エゼキエル書 7 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

エゼキエル書 7:1-27

7

終わりの時がくる

1続いて、神からのことばが私にありました。

2「イスラエルに告げよ。あなたの見るところはみな、東も西も、南も北も、もう終わりだ。この国はもう終わりが来た。 3わたしは、偶像を拝んだあなたに怒りをぶつける。もう絶体絶命だ。 4わたしはあなたから目を背け、あわれんだりはしない。とことんまで罰する。そうすれば、わたしが主であることを、あなたがたは知るようになるだろう。」

5-6神である主は言います。「次から次へと災いを送って、あなたにとどめを刺そう。終わりはすでにきている。終局の破滅が待っているだけだ。 7ああ、イスラエルよ。滅亡の日のきざしは現れ、時はきた。苦難の日は近い。それは喜びの声を上げる日ではなく、苦しみもだえて叫ぶ日だ。 8-9やがて、わたしは憤りを注ぎ、おまえたちの悪のすべてを徹底的に罰しよう。もはや、あなたを惜しまず、あわれまない。これをしているのが、主であるわたしであることを、あなたがたは知るようになるだろう。

10-11ついに、さばきの日がきた。朝日が昇ってくる。あなたの悪と高ぶりは頂点に達し、行き着くところまで行ったからだ。富におごり、高ぶる悪者は、一人も生き長らえない。高慢の鼻は完全にへし折られ、あなたがたの運命を嘆く者もいなくなる。

12さあ、その時がきた。その日が近づいた。神の怒りがその地に臨むので、買う物もなく、売る物もなくなる。 13主がイスラエルの民全体にさばきを宣言したので、たとえ商人が生き長らえても、商売はできなくなる。すべての人が滅ぼされる。罪に満ちた生活をしている者はだれも立ち直れない。

14イスラエル軍に、『進め』と角笛を吹き鳴らしても、だれも聞こうとしない。わたしの怒りがすべての者に臨むからだ。 15城壁の外に出れば、敵が彼らを殺そうと待ちかまえている。城壁の内側にとどまれば、ききんと疫病で滅ぼし尽くされる。 16運よく逃れた者も、山々にひそむ鳩のように、その寂しさを嘆き悲しみ、自分の罪のために泣き悲しむ。 17手も弱くなり、ひざもがくがく震えるようになる。 18彼らは荒布をまとい、恐怖と恥で包まれ、悲しみと自責の念にかられて頭をそる。

19金銀を投げ捨てよ。怒りの日には何の価値もなくなるのだから、がらくたのように放り出せ。彼らの罪の根本は金銀を愛することにある。それが、腹を満たすことも満足させることもできなくなるのだ。 20わたしの神殿を美しく飾るために与えた金で、彼らは偶像を造ってしまった。それゆえ、わたしはそれを全部取り上げる。 21戦利品として外国人や悪者どもに与える。彼らはわたしの神殿を汚すだろう。 22その時、わたしは見て見ぬふりをする。止めはしない。彼らは強盗のように宝物をあさり、神殿を廃墟のようにする。

23わたしの民のために鎖を用意せよ。この国は流血の罪で満ちているからだ。エルサレムは暴虐に満ちているので、わたしはその住民を奴隷とする。 24諸国の中でも最悪の国を、エルサレムに来させよう。彼らの家々を占領させ、彼らが誇っている要塞を破壊させ、神殿を汚させ、高慢の鼻をへし折らせる。 25イスラエルを切り捨てる時が、いよいよきた。平和を求めても得られない。 26-27災いの上に災いが、悲しみの上に悲しみが、惨事の上に惨事が襲う。彼らは預言者の指導を求める。それなのに、祭司も長老も、王も君主も、ただ手をこまねいているだけで、絶望のうちに泣き悲しんでいる。わたしは彼らが行った悪に対し、それに十分見合った報いをするので、彼らは恐怖のあまり震えおののく。そして、わたしが主であることを知るようになる。」

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 7:1-27

ፍጻሜው ደረሰ

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“አንተ የሰው ልጅ ሆይ፤ ጌታ እግዚአብሔር ለእስራኤል ምድር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ፍጻሜ! በአራቱም የምድሪቱ ማእዘን

ፍጻሜ መጥቷል!

3አሁንም መጨረሻሽ ደርሷል፤

ቍጣዬን በአንቺ ላይ አፈስሳለሁ፤

እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤

ስለ ጸያፍ ተግባርሽ ሁሉ፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

4በርኅራኄ ዐይን አልመለከትሽም፤

ምሕረትም አላደርግልሽም፤

ስለ አካሄድሽና በመካከልሽ ስላለው ጸያፍ ተግባር፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ፤

በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።’

5“ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘መዓት! ተሰምቶ የማይታወቅ መዓት7፥5 አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች እንዲሁ ናቸው፤ አንዳንድ የዕብራይስጥና የሱርስት የጥንት ቅጆች ግን በጥፋት ላይ ጥፋት ይላሉ ይመጣል።

6ፍጻሜ መጥቷል!

ፍጻሜ መጥቷል!

በአንቺ ላይ ተነሣሥቷል፤

እነሆ፤ ደርሷል!

