Jesaja 12 – HTB & NASV

Het Boek

Jesaja 12:1-6

Een loflied voor God

1Op die dag zult u zeggen: ‘Ik loof U, Here! Uw toorn was op mij, maar nu troost U mij.

2Kijk, God is gekomen om mij te redden! Ik zal vertrouwen en niet bang zijn, want de Here is mijn kracht en mijn lied, Hij is mijn heil. 3Wat is het een vreugde om te drinken uit zijn fontein van heil!’

4Op die wonderbaarlijke dag zult u zeggen: ‘De Here zij gedankt! Geprezen zij zijn Naam! Vertel de wereld over zijn liefdevolle daden. Want Hij is machtig! 5Zing voor de Here, want Hij heeft wonderbaarlijke dingen gedaan. Maak zijn glorie over de hele wereld bekend. 6Laten alle inwoners van Jeruzalem met vreugde juichen, want groot en machtig is de Heilige van Israël, die onder u woont.’

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 12:1-6

የውዳሴ መዝሙር

1በዚያን ቀን እንዲህ ትላለህ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤

ቀድሞ ተቈጥተኸኝ ነበር፤

አሁን ግን ከቍጣህ ተመለስህ፤

ደግሞም አጽናንተኸኛልና አወድስሃለሁ።

2እነሆ፣ እግዚአብሔር ድነቴ ነው፤

እታመናለሁ፣ ደግሞም አልፈራም፤

12፥2 እግዚአብሔር በሚለው ስም ፈንታ ተተክቶ የገባ ነው። ጌታ እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤

ድነቴም ሆኗል።”

3ከድነቴ ምንጮች

ውሃ በደስታ ትቀዳላችሁ።

4በዚያን ቀን እንዲህ ትላላችሁ፤

እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤

ያደረገውንም በአሕዛብ መካከል አስታውቁ፤

ስሙ ከፍ ከፍ ማለቱንም ዐውጁ።

5ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ታላቅ ሥራ ሠርቷልና፤

ይህም ለዓለም ሁሉ ይታወቅ።

6የጽዮን ሕዝብ ሆይ፤ እልል በሉ፤

በደስታም ዘምሩ፤

በመካከላችሁ ያለው የእስራኤል ቅዱስ ታላቅ ነውና።”