箴言 知恵の泉 19 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 19:1-29

19

1人をだまして金持ちになるより、

貧しくても正直に生きるほうが幸せです。

2よく調べもせずに突っ走るのは、

失敗のもとです。

3人は自分の不注意でチャンスを逃しては、

それを主のせいにします。

4金持ちには友がたくさんできますが、

貧しい人にはだれも寄りつきません。

5偽証すれば罰せられ、

うそをつけば罰を免れません。

6気前のいい人は大ぜいの人に好かれ、

だれとでも友になります。

7貧しいと、

友ばかりか兄弟にもそっぽを向かれます。

どんなに呼んでも、去った人は戻りません。

8知恵のある人は、

自分の一番大事な仕事を愛して成功します。

9偽証すれば罰せられ、

うそをつけば捕まります。

10愚か者が成功し、

使用人が主人を支配するのはふさわしくありません。

11利口な人は侮辱されても、

忍耐を働かせて信用を得ます。

12王の怒りはライオンのうなり声のように恐ろしく、

優しいことばは草に降りる露のように快いものです。

13不従順な子は、

父にとってわずらわしい存在です。

文句ばかり言う妻は、

したたり続ける雨もりのようにやっかいです。

14家や財産なら父親でも息子に残すことができます。

賢い妻は、主に与えていただくしかありません。

15怠けて眠りこけてばかりいると、

そのうち飢えることになります。

16いのちが惜しければ命令を守りなさい。

命令を無視する者は死にます。

17貧しい人に手を差し伸べるのは、

主に貸すのと同じです。

あとで主が報いてくれます。

18まだ望みのあるうちに子どもを懲らしめなさい。

放っておいて、その一生を台なしにしてはいけません。

19短気な者が失敗したら、自分で後始末をさせなさい。

一度でも助けてやると、くり返すようになります。

20忠告はできるだけ聞いて、賢く生きなさい。

21人はたくさんの計画を立てますが、

主の計画だけが成るのです。

22親切な人はだれにも好かれます。

貧しくても、うそつきよりは良いのです。

23主を恐れることは、幸せで安全な生活のかぎです。

24目の前に食べ物があるのに、

口に入れようともしない怠け者がいます。

25人をさげすむ者を罰すれば見せしめになり、

知恵のある人をしかると、ますます賢くなります。

26親に乱暴する者は辱めを受けます。

27間違っていると思う教えを聞くのはやめなさい。

28偽りの証人は正しい裁判を侮り、

こりずにまた罪を犯します。

29さばきをさげすんで守らない者は、

きびしく罰せられます。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 19:1-29

1ንግግሩ ጠማማ ከሆነ ዐጕል ሰው ይልቅ፣

ያለ ነውር የሚሄድ ድኻ ሰው ይሻላል።

2ዕውቀት አልባ የሆነ ቀናኢነት መልካም አይደለም፤

ጥድፊያም መንገድን ያስታል።

3ሰው በራሱ ተላላነት ሕይወቱን ያበላሻል፤

በልቡ ግን እግዚአብሔርን ያማርራል።

4ሀብት ብዙ ወዳጅ ታፈራለች፤

ድኻን ግን ወዳጁ ገሸሽ ያደርገዋል።

5ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤

ውሸት የሚነዛም ሳይቀጣ አይቀርም።

6ብዙ ሰዎች በገዥ ዘንድ ሞገስ ለማግኘት ያሸረግዳሉ፤

ስጦታን ከሚሰጥ ሰው ጋር ሁሉም ወዳጅ ነው።

7ድኻ በሥጋ ዘመዶቹ ሁሉ የተጠላ ነው፤

ታዲያ ወዳጆቹማ የቱን ያህል ይሸሹት!

እየተከታተለ ቢለማመጣቸውም፣

ከቶ አያገኛቸውም።19፥7 ለዚህ ዐረፍተ ነገር የገባው የዕብራይስጡ ትርጓሜ በትክክል አይታወቅም።

8ጥበብን ገንዘቡ የሚያደርጋት ነፍሱን ይወድዳል፤

ማስተዋልን የሚወድዳት ይሳካለታል።

9ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤

ውሸት የሚነዛም ይጠፋል።

10ተላላ ተንደላቅቆ መኖር አይገባውም፤

ባሪያ የመሳፍንት ገዥ ከሆነማ የቱን ያህል ይከፋ!

11ጥበብ ሰውን ታጋሽ ታደርገዋለች፤

በደልን ንቆ መተውም መከበሪያው ነው።

12የንጉሥ ቍጣ እንደ አንበሳ ግሣት ነው፤

በፊቱ ሞገስ ማግኘትም በሣር ላይ እንዳለ ጠል ነው።

13ተላላ ልጅ ለአባቱ መጥፊያ ነው፤

ጨቅጫቃ ሚስትም እንደማያቋርጥ ጠፈጠፍ ናት።

14ቤትና ሀብት ከወላጆች ይወረሳሉ፤

አስተዋይ ሚስት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ናት።

15ስንፍና ከባድ እንቅልፍ ላይ ይጥላል፤

ዋልጌም ሰው ይራባል።

16ትእዛዞችን የሚያከብር ሕይወቱን ይጠብቃል፤

መንገዱን የሚንቅ ግን ይሞታል።

17ለድኻ የሚራራ ለእግዚአብሔር ያበድራል፤

ስላደረገውም ተግባር ዋጋ ይከፍለዋል።

18ገና ተስፋ ሳለ፣ ልጅህን ሥርዐት አስይዘው፤

ሲሞት ዝም ብለህ አትየው።

19ግልፍተኛ ሰው ቅጣትን መቀበል ይገባዋል፤

በምሕረት ካለፍኸው ሌላም ጊዜ አይቀርልህም።

20ምክርን ስማ፤ ተግሣጽን ተቀበል፤

በመጨረሻም ጠቢብ ትሆናለህ።

21በሰው ልብ ብዙ ሐሳብ አለ፤

የሚፈጸመው ግን የእግዚአብሔር ሐሳብ ነው።

22ሰው የሚመኘው ጽኑ ፍቅር19፥22 ወይም የሰው ሥሥት ውርደት ወይም ኀፍረት ያመጣበታል። ነው፤

ውሸታም ከመሆንም ድኻ መሆን ይሻላል።

23እግዚአብሔርን መፍራት ወደ ሕይወት ይመራል፤

እንዲህ ያለውም ሰው እፎይ ብሎ ያርፋል፤ መከራም አያገኘውም።

24ሰነፍ እጁን ከወጭቱ ያጠልቃል፤

ወደ አፉ ግን መመለስ እንኳ ይሳነዋል።

25ፌዘኛን ግረፈው፤ ብስለት የሌለውም ማስተዋልን ይማራል፤

አስተዋይን ዝለፈው፤ ዕውቀትን ይገበያል።

26አባቱን የሚዘርፍ፣ እናቱንም የሚያሳድድ፣

ዕፍረትና ውርደት የሚያመጣ ልጅ ነው።

27ልጄ ሆይ፤ እስቲ ምክርን ማዳመጥ ተው፤

ከዕውቀትም ቃል ትስታለህ።

28አባይ ምስክር በፍትሕ ላይ ያፌዛል፤

የክፉዎችም አፍ በደልን ይሰለቅጣል።

29ለፌዘኞች ቅጣት፣

ለተላሎችም ጀርባ ጅራፍ ተዘጋጅቷል።