢአት፣

የሰማርያም ክፋት ይገለጣል።

እነርሱ ያጭበረብራሉ፤

ሌቦች ቤቶችን ሰብረው ይገባሉ፤

ወንበዴዎችም በየመንገድ ይዘርፋሉ።

2ነገር ግን ክፉ ድርጊታቸውን ሁሉ እንደማስታውስ፣

እነርሱ አይገነዘቡም፤

ኀጢአታቸው ከብቧቸዋል፤

ሁልጊዜም በፊቴ ናቸው።

3“ንጉሡን በክፋታቸው፣

አለቆችንም በሐሰታቸው ያስደስታሉ።

4ሊጡ ቦክቶ ኩፍ እንደሚል፣

ዳቦ ጋጋሪው እሳት መቈስቈስ እስከማያስፈልገው ድረስ፣

እንደሚነድድ ምድጃ፣

ሁሉም አመንዝራ ናቸው።

5በንጉሣችን የበዓል ቀን፣

አለቆች በወይን ጠጅ ስካር ጋሉ፤

እርሱም ከፌዘኞች ጋር ተባበረ።

6ልባቸው እንደ ምድጃ የጋለ ነው፤

በተንኰል ይቀርቡታል፤

ቍጣቸው ሌሊቱን ሙሉ ይጤሳል፤

እንደሚነድድም እሳት በማለዳ ይንበለበላል።

7ሁሉም እንደ ምድጃ የጋሉ ናቸው፤

ገዦቻቸውን ፈጁ፤

ንጉሦቻቸው ሁሉ ወደቁ፤

ከእነርሱም ወደ እኔ የቀረበ ማንም የለም።

8“ኤፍሬም ከአሕዛብ ጋር ተደባለቀ፤

ኤፍሬም ያልተገላበጠ ቂጣ ነው።

9እንግዶች ጕልበቱን በዘበዙ፤

እርሱ ግን አላስተዋለም።

ጠጕሩም ሽበት አወጣ፤

እርሱ ግን ልብ አላለም።

10የእስራኤል ትዕቢት በራሱ ላይ መሰከረበት፤

ይህ ሁሉ ሆኖ ግን፣

ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር አልተመለሰም፤

እርሱንም አልፈለገም።

11“ኤፍሬም በቀላሉ እንደምትታለል፣

አእምሮም እንደሌላት ርግብ ነው፤

አንድ ጊዜ ወደ ግብፅ ይጣራል፤

ሌላ ጊዜ ደግሞ ወደ አሦር ይዞራል።

12ሲበርሩ፣ መረቤን በላያቸው እዘረጋለሁ፤

እንደ ሰማይ ወፎችም ጐትቼ አወርዳቸዋለሁ፤

ስለ ክፉ ሥራቸውም፣

በጕባኤ መካከል እቀጣቸዋለሁ።

13ወዮ ለእነርሱ፤

ከእኔ ርቀው ሄደዋልና!

ጥፋት ይምጣባቸው!

በእኔ ላይ ዐምፀዋልና።

ልታደጋቸው ፈለግሁ፤

እነርሱ ግን በእኔ ላይ ሐሰት ይናገራሉ።

14ከልባቸው ወደ እኔ አይጮኹም፤

ነገር ግን በዐልጋቸው ላይ ሆነው ያለቅሳሉ።

ስለ እህልና ስለ አዲስ የወይን ጠጅ

ይሰበሰባሉ፤

ነገር ግን ከእኔ ዘወር ብለዋል።

15እኔ አሠለጠንኋቸው፤ አጠነከርኋቸውም፤

እነርሱ ግን ዐደሙብኝ።

16ወደ ከንቱ ነገር ተመለሱ፤

ዒላማውን እንደ ሳተ ቀስት ናቸው፤

መሪዎቻቸው ስለ ክፉ ቃላቸው፣

በሰይፍ ይወድቃሉ፤

በዚህም ምክንያት በግብፅ ምድር፣

መዘባበቻ ይሆናሉ።”

