Otkrivenje 10 – CRO & NASV

Knijga O Kristu

Otkrivenje 10:1-11

Anđeo i mali svitak

1Ugledam zatim još jednoga jakog anđela kako silazi s neba okružen oblacima, s dugom iznad glave. Lice mu je sjalo poput sunca, a noge poput ognjenih stupova. 2U ruci je imao maleni razvijeni svitak. Desnom nogom stane na more, a lijevom na zemlju 3pa poviče glasno kao da lav riče. Kad vikne, zatutnji sedam gromova.

4Kad je progovorilo sedam gromova htio sam to zapisati, ali začujem glas s neba: “Sačuvaj tajnim što je reklo sedam gromova. To ne zapisuj.”

5Zatim snažni anđeo što je stajao na moru i na zemlji podigne desnu ruku prema nebu. 6Zakune se u ime onoga koji živi u vijeke vjekova, koji je stvorio nebo i sve u njemu, zemlju i sve na njoj, more i sve u njemu te reče: “Bog više neće čekati. 7Kad se oglasi trublja sedmoga anđela, Božji će se tajni naum ispuniti, kao što je svojim slugama navijestio po prorocima.”

8Evo glasa s neba: “Idi i uzmi razvijen svitak od anđela koji stoji na moru i na zemlji.”

9Pristupim mu zato i zamolim ga da mi dade svitak. “Uzmi ga i pojedi”, reče mi. “U ustima će ti biti sladak kao med, ali kad ga progutaš, zagorčit će ti utrobu.” 10Uzmem ga iz njegove ruke i pojedem. U ustima mi je bio sladak, ali mi je zagorčio utrobu. 11Zatim mi reče: “Moraš opet prorokovati narodima, pucima i kraljevima.”

New Amharic Standard Version

ራእይ 10:1-11

መልአኩና ትንሿ መጽሐፍ

1ከዚህ በኋላ ሌላ ብርቱ መልአክ ደመና ተጐናጽፎ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ እርሱም በራሱ ላይ ቀስተ ደመና ነበር። ፊቱ እንደ ፀሓይ፣ እግሮቹ እንደ እሳት ዐምዶች ነበሩ። 2በእጁም የተከፈተች ትንሽ ጥቅልል መጽሐፍ ይዞ ነበር፤ ቀኝ እግሩን በባሕር ላይ፣ ግራ እግሩን በምድር ላይ አኖረ፤ 3እንደሚያገሣ አንበሳም ድምፁን ከፍ አድርጎ ጮኸ፤ በጮኸም ጊዜ የሰባቱ ነጐድጓዶች ድምፆች ተናገሩ። 4ሰባቱ ነጐድጓዶች በተናገሩ ጊዜ፣ ለመጻፍ ተዘጋጀሁ፤ ነገር ግን፣ “ሰባቱ ነጐድጓዶች የተናገሩትን በማኅተም ዝጋው እንጂ አትጻፍ” የሚል ድምፅ ከሰማይ ሰማሁ።

5ከዚህ በኋላ በባሕርና በምድር ላይ ቆሞ ያየሁት መልአክ ቀኝ እጁን ወደ ሰማይ አነሣ፤ 6እርሱም ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው፣ ሰማይንና በውስጡ ያሉትን፣ ምድርንና በውስጧ ያሉትን፣ ባሕርንና በውስጡ ያሉትን በፈጠረው በእርሱ ማለ፤ እንዲህም አለ፤ “ከእንግዲህ መዘግየት አይኖርም፤ 7ነገር ግን ሰባተኛው መልአክ መለከቱን በሚነፋባቸው ቀኖች፣ ለአገልጋዮቹ ለነቢያት በገለጠላቸው መሠረት የእግዚአብሔር ምስጢር ይፈጸማል።”

8ከዚያም ከሰማይ የሰማሁት ድምፅ እንደ ገና እንዲህ ሲል ተናገረ፤ “ሂድ፤ በባሕርና በምድር ላይ ከቆመው መልአክ እጅ የተከፈተችውን ጥቅልል መጽሐፍ ውሰድ።”

9እኔም ወደ መልአኩ ሄጄ ትንሿን ጥቅልል መጽሐፍ እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፤ እርሱም፣ “ውሰድና ብላት፤ ሆድህን መራራ ታደርገዋለች፤ በአፍህ ግን እንደ ማር ትጣፍጣለች” አለኝ። 10ትንሿንም መጽሐፍ ከመልአኩ እጅ ተቀብዬ በላኋት፤ በአፌ እንደ ማር ጣፈጠች፤ ከበላኋት በኋላ ግን ሆዴ መራራ ሆነ፤ 11ከዚያም፣ “ስለ ብዙ ሕዝቦች፣ ወገኖች፣ ቋንቋዎችና ነገሥታት እንደ ገና ትንቢት ልትናገር ይገባሃል” ተባልሁ።