1እስራኤል የተንዠረገገ ወይን ነበር፤
ብዙ ፍሬም አፈራ፤
ፍሬው በበዛ መጠን፣
ብዙ መሠዊያዎችን ሠራ፤
ምድሩ በበለጸገ መጠን፣
የጣዖታት ማምለኪያ ዐምዶችን አስጌጠ።
2ልባቸው አታላይ ነው፤
ስለዚህም በደላቸውን ይሸከማሉ።
እግዚአብሔር መሠዊያዎቻቸውን ያወድማል፤
የጣዖት ማምለኪያ ዐምዶቻቸውን ያፈራርሳል።
3እነርሱም፣ “እኛ ንጉሥ የለንም፤
እግዚአብሔርን አላከበርንምና፤
ንጉሥ ቢኖረንስ፣
ምን ሊያደርግልን ይችል ነበር?” ይላሉ።
4ከንቱ ተስፋ ይሰጣሉ፤
በሐሰት በመማል፣
ቃል ኪዳን ያደርጋሉ፤
ስለዚህም ፍርድ፣
በዕርሻ ውስጥ እንደሚገኝ መርዛማ ዐረም ይበቅላል።
5በሰማርያ የሚኖረው ሕዝብ፣
በቤትአዌን ስላለው የጥጃ ጣዖት ይፈራል፤
ሕዝቡም ያለቅስለታል፤
በክብሩ እጅግ ደስ ያላቸው ሁሉ፣
አመንዝራ ካህናትም እንደዚሁ ያለቅሱለታል፤
በምርኮ ከእነርሱ ተወስዷልና።
6ለታላቁ ንጉሥ እንደ እጅ መንሻ፣
ወደ አሦር ይወሰዳል፤
ኤፍሬም ይዋረዳል፤
እስራኤልም ስለ ጣዖቱ ያፍራል።10፥6 ወይም ስለ ምክሩ
7ሰማርያና ንጉሧ፣
በውሃ ላይ እንዳለ ኵበት ተንሳፍፈው ይጠፋሉ።
8የእስራኤል ኀጢአት የሆነው፣
የአዌን ማምለኪያ ኰረብታ ይጠፋል፤
እሾኽና አሜኬላ ይበቅልባቸዋል፤
መሠዊያዎቻቸውንም ይወርሳል፤
በዚያን ጊዜ ተራሮችን፣ “ሸፍኑን!”
ኰረብታዎችንም፣ “ውደቁብን!” ይላሉ።
9“እስራኤል ሆይ፤ ከጊብዓ ጊዜ ጀምሮ ኀጢአት ሠራችሁ፤
በዚያም ጸናችሁ፤10፥9 ወይም በዚያም አቋም ወሰዳቸው
በጊብዓ የነበሩትን ክፉ አድራጊዎች፣
ጦርነት አልጨረሳቸውምን?
10በፈለግሁ ጊዜ እቀጣቸዋለሁ፤
ስለ ድርብ ኀጢአታችሁም ይቀጧቸው ዘንድ፣
በእነርሱ ላይ ይሰበሰባሉ፤
11ኤፍሬም ማበራየት እንደምትወድድ፣
እንደ ተገራች ጊደር ነው፤
በተዋበ ጫንቃዋም ላይ፣
ቀንበርን አኖራለሁ፤
ኤፍሬምን እጠምዳለሁ፤
ይሁዳ ያርሳል፤
ያዕቆብም መሬቱን ያለሰልሳል።
12ለራሳችሁ ጽድቅን ዝሩ፤
የጽኑ ፍቅርን ፍሬ ዕጨዱ፤
ዕዳሪውንም መሬት ዕረሱ፤
እርሱም መጥቶ፣
ጽድቅን በላያችሁ እስኪያዘንብ ድረስ፣
እግዚአብሔርን የምትፈልጉበት ጊዜ ነውና።
13እናንተ ግን ክፋትን ዘራችሁ፤
ኀጢአትንም ዐጨዳችሁ፤
የሐሰትንም ፍሬ በላችሁ።
በራሳችሁ ጕልበት፣
በተዋጊዎቻችሁም ብዛት ታምናችኋልና፣
14ሰልማን፣ ቤት አርብኤልን በጦርነት ጊዜ እንዳፈራረሰ፣
እናቶችንም ከልጆቻቸው ጋር በምድር ላይ እንደ ፈጠፈጣቸው፣
ሽብር በሕዝብህ ላይ ይመጣል፤
ምሽጎችህም ሁሉ ይፈራርሳሉ።
15ስለዚህ ቤቴል ሆይ፤ ክፋትሽ ታላቅ ስለሆነ፣
በአንቺም ላይ እንደዚሁ ይሆናል፤
ያ ቀን ሲደርስም፣
የእስራኤል ንጉሥ ፈጽሞ ይጠፋል።”
1Israel is an empty vine, he bringeth forth fruit unto himself: according to the multitude of his fruit he hath increased the altars; according to the goodness of his land they have made goodly images.10.1 an…: or, a vine emptying the fruit which it giveth10.1 images: Heb. statues, or, standing images 2Their heart is divided; now shall they be found faulty: he shall break down their altars, he shall spoil their images.10.2 Their heart…: or, He hath divided their heart10.2 break…: Heb. behead10.2 images: Heb. statues, or, standing images 3For now they shall say, We have no king, because we feared not the LORD; what then should a king do to us? 4They have spoken words, swearing falsely in making a covenant: thus judgment springeth up as hemlock in the furrows of the field. 5The inhabitants of Samaria shall fear because of the calves of Beth-aven: for the people thereof shall mourn over it, and the priests thereof that rejoiced on it, for the glory thereof, because it is departed from it.10.5 the priests…: or, Chemarim 6It shall be also carried unto Assyria for a present to king Jareb: Ephraim shall receive shame, and Israel shall be ashamed of his own counsel. 7As for Samaria, her king is cut off as the foam upon the water.10.7 the water: Heb. the face of the water 8The high places also of Aven, the sin of Israel, shall be destroyed: the thorn and the thistle shall come up on their altars; and they shall say to the mountains, Cover us; and to the hills, Fall on us.
9O Israel, thou hast sinned from the days of Gibeah: there they stood: the battle in Gibeah against the children of iniquity did not overtake them. 10It is in my desire that I should chastise them; and the people shall be gathered against them, when they shall bind themselves in their two furrows.10.10 when…: or, when I shall bind them for their two transgressions, or, in their two habitations 11And Ephraim is as an heifer that is taught, and loveth to tread out the corn; but I passed over upon her fair neck: I will make Ephraim to ride; Judah shall plow, and Jacob shall break his clods.10.11 her…: Heb. the beauty of her neck 12Sow to yourselves in righteousness, reap in mercy; break up your fallow ground: for it is time to seek the LORD, till he come and rain righteousness upon you. 13Ye have plowed wickedness, ye have reaped iniquity; ye have eaten the fruit of lies: because thou didst trust in thy way, in the multitude of thy mighty men. 14Therefore shall a tumult arise among thy people, and all thy fortresses shall be spoiled, as Shalman spoiled Beth-arbel in the day of battle: the mother was dashed in pieces upon her children. 15So shall Beth-el do unto you because of your great wickedness: in a morning shall the king of Israel utterly be cut off.10.15 your…: Heb. the evil of your evil