Hosea 14 – KJV & NASV

King James Version

Hosea 14:1-9

1O Israel, return unto the LORD thy God; for thou hast fallen by thine iniquity. 2Take with you words, and turn to the LORD: say unto him, Take away all iniquity, and receive us graciously: so will we render the calves of our lips.14.2 receive…: or, give good 3Asshur shall not save us; we will not ride upon horses: neither will we say any more to the work of our hands, Ye are our gods: for in thee the fatherless findeth mercy.

4¶ I will heal their backsliding, I will love them freely: for mine anger is turned away from him. 5I will be as the dew unto Israel: he shall grow as the lily, and cast forth his roots as Lebanon.14.5 grow: or, blossom14.5 cast…: Heb. strike 6His branches shall spread, and his beauty shall be as the olive tree, and his smell as Lebanon.14.6 spread: Heb. go 7They that dwell under his shadow shall return; they shall revive as the corn, and grow as the vine: the scent thereof shall be as the wine of Lebanon.14.7 grow: or, blossom14.7 scent: or, memorial

8Ephraim shall say, What have I to do any more with idols? I have heard him, and observed him: I am like a green fir tree. From me is thy fruit found. 9Who is wise, and he shall understand these things? prudent, and he shall know them? for the ways of the LORD are right, and the just shall walk in them: but the transgressors shall fall therein.

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 14:1-9

በረከትን ለማግኘት ንስሓ መግባት

1እስራኤል ሆይ፤ በኀጢአትህ ምክንያት ስለ ወደቅህ፣

ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ተመለስ።

2የምትሉትን ቃል ይዛችሁ፣

ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ፤

እንዲህም በሉት፤

“ኀጢአታችንን ሁሉ ይቅር በለን፤

የከንፈራችንንም ፍሬ እንድናቀርብ፣14፥2 ወይም እንደ ኮርማዎች መሥዋዕት የከንፈራችንን ፍሬ እንድናቀርብ

በምሕረትህ ተቀበለን።

3አሦር ሊያድነን አይችልም፤

በጦር ፈረሶችም ላይ አንቀመጥም፤

ከእንግዲህም የገዛ እጆቻችን የሠሯቸውን፣

‘አምላኮቻችን’ አንላቸውም፤

ድኻ ዐደጉ ከአንተ ርኅራኄ ያገኛልና።”

4“እኔ ከዳተኛነታቸውን እፈውሳለሁ፤

እንዲሁ እወድዳቸዋለሁ፤

ቍጣዬ ከእነርሱ ተመልሷልና።

5እኔ ለእስራኤል እንደ ጠል እሆናለሁ፤

እንደ ውብ አበባ ያብባል፤

እንደ ሊባኖስ ዝግባም፣

ሥር ይሰድዳል፤

6ቅርንጫፉ ያድጋል፤

ውበቱ እንደ ወይራ ዛፍ፣

ሽታውም እንደ ሊባኖስ ዝግባ ይሆናል።

7ሰዎች እንደ ገና ከጥላው በታች ያርፋሉ፤

እርሱም እንደ እህል ይለመልማል፤

እንደ ወይን ተክል ያብባል፤

ዝናውም እንደ ሊባኖስ የወይን ጠጅ ይወጣል።

8ኤፍሬም ሆይ፤ ከእንግዲህ ከጣዖት ጋር

ምን ጕዳይ አለኝ?14፥8 ወይም ከእንግዲህ ከጣዖት ጋር ኤፍሬም ሌላ ምን አለው?

የምሰማህና የምጠነቀቅልህ እኔ ነኝ፤

እኔ እንደ ለመለመ የጥድ ዛፍ ነኝ፤

ፍሬያማነትህም ከእኔ የተነሣ ነው።”

9ጥበበኛ የሆነ እነዚህን ነገሮች ያስተውላል፤

አስተዋይም እነዚህን ነገሮች ይረዳል።

የእግዚአብሔር መንገድ ቅን ነውና፤

ጻድቃን ይሄዱበታል፤

ዐመፀኞች ግን ይሰናከሉበታል።