7እናንት በምድሪቱ የምትኖሩ ሆይ፤

የጥፋት ፍርድ መጥቶባችኋል፤

ጊዜው ደርሷል፤

በተራሮች ላይ እልልታ ሳይሆን ሽብር የሚሰማበት ቀን ቀርቧል።

8እነሆ፤ መዓቴን በቅርብ ቀን አፈስስብሻለሁ፤

በአንቺ ላይ ቍጣዬን እፈጽምብሻለሁ፤

እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤

ስለ ጸያፍ ተግባርሽም ሁሉ ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

9በርኅራኄ ዐይን አልመለከትሽም፤

ምሕረት አላደርግልሽም፤

ስለ አካሄድሽና በመካከልሽ ስላለው ጸያፍ ተግባር፣

ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ፤

በዚያ ጊዜ፣ የምቀሥፍ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ታውቃላችሁ።

10“ ‘እነሆ ቀኑ ይኸው ደረሰ!

የጥፋት ፍርድ ተገልጧል፤

በትሩ አቈጥቍጧል፤

ትዕቢት አብቧል።

11ዐመፅ ዐድጋ7፥11 ወይም ዐመፀኛው የክፋት በትር

የክፋት በትር ሆነች፤

ከሕዝቡ አንድም አይተርፍም፤

ከሰዎቹ፣

ከሀብታቸውና እርባና ካለው ነገር

አንዳች አይቀርም።

12ጊዜው ደርሷል፤

ቀኑም ይኸው!

መዓት በሕዝቡ ሁሉ ላይ ስለ መጣ፣

የሚገዛ አይደሰት፤

የሚሸጥም አይዘን።

13ሁለቱ በሕይወት እስካሉ ድረስ

ሻጩ የሸጠውን መሬት አያስመልስም፤

ስለ መላው ሕዝብ የተነገረው ራእይ አይለወጥምና።

ከኀጢአታቸው የተነሣ ሕይወቱን ማትረፍ የሚችል አንድም አይገኝም።

14“ ‘መለከት ቢነፉም፣

ሁሉንም ነገር ቢያዘጋጁም፣

ወደ ጦርነት የሚሄድ አንድ እንኳ አይኖርም፤

መዓቴ በሕዝብ ሁሉ ላይ መጥቷልና።

15በውጭ ሰይፍ፣

በውስጥ ደግሞ ቸነፈርና ራብ አለ፤

በገጠር ያሉት

በሰይፍ ይወድቃሉ፤

በከተማ ያሉትም

በራብና በቸነፈር ያልቃሉ።

16ተርፈው ያመለጡት ሁሉ

በሸለቆ እንደሚኖሩ ርግቦች

ስለ ኀጢአታቸው እያለቀሱ

በተራራ ላይ ይሆናሉ።

17እጅ ሁሉ ይዝላል፤

ጕልበት ሁሉ ውሃ ይሆናል።

18ማቅ ይለብሳሉ፤

ሽብርም ይውጣቸዋል።

ፊታቸው ኀፍረት ይለብሳል፤

ራሳቸውም ይላጫል።

19“ ‘ብራቸውን በየጐዳናው ይጥላሉ፤

ወርቃቸውም እንደ ርኩስ ነገር ይቈጠራል።

በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን

ብራቸውና ወርቃቸው

ሊያድናቸው አይችልም፤

በኀጢአት እንዲወድቁ ዕንቅፋት ሆኖባቸዋልና

በልተው አይጠግቡበትም፤ ሆዳቸውንም አይሞሉበትም።

20በውብ ዕንቋቸው ታብየዋል፤

ይህንም አስጸያፊ የጣዖት ምስሎቻቸውንና

ርኩስ ቅርጻ ቅርጾችን ለመሥራት ተጠቅመውበታል።

ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ወደ ርኩሰት እለውጥባቸዋለሁ።

21ለባዕዳን ዝርፊያ፣ ለምድር ክፉዎችም ብዝበዛ አድርጌ አሳልፌ እሰጣለሁ፤

እነርሱም ያረክሱታል።

22ፊቴን ከእነርሱ እመልሳለሁ፤

እነርሱም የከበረውን ቦታዬን ያረክሳሉ፤

ወንበዴዎች ይገቡበታል፤

ያረክሱታልም።

23“ ‘ምድር በደም መፋሰስ፣

ከተማዪቱም በዐመፅ ተሞልታለችና

ሰንሰለት አዘጋጅ።

24እጅግ የከፉትን ከአሕዛብ አምጥቼ

ቤቶቻቸውን እንዲነጥቁ አደርጋለሁ፣

የኀያላኑንም ትዕቢት አጠፋለሁ፤

መቅደሳቸውም ይረክሳል።

25ሽብር በመጣ ጊዜ ሰላምን ይሻሉ፤

ነገር ግን አያገኟትም።

26ጥፋት በጥፋት ላይ፣

ወሬም በወሬ ላይ ይመጣል።

ራእይን ከነቢይ ለማግኘት ይጥራሉ፤

የሕግ ትምህርት ከካህኑ፣

ምክርም ከሽማግሌው ዘንድ ይጠፋል።

27ንጉሡ ያለቅሳል፤

መስፍኑ ተስፋ መቍረጥን ይከናነባል፤

የምድሪቱም ሕዝብ እጅ ትንቀጠቀጣለች።

የእጃቸውን እከፍላቸዋለሁ፤

ራሳቸው ባወጡት መስፈርት መሠረት

እፈርድባቸዋለሁ።

በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።’ ”