시편 123 – KLB & NASV

Korean Living Bible

시편 123:1-4

멸시받는 자의 호소

(성전에 올라가는 노래)

1하늘에 계시는 주여,

내가 눈을 들어

주를 바라봅니다.

2종이 자기 주인의 손을 바라보듯이

우리가 우리 하나님

여호와를 바라보며

주께서 우리를

불쌍히 여기실 때까지

우리가 기다립니다.

3여호와여, 우리를

불쌍히 여기시고

불쌍히 여기소서.

우리가 심한 멸시를 받고 있습니다.

4부자들이 우리를 조롱하며

교만한 자들이

우리를 경멸하고 있습니다.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 123:1-4

መዝሙር 123

የተጨነቀ ሰው ጸሎት

መዝሙረ መዓርግ።

1በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጥህ ሆይ፤

ዐይኖቼን ወደ አንተ አነሣለሁ።

2የባሪያዎች ዐይን ወደ ጌታቸው እጅ፣

የባሪያዪቱም ዐይን ወደ እመቤቷ እጅ እንደሚመለከት፣

ምሕረት እስከሚያደርግልን ድረስ፣

የእኛም ዐይኖች ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ይመለከታሉ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ንቀት በዝቶብናልና፣

ማረን፤ እባክህ ማረን።

4ነፍሳችን የቅንጡዎች ስድብ፣

የትዕቢተኞችም ንቀት እጅግ በዝቶባታል።