箴言 知恵の泉 18 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 18:1-24

18

1自分のことしか考えない者は、

あらゆる規則に盾をつき、

自分のやり方を押し通します。

2神に背く者はただ大声で叫びたいだけで、

事実はどうでもよいのです。

3悪いことをすれば必ず恥をかきます。

4知恵のある人は、

深い流れのように味わいのあることを言います。

5裁判官が悪者をかばい、

無実の者を罰するのはよくありません。

6-7愚か者はすぐにけんかをします。

愚か者の口は破滅のもとで、

いつも危ない橋を渡ります。

8陰口はよだれの出そうなごちそうのように、

大いに食欲をそそります。

9怠け者は破壊する者の兄弟です。

10主は絶対安全なとりで、

正しい人はその中に逃げ込みます。

11金持ちは浅はかにも、

「富がすべて。富さえあれば絶対安全だ」と思っています。

12高慢になると身を滅ぼし、

謙遜になると人から称賛されます。

13よく聞かないで早合点すると、恥をかきます。

14心がしっかりしていれば病気にも負けません。

しかし、心が失せたら望みはありません。

15知識のある人はいつも、

新しいことを知ろうと努力します。

16贈り物には不思議な力があります。

地位ある人の前に彼を導きます。

17だれの話でも、他の人が裏を明かして、

全貌がわかるまではもっともらしく思えます。

18いくら言い争っても解決しないときは、

くじで決めなさい。

そうすれば丸く収まります。

19堅固な城を攻め落とすより、

けんかした友人と仲直りするほうが大変です。

怒った相手は、頑としてあなたを受けつけません。

20忠告するのが上手な人は、

ごちそうをたらふく食べたときのような

満足感をいつも味わいます。

21おしゃべり好きは、

おしゃべりの後始末をさせられます。

うっかり間違ったことを言って

死ぬ場合もあるのです。

22良い妻を見つける人は幸せ者です。

良い妻は神からのすばらしい贈り物です。

23貧しい人は拝むようにして頼み、

金持ちは相手を軽蔑しきって答えます。

24友人のふりをする「友人」もいれば、

実の兄弟より親しい友人もいます。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 18:1-24

1ወዳጅነትን የማይፈልግ ሰው የራሱን ፍላጎት ብቻ ይከተላል፤

ቅን የሆነውንም ፍርድ ሁሉ ይቃወማል።

2ተላላ ከማስተዋል ርካታን አያገኝም፤

የራሱን ሐሳብ በመግለጥ ግን ደስ ይለዋል።

3ክፋት ስትመጣ ንቀት ትከተላለች፤

ከዕፍረትም ጋር ውርደት ትመጣለች።

4ከሰው አፍ የሚወጡ ቃላት ጥልቅ ውሆች ናቸው፤

የጥበብም ምንጭ እንደሚንዶለዶል ፏፏቴ ነው።

5ለክፉ ሰው ማድላት፣

ንጹሑንም ፍትሕ መንሣት ተገቢ አይደለም።

6የተላላ ከንፈር ጠብ ያመጣበታል፤

አፉም በትር ይጋብዛል።

7ተላላ ሰው አፉ መጥፊያው ነው፤

ከንፈሮቹም ለነፍሱ ወጥመድ ናቸው።

8የሐሜተኛ ቃል እንደ ጣፋጭ ጕርሻ ነው፤

ወደ ሰው ውስጣዊ ክፍል ዘልቆ ይገባል።

9ለሥራው ደንታ የሌለው ሰው፣

የአጥፊ ወንድም ነው።

10የእግዚአብሔር ስም ጽኑ ግንብ ነው፤

ጻድቅ ወደ እርሱ በመሮጥ ተገን ያገኝበታል።

11የባለጠጎች ሀብት የተመሸገ ከተማቸው ነው፤

እንደማይወጣ ረዥም ግንብም ይቈጥሩታል።

12ከውድቀቱ በፊት ሰው ልቡ ይታበያል፤

ትሕትና ግን ክብርን ትቀድማለች።

13ከማዳመጡ አስቀድሞ የሚመልስ፣

ቂልነትና ዕፍረት ይሆንበታል።

14በሕመም ጊዜ፣ ሰውን መንፈሱ ትደግፈዋለች፤

የተሰበረውን መንፈስ ግን ማን ሊሸከም ይችላል?

15የአስተዋይ ልብ ዕውቀትን ይገበያል፤

የጠቢብም ጆሮ አጥብቆ ይሻታል።

16እጅ መንሻ ለሰጪው መንገድ ትከፍትለታለች፤

ታላላቅ ሰዎች ፊትም ታቀርበዋለች።

17አስቀድሞ ጕዳዩን የሚያሰማ ትክክለኛ ይመስላል፤

ይኸውም ባላንጣው መጥቶ እስከሚመረመር ድረስ ነው።

18ዕጣ መጣጣል ሙግትን ያስቆማል፤

ኀይለኛ ባላንጣዎችንም ይገላግላል።

19የተበደለ ወንድም ከተመሸገ ከተማ ይበልጥ የማይበገር ነው፤

ጠቡም እንደ ጠንካራ የግንብ መዝጊያ ነው።

20ሰው በአንደበቱ ፍሬ ሆዱ ይጠግባል፤

በከንፈሩም ምርት ይረካል።

21አንደበት የሞትና የሕይወት ኀይል አላት፤

የሚወድዷትም ፍሬዋን ይበላሉ።

22ሚስት የሚያገኝ መልካም ነገርን ያገኛል፤

ከእግዚአብሔርም ዘንድ ሞገስን ይቀበላል።

23ድኻ በመለማመጥ ምሕረት ይለምናል፤

ሀብታም ግን በማናለብኝነት ይመልሳል።

24ወዳጅ የሚያበዛ ሰው ራሱን ለጥፋት ይዳርጋል፤

ነገር ግን ከወንድም አብልጦ የሚቀርብ ጓደኛም አለ።