Thai New Contemporary Bible

โฮเชยา 7:1-16

1เมื่อใดก็ตามที่เราจะรักษาอิสราเอล

เมื่อนั้นบาปทั้งหลายของเอฟราอิมจะถูกตีแผ่

และอาชญากรรมของสะมาเรียจะถูกเปิดโปง

พวกเขาชอบการหลอกลวง

พวกขโมยพังเข้าไปในบ้านเรือน

โจรผู้ร้ายก็ปล้นชิงตามท้องถนน

2แต่พวกเขาไม่สำนึก

ว่าเราจดจำการกระทำอันชั่วร้ายทั้งปวงของพวกเขา

บาปของพวกเขาท่วมท้นเหนือพวกเขา

มันอยู่ตรงหน้าเราเสมอ

3“พวกเขาทำให้กษัตริย์พอพระทัยด้วยความชั่วช้าของพวกเขา

ทำให้บรรดาเจ้านายพอใจด้วยคำโกหกของพวกเขา

4พวกเขาล้วนแล้วแต่เป็นคนเล่นชู้

เร่าร้อนเหมือนเตาอบ

ที่คนทำขนมปังไม่ต้องโหมไฟในเตานั้น

ตั้งแต่ลงมือนวดแป้งจนก้อนแป้งขึ้นฟู

5ในวันฉลองกษัตริย์ของเรา

บรรดาเจ้านายก็เร่าร้อนด้วยฤทธิ์เหล้าองุ่น

และกษัตริย์นั้นก็จับมือกับคนเยาะเย้ย

6จิตใจของพวกเขาเหมือนเตาอบ

พวกเขาใช้เล่ห์เพทุบายเข้าหากษัตริย์

อารมณ์ของเขาคุกรุ่นอยู่ตลอดคืน

และตอนเช้าก็ร้อนแรงเหมือนไฟลุกจ้า

7พวกเขาทุกคนร้อนเหมือนเตาอบ

กลืนกินผู้ปกครองของพวกเขา

กษัตริย์ทั้งปวงของเขาล้มลง

และไม่มีสักคนในพวกเขาร้องทูลเรา

8“เอฟราอิมเข้าปะปนกับชาติต่างๆ

เอฟราอิมเป็นเหมือนขนมปิ้งที่ไม่ได้พลิกด้าน

9คนต่างชาติสูบพลังวังชาของเขาไป

แต่เขาไม่รู้สึกตัวเลย

ผมของเขาหงอกประปรายแล้ว

แต่เขาไม่ได้สังเกตเลย

10ความหยิ่งผยองของอิสราเอลปรักปรำตนเอง

แม้จะเป็นเช่นนี้แล้ว

เขาก็ไม่ยอมหันมาหาพระยาห์เวห์พระเจ้าของเขา

หรือแสวงหาพระองค์

11“เอฟราอิมเป็นเหมือนนกเขา

ที่ถูกหลอกง่ายและไร้สติ

เดี๋ยวร้องหาอียิปต์

เดี๋ยวหันมาหาอัสซีเรีย

12เมื่อพวกเขาไป เราจะเหวี่ยงตาข่ายของเราจับเขาไว้

เราจะดึงพวกเขาลงมาเหมือนนกในอากาศ

เมื่อเราได้ยินเสียงเขาจับกลุ่มกัน

เราจะจับเขา

13วิบัติแก่พวกเขา

เพราะเขาหลงทางไปจากเรา!

หายนะจงมีแก่เขา

เพราะเขากบฏต่อเรา!

เราปรารถนาจะไถ่เขาเหลือเกิน

แต่เขาพูดเท็จกับเรา

14พวกเขาไม่ได้ร้องเรียกเราจากใจจริง

เอาแต่คร่ำครวญบนที่นอน

พวกเขารวมตัวกัน7:14 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูบางฉบับ และฉบับ LXX. ว่าพวกเขากรีดตนเองเพื่อเมล็ดข้าวและเหล้าองุ่นใหม่

แต่กลับหันหนีไปจากเรา

15เราได้ฝึกฝนพวกเขาและทำให้เขาเข้มแข็งขึ้น

แต่เขาก็คิดการร้ายต่อเรา

16พวกเขาไม่ได้หันมาหาองค์ผู้สูงสุด

พวกเขาเหมือนคันธนูที่บิดเบี้ยว

ผู้นำของพวกเขาจะล้มลงด้วยดาบ

เพราะถ้อยคำอวดดี

ด้วยเหตุนี้พวกเขาจะถูกเย้ยหยัน

ในดินแดนอียิปต์