ሆሴዕ 12 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 12:1-14

1ኤፍሬም የነፋስ እረኛ ነው፤

ቀኑን ሙሉ የምሥራቅን ነፋስ ይከተላል፤

ሐሰትንና ዐመፅን ያበዛል።

ከአሦር ጋር ቃል ኪዳን ያደርጋል፤

የወይራ ዘይትንም ወደ ግብፅ ይልካል።

2እግዚአብሔር በይሁዳ ላይ የሚያቀርበው ክስ አለው፤

ያዕቆብን12፥2 ያዕቆብ ማለት ተረከዝ ይይዛል ማለት ሲሆን፣ ያታልላል ለማለት ዘይቤአዊ አገላለጽ ነው። እንደ መንገዱ ይቀጣዋል፤

እንደ ሥራውም ይከፍለዋል።

3በማሕፀን ሳለ የወንድሙን ተረከዝ ያዘ፤

ሙሉ ሰውም ሲሆን ከአምላክ ጋር ታገለ።

4ከመልአኩም ጋር ታገለ፤ አሸነፈውም፤

በፊቱ ሞገስን ለማግኘት አልቅሶ ለመነው፣

እርሱንም በቤቴል አገኘው፤

በዚያም ከእርሱ ጋር ተነጋገረ፤

5እርሱም ሁሉን የሚገዛ አምላክ እግዚአብሔር

የሚታወቅበት ስሙም እግዚአብሔር ነው።

6ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤

ፍቅርንና ፍትሕን ጠብቅ፤

ዘወትርም በአምላክህ ታመን።

7ነጋዴው በሐሰተኛ ሚዛን ይሸጣል፤

ማጭበርበርንም ይወድዳል።

8ኤፍሬም እንዲህ እያለ ይታበያል፤

“እኔ ባለጠጋ ነኝ፤ ሀብታምም ሆኛለሁ፤

ይህ ሁሉ ሀብት እያለኝ፣

ምንም ዐይነት በደል ወይም ኀጢአት አያገኙብኝም።”

9“ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ፣12፥9 ወይም በግብፅ ከነበራችሁበት ጊዜ አንሥቶ አምላካችሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤

በዓመት በዓላችሁ ቀን ታደርጉ እንደ ነበረው ሁሉ፣

እንደ ገና በድንኳኖች እንድትቀመጡ

አደርጋችኋለሁ።

10ለነቢያት ተናገርሁ፤

ራእይንም አበዛሁላቸው፤

በእነርሱም በኩል በምሳሌ ተናገርሁ።”

11ገለዓድ ክፉ ነው፤

ሕዝቡም ከንቱ ናቸው፤

ኮርማዎችን በጌልገላ ይሠዋሉን?

መሠዊያዎቻቸው በታረሰ መሬት ላይ እንዳለ፣

የድንጋይ ክምር ይሆናሉ።

12ያዕቆብ ወደ ሶርያ12፥12 ሰሜን መስጴጦምያን ያመለክታል ሸሸ፤

እስራኤል ሚስት ለማግኘት ሲል አገለገለ፤

ዋጋዋንም ለመክፈል በጎችን ጠበቀ።

13እግዚአብሔር በነቢይ አማካይነት እስራኤልን ከግብፅ አወጣ፤

በነቢይም በኩል ተንከባከበው።

14ኤፍሬም ግን ክፉኛ አስቈጣው፤

ጌታውም የደም አፍሳሽነቱን በደል በላዩ ላይ ያደርግበታል፤

ስለ ንቀቱም የሚገባውን ይከፍለዋል።

New International Reader’s Version

Hosea 12:1-14

1The people of Ephraim look to others for help.

It’s like chasing the wind.

The wind they keep chasing

is hot and dry.

They tell more and more lies.

They are always hurting others.

They make a peace treaty with Assyria.

They send olive oil to Egypt to get help.

2The Lord is bringing charges against Judah.

He will punish Jacob’s people

because of how they act.

He’ll pay them back

for the evil things they’ve done.

3Even before Jacob was born,

he was holding on to his brother’s heel.

When he became a man,

he struggled with God.

4At Peniel he struggled with the angel and won.

Jacob wept and begged for his blessing.

God also met with him at Bethel.

He talked with him there.

5He is the Lord God who rules over all.

His name is the Lord.

6People of Jacob, you must return to your God.

You must hold on to love and do what is fair.

You must trust in your God always.

7You are like a trader who uses dishonest scales.

You love to cheat others.

8People of Ephraim, you brag,

“We are very rich.

We’ve become wealthy.

And no one can prove we sinned

to gain all this wealth.”

9The Lord says,

“I have been the Lord your God

ever since you came out of Egypt.

But I will make you live in tents again.

That is what you did when you celebrated

the Feast of Booths in the desert.

10I spoke to the prophets.

They saw many visions.

I gave you warnings through them.”

11The people of Gilead are evil!

They aren’t worth anything!

Gilgal’s people sacrifice bulls to other gods.

Their altars will become like piles of stones

on a plowed field.

12Jacob ran away to the country of Aram.

There Israel served Laban to get a wife.

He took care of sheep to pay for her.

13The prophet Moses brought Israel up from Egypt.

The Lord used him to take care of them.

14But Ephraim’s people have made the Lord very angry.

Their Lord will hold them accountable for the blood they’ve spilled.

He’ll pay them back for the shameful things they’ve done.