詩篇 64 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

詩篇 64:1-10

64

1-2神よ、この訴えに耳を傾け、

残忍な悪者どもの企みから守ってください。

3彼らの舌は、剣のように研ぎすまされていて、

私をひどく傷つけます。

情け容赦ないことばを矢のように、

この胸に射かけてくるのです。

4彼らは待ち伏せては、

罪のない者を不意打ちにしますが、

何かを恐れるということもありません。

5彼らは互いに励まし、悪事を行うのです。

ひそかに示し合わせては罠をしかけ、

「まさか、気づかれるはずがない」と言っています。

6目を光らせて悪事を重ねる機会をねらっているのです。

いくらでも時間をかけて、際限のない悪知恵を働かせ、

策略を巡らします。

7しかし、神から不意に矢が飛んで来て、

彼らを突き刺します。

8彼らはよろめいてのけぞり、

敵対していた相手の手によって、

息の根を止められるのです。

それを見ていた人々はみな、あざ笑います。

9同時に、すべての人は恐れに取りつかれ、

神の奇跡の偉大さを口にするのです。

こうして、神は驚くべきことをなさるお方だと

思い知ります。

10正しい人は主を信頼して喜び、

賛美のことばを惜しみません。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 64:1-10

መዝሙር 64

የተሳዳቢዎች ቅጣት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1አምላክ ሆይ፤ የብሶት ቃሌን ስማ፤

ሕይወቴንም ከሚያስፈራ የጠላት ዛቻ ከልላት።

2ከክፉዎች አድማ ሰውረኝ፤

ከዐመፀኞችም ሸንጎ ጋርደኝ።

3እነርሱ ምላሳቸውን እንደ ሰይፍ ይስላሉ፤

መርዘኛ ቃላቸውንም እንደ ፍላጻ ያነጣጥራሉ።

4አሸምቀው ንጹሑን ሰው ይነድፉታል፤

ድንገት ይነድፉታል፤ አይፈሩምም።

5ክፉ ተግባር ለማከናወን እርስ በርስ ይመካከራሉ፤

በስውር ወጥመድ ለመዘርጋት ይነጋገራሉ፤

“ማንስ ሊያየን ይችላል?”64፥5 ወይም ማንስ ሊያያቸው ይችላል ይባባላሉ።

6ግፍን ያውጠነጥናሉ፤

ደግሞም፣ “የረቀቀች ሤራ አዘጋጅተናል” ይላሉ፤

አቤት! የሰው ልቡ፣ አእምሮውም እንዴት ጥልቅ ነው!

7እግዚአብሔር ግን በፍላጻው ይነድፋቸዋል፤

እነርሱም ድንገት ይቈስላሉ።

8በገዛ ምላሳቸው ያሰናክላቸዋል፤

ጥፋትንም ያመጣባቸዋል፤

የሚያዩአቸውም ሁሉ በትዝብት ራሳቸውን ይነቀንቃሉ።

9የሰው ልጆች ሁሉ ይፈራሉ፤

የእግዚአብሔርን ሥራ በይፋ ያወራሉ፤

ያደረገውንም በጥሞና ያሰላስላሉ።

10ጻድቅ በእግዚአብሔር ደስ ይበለው፤

እርሱንም መጠጊያ ያድርገው፤

ልበ ቅኖችም ሁሉ ደስ ይበላቸው።