ヨブ 記 5 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

ヨブ 記 5:1-27

5

1助けを呼び求めても、だれも答えてくれない。

神々によりすがっても、助けてもらえない。

2怒り狂い、のたうち回って息絶えるだけだ。

3神に背く者は、しばらくは栄えても、

思いもよらない災いにみまわれる。

4彼らの子どもたちは、だれにもかばってもらえず、

簡単にだまされる。

5せっかく上げた収穫も人手に渡り、

その富は、ほかの人の渇きをいやす。

6罪の種をまいた者には、罰として不幸が襲う。

7火種から勢いよく炎が吹き上げるように、

人は罪と不幸に向かってまっしぐらに進むのだ。

8だから、あなたに忠告したい。

神に罪を告白しなさい。

9神は、目をみはるような奇跡を何度でも行うからだ。

10神は地に雨を降らせて田畑をうるおし、

11貧しい者と謙遜な者を富ませ、

苦しむ者を安全な場所へ連れて行く。

12神は、悪賢い者の計画をくつがえす。

13彼らは知恵をこらして計画を練り、

そのわなに自分でかかる。

14彼らは夜だけでなく、日中でも、

目の見えない者のように手探りで歩く。

15神は、このような横暴な連中から、

身寄りのない者や貧しい者を救う。

16こうして、貧しい者は希望を見いだし、

悪者の牙はへし折られる。

17神に誤りを正してもらえる人は、

なんと幸せなことか。

神の懲らしめをないがしろにしてはいけない。

自分で罪を犯し、招いた結果なのだから。

18神は傷つけても包帯を巻き、治してくださる。

19何度でも救い出してくださる。

だから、災いがあなたに寄りつく暇もない。

20あなたはききんの時には死から、

戦いの時には剣から守られる。

21人の中傷も苦にならず、将来の心配もなくなる。

22あなたは戦いもききんも心配する必要がなく、

野獣に襲われることもない。

23どう猛な野獣は、あなたと平和協定を結ぶからだ。

24家を留守にしても、何の心配もない。

倉庫には、だれも指一本ふれないからだ。

25あなたの息子たちは、なくてはならぬ人物となり、

子孫は草のように増え広がる。

26麦は、収穫の時までは

どんなことがあっても刈り取られない。

そのように、あなたも幸せな一生を送り、

長寿を全うする。

27このことがうそ偽りでないことを

私は経験から知ったのだ。

あなたのためを思えばこそ忠告するのだ。

私の助言を聞いてくれ。」

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 5:1-27

1“እስቲ ተጣራ፤ የሚመልስልህ አለን?

ከቅዱሳንስ ወደ ማንኛው ዘወር ትላለህ?

2ሞኙን ሰው ብስጭት ይገድለዋል፤

ቂሉንም ቅናት ያጠፋዋል።

3ቂል ሰው ሥር ሰድዶ አየሁት፤

ግን ድንገት ቤቱ ተረገመ።

4ልጆቹ የኑሮ ዋስትና የራቃቸው፤

በፍርድ አደባባይ ጥቃት የደረሰባቸው፣ ታዳጊ የሌላቸው ናቸው።

5ከእሾኽ መካከል እንኳ አውጥቶ፣

ራብተኛ ሰብሉን ይበላበታል፤

ጥማተኛም ሀብቱን ይመኝበታል።

6ችግር ከምድር አይፈልቅም፤

መከራም ከመሬት አይበቅልም።

7ፍንጣሪው ከእሳቱ ላይ ሽቅብ እንደሚወረወር፣

ሰውም ለመከራ ይወለዳል።

8“እኔ ብሆን ኖሮ፣ ወደ እግዚአብሔር በቀረብሁ፣

ጕዳዬንም በፊቱ በገለጽሁለት ነበር።

9እርሱ፣ የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮች፣

የማይቈጠሩም ታምራት ያደርጋል።

10ምድሪቱን በዝናብ ያረሰርሳል፤

ሜዳውንም ውሃ ያጠጣል።

11የተዋረዱትን በከፍታ ቦታ ያስቀምጣል፤

ያዘኑትንም ወደ አስተማማኝ ስፍራ ያወጣቸዋል።

12እጃቸው ያሰቡትን እንዳይፈጽም፣

የተንኰለኞችን ዕቅድ ያከሽፋል።

13ጠቢባንን በጥበባቸው ይይዛል፤

የተንኰለኞችንም ሤራ ያጠፋል።

14ቀኑ ጨለማ ይሆንባቸዋል፤

በቀትርም ጊዜ በሌሊት እንዳለ ሰው በዳበሳ ይሄዳሉ።

15ችግረኛውን ከአፋቸው ሰይፍ፣

ከኀይለኛውም እጅ ያድነዋል።

16ስለዚህ ድኻ ተስፋ አለው፤

ዐመፅም አፏን ትዘጋለች።

17“እነሆ፤ እግዚአብሔር የሚገሥጸው ሰው ምስጉን ነው፤

ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን5፥17 በዕብራይስጥ ሻዳይ ማለት ሲሆን፣ በዚህ ቍጥርና በኢዮብ መጽሐፍ ውስጥም እንዲሁ ነው። አምላክ ተግሣጽ አትናቅ።

18እርሱ ያቈስላል፤ ይፈውሳል፤

እርሱ ይሰብራል፤ በእጁም ይጠግናል፤

19እርሱ ከስድስት መቅሠፍት ይታደግሃል፤

በሰባተኛውም ጕዳት አያገኝህም።

20በራብ ጊዜ ከሞት፣

በጦርነትም ከሰይፍ ያድንሃል።

21ከምላስ ጅራፍ ትሰወራለህ፤

ጥፋት ሲመጣም አትፈራም።

22በጥፋትና በራብ ላይ ትሥቃለህ፤

የምድርንም አራዊት አትፈራም።

23ከሜዳ ድንጋዮች ጋር ትዋዋላለህና፤

የዱር አራዊትም ከአንተ ጋር ይስማማሉ።

24ድንኳንህ በሚያስተማምን ሁኔታ እንዳለ ታውቃለህ፤

በረትህን ትቃኛለህ፤ አንዳችም አይጐድልብህም።

25ዘሮችህ አያሌ እንደሚሆኑ፣

የምትወልዳቸውም እንደ ሣር እንደሚበዙ ታውቃለህ።

26የእህል ነዶ ጐምርቶ በወቅቱ እንደሚሰበሰብ፣

ዕድሜ ጠግበህ ወደ መቃብር ትሄዳለህ።

27“እነሆ፤ ይህን ሁሉ መርምረናል፤ እውነት ሆኖ አግኝተነዋል፤

ስለዚህ ልብ በል፤ ተቀበለውም።”