7
神に選ばれた人々
1それから私は、四人の天使が地の四すみに立っているのを見ました。彼らは、四方からの風をしっかり押さえていたので、木の葉一枚そよがず、海面は鏡のように静かでした。 2次に、もう一人の天使が、生ける神の大きな刻印を持って、東から来るのが見えました。彼は、地と海とを破壊する権限を与えられた四人の天使に、大声で叫びました。 3「お待ちなさい。私たちが、神に仕える人々の額に神の刻印を押し終わるまでは、手出しをしてはなりません。地にも海にも木にも、害を加えてはいけません。」
4-8それから私が、「いったい何人の人に、神の刻印がつけられたのでしょうか」と尋ねると、「十四万四千人」という答えが返ってきました。その人々は、イスラエルの全十二部族から選ばれていました。内訳は次のようです。ユダの部族一万二千人、ルベンの部族一万二千人、ガドの部族一万二千人、アセルの部族一万二千人、ナフタリの部族一万二千人、マナセの部族一万二千人、シメオンの部族一万二千人、レビの部族一万二千人、イッサカルの部族一万二千人、ゼブルンの部族一万二千人、ヨセフの部族一万二千人、ベニヤミンの部族一万二千人。
9その後、私の目には、おびただしい群衆が映りました。あらゆる国民、民族、国語の人々で、とても数えきれません。彼らは白い衣をまとい、しゅろの枝を手にして、王座と小羊との前に立っていました。 10そして、声を張り上げ、「救いは、王座に座っておられる神と小羊とから来ます」と叫んでいました。 11天使はみな、王座と長老、それに四つの生き物の回りに集まり、ひれ伏して神を礼拝してから、 12こう言いました。「アーメン。祝福と栄光と知恵と感謝と誉れと力と勢いとが、永遠に神にありますように。アーメン。」
13その時、二十四人の長老の一人が、私に尋ねました。「この白い衣の人たちがだれだか、わかりますか。どこから来たか知っていますか。」 14「わかりません。どうか教えてください」と答えると、彼は言いました。「あの人たちは激しい迫害をくぐり抜け、小羊の血で、その衣を洗って白くした人たちです。 15だから、こうして神の王座の前にいて、昼も夜も、神殿で奉仕しているのです。そして、王座に座っておられる方によって、安全にかくまわれています。 16彼らはもう二度と飢えることも、渇くこともありません。灼熱の太陽からも守られています。 17それは、王座の正面に立たれる小羊が、羊飼いとして彼らを養い、いのちの水の泉に導いてくださるからです。また神は、彼らの目からあふれる涙を、すっかりぬぐい取ってくださるのです。」
መቶ አርባ አራት ሺሑ መታተማቸው
1ከዚህ በኋላ አራት መላእክት በአራቱ የምድር ማእዘኖች ቆመው አየሁ፤ እነርሱም ነፋስ በምድር ወይም በባሕር፣ ወይም በማንኛውም ዛፍ ላይ እንዳይነፍስ አራቱን የምድር ነፋሶች ያዙ። 2ከዚያም የሕያው አምላክ ማኅተም ያለው ሌላ መልአክ ከምሥራቅ ሲመጣ አየሁ፤ እርሱም ምድርንና ባሕርን ለመጕዳት ሥልጣን የተሰጣቸውን አራቱን መላእክት በታላቅ ድምፅ እንዲህ አላቸው፤ 3“በአምላካችን አገልጋዮች ግንባር ላይ ማኅተም እስከምናደርግባቸው ድረስ ምድርን ወይም ባሕርን፣ ወይም ዛፎችን አትጕዱ።” 4የታተሙትንም ቍጥር ሰማሁ፤ እነርሱም ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ መቶ አርባ አራት ሺሕ ነበሩ፤
5ከይሁዳ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከሮቤል ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከጋድ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
6ከአሴር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከንፍታሌም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከምናሴ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
7ከስምዖን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከሌዊ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከይሳኮር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
8ከዛብሎን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከዮሴፍ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣
ከብንያም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ታተሙ።
ነጭ ልብስ የለበሱ እጅግ ብዙ ሕዝብ
9ከዚህም በኋላ አየሁ፤ እነሆ፤ በዙፋኑና በበጉ ፊት ማንም ሊቈጥራቸው የማይችል ከሕዝብ፣ ከነገድ፣ ከወገን፣ ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሕዝብ ቆመው ነበር፤ እነርሱም ነጭ ልብስ ለብሰው፣ የዘንባባ ዝንጣፊ በእጃቸው ይዘው ነበር። 10በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ጮኹ፤
“ማዳን በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው፣
የአምላካችንና የበጉ ነው።”
11መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ፣ በአራቱም ሕያዋን ፍጡራን ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑ ፊት በግንባራቸው ተደፍተው ለእግዚአብሔር ሰገዱ፤ 12እንዲህም ይሉ ነበር፤
“አሜን፤
ውዳሴና ክብር፣
ጥበብ፣ ምስጋናና፣ ሞገስ፣
ኀይልና ብርታትም፣
ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤
አሜን።”
13ከዚያም ከሽማግሌዎቹ አንዱ፣ “እነዚህ ነጭ ልብስ የለበሱት እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ?” አለኝ።
14እኔም፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ” አልሁት።
እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፤ ልብሳቸውንም በበጉ ደም ዐጥበው አንጽተዋል። 15ስለዚህ፣
“በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት ሆነው፣
ቀንና ሌሊት በመቅደሱ ያገለግሉታል፤
በዙፋኑም ላይ የተቀመጠው ድንኳኑን
በላያቸው ይዘረጋል፤
16ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም፤
ከዚህም በኋላ አይጠሙም፤
ፀሓይ አይመታቸውም፤
ሐሩሩም ሁሉ አያቃጥላቸውም፤
17ምክንያቱም በዙፋኑ መካከል ያለው
በግ እረኛቸው ይሆናል፤
ወደ ሕይወት ውሃ ምንጭም ይመራቸዋል፤
እግዚአብሔር እንባን ሁሉ ከዐይናቸው ያብሳል።”