Psalmen 6 – HTB & NASV

Het Boek

Psalmen 6:1-11

1Een psalm van David voor de koordirigent. Te begeleiden met snarenspel en te zingen op de wijs van ‘De Achtste.’

2O Here, nee, straf mij niet

in het vuur van uw toorn!

3Heb medelijden met mij, Here,

want ik ben maar een zwak mens.

Genees mij,

want mijn lichaam is ziek

4en mijn geest verward.

Laat mij toch snel weer tot mijzelf komen!

5Kom, Here, red mijn ziel,

red mij door uw goedheid.

6Want doden kunnen u geen eer bewijzen

en in het dodenrijk kan niemand U loven.

7Het verdriet put mij uit,

elke nacht wordt mijn kussen nat van de vele tranen.

8Mijn ogen staan dof

en mijn blik is duister

omwille van mijn vijanden.

9Verdwijn uit mijn ogen, zondaars,

want de Here heeft mijn tranen gezien

10en mijn smeken gehoord.

Hij zal mijn gebeden beantwoorden.

11Al mijn vijanden zullen voor schut staan,

onverwachts in verwarring raken

en beschaamd de aftocht blazen.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 6:1-10

መዝሙር 6

በጭንቅ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር በሸሚኒት6 ርእሱ በሙዚቃ ውስጥ የሚጠቀሙበት ቃል ሳይሆን አይቀርም።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በቍጣህ

አትገሥጸኝ፤

በመዓትህም አትቅጣኝ።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐቅመ ቢስ ነኝና ማረኝ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐጥንቶቼ ተናግተዋልና ፈውሰኝ።

3ነፍሴ እጅግ ታውካለች፤

እስከ መቼ፣ አንተ እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ድረስ ይሆናል?

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ተመለስና ሕይወቴን ታደጋት፤

ስለ ጽኑ ፍቅርህም አድነኝ፤

5በሞት የሚያስታውስህ የለምና፤

በሲኦልስ6፥5 ወይም በመቃብር ማን ያመሰግንሃል?

6ከመቃተቴ የተነሣ ዝያለሁ፤

ሌሊቱን ሁሉ በልቅሶ ዐልጋዬን አርሳለሁ፤

መኝታዬንም በእንባዬ አሾቃለሁ።

7ዐይኖቼ በሐዘን ብዛት ደክመዋል፤

ከጠላቶቼም ሁሉ የተነሣ ማየት ተስኗቸዋል።

8እናንተ ክፉ አድራጊዎች ሁሉ፤ ከእኔ ራቁ፤

እግዚአብሔር የልቅሶዬን ድምፅ ሰምቷልና።

9እግዚአብሔር ልመናዬን አድምጧል፤

እግዚአብሔር ጸሎቴን ይቀበላል።

10ጠላቶቼ ሁሉ ያፍራሉ፤ እጅግም ይደነግጣሉ፤

በመጡበት ይመለሳሉ፤ ድንገትም ይዋረዳሉ።