1הזכר למאמינים שעליהם לציית לשלטונות ולנציגיהם, ושעליהם להיות מוכנים תמיד לעשות מעשים טובים. 2עליהם להימנע מרכילות, הוצאת דיבה ומריבות, ולעומת זאת להיות עדינים ולהראות ענווה אמיתית לכולם.
3גם אנחנו היינו פעם טיפשים ולא שמענו לקול אלוהים; אנשים שונים הוליכו אותנו שולל, וגרמו לכך שנשתעבד לתשוקות וליצרים שלנו. התקופה ההיא הייתה נוראה; היינו חסרי־שלווה ומנוחה, מלאי קנאה וטינה, שנאנו את כולם וכולם שנאו אותנו. 4אך כאשר אלוהים מושיענו גילה לנו את טוב לבו ואהבתו, 5הוא הושיע אותנו, לא בגלל המעשים הצדיקים שעשינו, אלא מתוך רחמיו. הוא רחץ אותנו מחטאינו, ונתן לנו לידה חדשה וחיים חדשים באמצעות רוח הקודש. 6אלוהים עשה זאת בזכות קורבנו של ישוע המשיח, 7ובחסדו הרב הצדיק אותנו ונתן לנו חלק ונחלה בחיי הנצח, שלהם אנו מצפים. 8כל הדברים שאמרתי לך הם נכונים. הדגש את חשיבותם כדי שהמאמינים יהיו זהירים יותר ויעשו תמיד מעשים טובים, לא רק משום שזו חובתם, אלא משום שזה גם מועיל!
9הימנעו מוויכוחי סרק ומוויכוחים בנושאים השנויים במחלוקת; הימנעו מוויכוחים ומריבות בנוגע לקיום מצוות התורה, שכן הם מיותרים, חסרי־תועלת וגורמים רק נזק. 10אם מישהו מכם גורם לסכסוכים ולחילוקי דעות, הזהירו אותו פעם או פעמיים ולאחר מכן עזבוהו לנפשו, 11כי אדם כזה הוא מושחת וידוע לו היטב שהוא חוטא.
12אני עומד לשלוח אליך את ארטימס או את טוכיקוס. בהגיע אליך אחד מהשניים השתדל לבוא אלי לניקופוליס במהירות האפשרית, כי החלטתי להישאר שם למשך החורף. 13זינס, עורך־הדין, ואפולוס עומדים לצאת למסעם. עזור להם כמיטב יכולתך, ודאג לכך שהמאמינים יספקו את כל צרכיהם, 14כי על המאמינים לבטא את אמונתם במעשיהם הטובים ובהגשת עזרה.
15כולם כאן מוסרים דרישת שלום. מסור בבקשה דרישת שלום חמה לכל המאמינים בכרתים. יברך אתכם אלוהים. – אמן.
በጎ የሆነውን ማድረግ
1ሰዎች ለገዦችና ለባለሥልጣናት እንዲገዙ፣ እንዲታዘዙና መልካም የሆነውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስባቸው። 2እንዲሁም በማንም ላይ ክፉ እንዳይናገሩ፣ ሰላማውያን እንዲሆኑ፣ ለሰዎችም ሁሉ ከልብ የመነጨ ትሕትና እንዲያሳዩ አስገንዝባቸው።
3ቀደም ሲል እኛ ራሳችን ማስተዋል የጐደለን፣ የማንታዘዝ፣ የተታለልን፣ ለተለያየ ምኞትና ምቾት ባሪያ ሆነን የተገዛን ነበርን፤ እየተጣላንና እርስ በርስ እየተጠላላን በክፋትና በምቀኝነት እንኖር ነበር። 4ነገር ግን የአዳኛችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር በተገለጠ ጊዜ፣ 5ስላደረግነው የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነን። ያዳነንም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው፤ 6ይህንም መንፈስ እግዚአብሔር በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእኛ ላይ አትረፍርፎ አፈሰሰው፤ 7ይኸውም በጸጋው ጸድቀን የዘላለምን ሕይወት ተስፋ ይዘን ወራሾች እንድንሆን ነው። 8ይህም የታመነ ቃል ነው። በእግዚአብሔር ያመኑቱ መልካሙን ነገር ለማድረግ ራሳቸውን አሳልፈው ይሰጡ ዘንድ እነዚህን ነገሮች አስረግጠህ እንድትናገር እፈልጋለሁ። ይህ መልካምና ለማንኛውም ሰው የሚጠቅም ነው።
9ነገር ግን ከንቱ ከሆነ ክርክርና ከትውልድ ሐረግ ቈጠራ፣ ከጭቅጭቅና ስለ ሕግ ከሚነሣ ጠብ ራቅ፤ ይህ ዋጋ ቢስና ከንቱ ነውና። 10መከፋፈል የሚያመጣን ሰው አንድ ጊዜ ምከረው፤ ለሁለተኛ ጊዜ አስጠንቅቀው፤ ከዚያ ካለፈ ከእርሱ ጋር አንዳች ነገር አይኑርህ። 11እንዲህ ዐይነቱ ሰው የሳተና ኀጢአተኛ ነው፤ ራሱንም እንደሚኰንን ዕወቅ።
የመጨረሻ ምክር
12አርጢሞንን ወይም ቲኪቆስን ወደ አንተ እንደ ላክሁ እኔ ወዳለሁበት ወደ ኒቆጵልዮን ለመምጣት የተቻለህን ሁሉ አድርግ፤ ክረምቱን በዚያ ላሳልፍ ወስኛለሁ። 13ሕግ ዐዋቂውን ዜማስንና አጵሎስን በጕዟቸው ለመርዳት የተቻለህን ሁሉ አድርግ፤ የሚያስፈልጋቸውንም ሁሉ አሟላላቸው።
14ከእኛ ወገን የሆኑት ለዕለት የሚያስፈልጋቸውን እንዲያገኙና ኑሯቸውም ፍሬ የሌለው እንዳይሆን ለመልካም ሥራ መትጋትን ይማሩ ዘንድ ይገባቸዋል።
15ከእኔ ጋር ያሉት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
ከእምነት የተነሣ ለሚወድዱን ሰላምታ አቅርቡልን።
ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።