ሆሴዕ 11 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 11:1-12

የእግዚአብሔር ፍቅር ለእስራኤል

1“እስራኤል ገና ሕፃን ሳለ ወደድሁት፤

ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት።

2እስራኤል ግን አብዝቼ በጠራኋቸው11፥2 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ቅጆች እንዲሁ ሲሆኑ፣ ዕብራይስጡ ግን በጠሯቸው ይላል። ቍጥር፣

አብዝተው ከእኔ11፥2 ሰብዐ ሊቃናት እንዲሁ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን ከእነርሱ ይላል። ራቁ፤

ለበኣል አማልክት ሠዉ፤

ለምስሎችም ዐጠኑ።

3ኤፍሬምን እጁን ይዤ፣

እንዲራመድ ያስተማርሁት እኔ ነበርሁ፤

ነገር ግን የፈወስኋቸው እኔ እንደ ሆንሁ፣

እነርሱ አላስተዋሉም።

4በሰው የርኅራኄ ገመድ፣

በፍቅርም ሰንሰለት ሳብኋቸው፤

ቀንበሩን ከጫንቃቸው ላይ አነሣሁላቸው፤

ዝቅ ብዬም መገብኋቸው።

5“ታዲያ ንስሓ መግባትን እንቢ በማለታቸው፣

ወደ ግብፅ አይመለሱምን?

አሦርስ አይገዛቸውምን?

6በከተሞቻቸው ላይ ሰይፍ ይመዘዛል፤

የበሮቻቸውን መወርወሪያ ይቈርጣል፤

ስለ ክፉ ዕቅዳቸውም ይደመስሳቸዋል።

7ሕዝቤ ከእኔ ዘወር ማለትን መረጡ፤

ወደ ልዑል ቢጣሩም፣

በምንም ዐይነት አያከብራቸውም።

8“ኤፍሬም ሆይ፤ እንዴት እጥልሃለሁ?

እስራኤል ሆይ፤ እንዴትስ አሳልፌ እሰጥሃለሁ?

እንዴት እንደ አዳማ አደርግሃለሁ?

እንዴትስ እንደ ሲባዮ እፈጽምብሃለሁ?

ልቤ በውስጤ ተናወጠ፤

ምሕረቴም ሁሉ ተነሣሥቷል።

9የቍጣዬን መቅሠፍት አላመጣም፤

ተመልሼም ኤፍሬምን አላጠፋም፤

እኔ በመካከላችሁ ያለሁ ቅዱስ አምላክ ነኝ እንጂ፣

ሰው አይደለሁምና፣

በቍጣ አልመጣም።11፥9 ወይም በማንኛውም ከተማ ላይ በተቃውሞ አልመጣም

10እግዚአብሔርን ይከተላሉ፤

እርሱም እንደ አንበሳ ያገሣል፤

እርሱ ሲያገሣ፣

ልጆቹ እየተንቀጠቀጡ ከምዕራብ ይመጣሉ።

11እንደ ወፍ ከግብፅ፣

እንደ ርግብ ከአሦር፣

እየበረሩ ይመጣሉ፤

እኔም በቤታቸው አኖራቸዋለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

የእስራኤል ኀጢአት

12ኤፍሬም በሐሰት፣

የእስራኤልም ቤት በተንኰል ከበበኝ፤

ይሁዳ ለአምላክ የማይገዛ፣

የታመነውን ቅዱሱን የሚቃወም ነው።

New International Version

Hosea 11:1-12

God’s Love for Israel

1“When Israel was a child, I loved him,

and out of Egypt I called my son.

2But the more they were called,

the more they went away from me.11:2 Septuagint; Hebrew them

They sacrificed to the Baals

and they burned incense to images.

3It was I who taught Ephraim to walk,

taking them by the arms;

but they did not realize

it was I who healed them.

4I led them with cords of human kindness,

with ties of love.

To them I was like one who lifts

a little child to the cheek,

and I bent down to feed them.

5“Will they not return to Egypt

and will not Assyria rule over them

because they refuse to repent?

6A sword will flash in their cities;

it will devour their false prophets

and put an end to their plans.

7My people are determined to turn from me.

Even though they call me God Most High,

I will by no means exalt them.

8“How can I give you up, Ephraim?

How can I hand you over, Israel?

How can I treat you like Admah?

How can I make you like Zeboyim?

My heart is changed within me;

all my compassion is aroused.

9I will not carry out my fierce anger,

nor will I devastate Ephraim again.

For I am God, and not a man—

the Holy One among you.

I will not come against their cities.

10They will follow the Lord;

he will roar like a lion.

When he roars,

his children will come trembling from the west.

11They will come from Egypt,

trembling like sparrows,

from Assyria, fluttering like doves.

I will settle them in their homes,”

declares the Lord.

Israel’s Sin

12Ephraim has surrounded me with lies,

Israel with deceit.

And Judah is unruly against God,

even against the faithful Holy One.11:12 In Hebrew texts this verse (11:12) is numbered 12:1.