시편 47 – KLB & NASV

Korean Living Bible

시편 47:1-9

세상의 왕이신 하나님

(고라 자손의 시. 성가대 지휘자를 따라 부른 노래)

1너희 모든 백성들아,

손뼉을 치며

즐거운 소리로 하나님께 외쳐라.

2가장 높으신 여호와는

두려워해야 할 분이시니

그는 온 세상을 다스리는

위대한 왕이심이라.

3여호와께서 세계 만민을

우리 발 아래 복종하게 하시고

4우리가 살 땅을 택하셨으니

47:4 또는 ‘사랑하신 야곱의 영화로다’사랑하는 자기 백성의

자랑스런 유산이라네.

5하나님이 기쁨의 함성과

나팔 소리 가운데

47:5 암시됨.자기 보좌로 올라가신다.

6찬양하라. 하나님을 찬양하라.

찬양하라. 우리의 왕을 찬양하라.

7하나님은

온 세계를 다스리는 왕이시다.

노래로 그를 찬양하라.

8하나님이

거룩한 보좌에 앉아

온 세상을 다스리신다.

9이방 나라 통치자들이 모여서

아브라함의 하나님의

백성이 되는구나.

세상의 모든 47:9 또는 ‘방패는’왕들이

하나님께 속했으니

그가 크게 높임을 받는구나.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 47:1-9

መዝሙር 47

እግዚአብሔር፣ የእስራኤል ንጉሥና የዓለም ጌታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1ሕዝቦች ሁላችሁ እጆቻችሁን አጨብጭቡ፤

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር እልል በሉ።

2በምድር ሁሉ ላይ ታላቅ የሆነው ንጉሥ፣

ልዑል እግዚአብሔር የሚያስፈራ ነውና።

3ሕዝቦችን ከእኛ በታች አደረገ፤

መንግሥታትንም ከእግራችን ሥር አስገዛልን።

4ለሚወድደው ለያዕቆብ ክብር የሆነችውን፣

ርስታችንን እርሱ መረጠልን። ሴላ

5አምላክ በእልልታ፣

እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።

6አምላካችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

ንጉሣችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

7እግዚአብሔር የምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና፤

ምርጥ ዝማሬ47፥7 ዕብራይስጡ ማስኪል ይላል፤ ይኸውም የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የሙዚቃውን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። አቅርቡለት።

8እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ነግሧል፤

እግዚአብሔር በተቀደሰ ዙፋኑ ላይ ተቀምጧል።

9ከአብርሃም አምላክ ሕዝብ ጋር፣

የሕዝቦች መኳንንት ተሰበሰቡ፤

የምድር ነገሥታት47፥9 ወይም ጋሾች የእግዚአብሔር ናቸውና፤

እርሱም እጅግ ከፍ ከፍ ያለ ነው።